TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን!

#1440ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል #በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሰታወቀ። በአል በሰላም እንዲጠናቀቅ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት፣ ከእምነቱ አባቶችና ከበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ጋር ውይይት እንደተካሄደና ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ወደ ስራው የተገባ መሆኑ ፓሊስ አስታውቋል፡፡

በዚህ መሰረትም ምዕመኑ ለኢድ-ሶላት በሰላም ወጥቶ በሠላም እንዲገባ በዋና ዋና መንገዶች በተለይም በአዲስ አበባ ስታድየም እና በዙሪያው ከበዓሉ አስተባባሪ ወጣቶች ጋር በመቀናጀት ጠንካራ የፀጥታ ሰራ ተከናውኗል፡፡ ለስራው ስኬታማነት የእምነቱ ተከታዮች ላሳዩት ቀና ትብብር የአዲስ አበባ ፖሊሰ ኮሚሽን ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia