TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🎉 ዛሬ ከምሽቱ 12፡30 የማንቸስተር ቀለም ይለያል! ቀይ ወይም ሰማያዊ!! 🔴🔵

🔥ከባድ ትንቅንቅ የማያጣው የማንቸስተር ደርቢ - ማንቸስተር ሲቲ ከ ማንቸስተር ዩናይትድ🔥

🤔ዩናይትድ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከደረሰበት ሽንፈት ለመመለስ ይጓጓል። ሲቲ የሊጉን ዋንጫ ለማንሳትና መሪነቱን ለመቆናጠጥ ይፋለማል፡፡

ይህ ታሪካዊ ፉክክር እንዳያመልጥዎ…

👉ሲቲ ከማንቼ የሚያደርጉትን ፍልሚያ ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።

👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#PremierLeagueOnDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
ደም እንለግስ !

" በወሊድ ወቅት ደም ለሚያስፈልጋቸው እናቶች ደም እንለግስ " ሲል የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጥሪ አቅርቧል።

የሕክምና ኮሌጁ ለቲክቫህ ቤተሰቦች በላከው አጭር መልዕክት የፊታችን የካቲት 28 እና 29 ቀን 2016 ዓ/ም በኮሌጁ 5ኛ በር አካባቢ የደም ልገሳ እንደሚደረግ ጠቁሟል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ አሁን ላይ በወሊድ ወቅት ለእናቶች የሚሆን ደም በጣም እየተፈለገ እንደሆነ ተረድቷል።

ሁሉም የሚችል የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባል ፤ በሁለቱ ቀናት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ በመገኘት ደም እንዲለግስ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ቦታውን ለማታውቁ Google Map ተጠቀሙ።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶች አሳሳቢ እየሆኑና እየሰፉ እንደሄዱ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ሴቶች ማኀበር ሴቶች ላይ የሚደርሱ የተለያዩ ጥቃቶችን በተመለከተ በዘርፉ ከተሰማሩ የተለያዪ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ተቋማት በመጋበዝ የካቲት 20 በአዲስ አበባ የውይይት መድክ አዘጋጅቶ ነበር።

በዚህም ላይ ከተገኙት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ሴቶች ማኀበር በተለይ በጦርነት ወቅት የሚፈጸሙ ፆታዊ ጥቃቶችን ፣ የሕጉን አተገባበር በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥቷል።

በመርሀ ግብሩ ላይ ታድሞ የነበረው የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባል ፦

° በተለይ ከጦርነት፣ ከግጭት ጋር ተያይዞ ፆታዊ ጥቃቶች በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ፣
በምን ያህል ሰዎች ፆታዊ ጥቃቶች እንደተፈጸሙ ለኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ሴቶች ማኀበር ጥያቄዎችን አቅርቧል።

የማኀበሩ የሕግ ድጋፍ መስጫ አስተባባሪ ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳዬ ምን አሉ ?

በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የአቅም ግንባታ፣ ሌጋል ሪሰርች ፣ ሌጋል ኤይድ ይሰጣል። በሌጋል ኤይድ ሴክተራችን የተለያዩ ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች (Sexual harassment, Sexual violence, አካላዊ ድብደባዎች) ሪፖርት ይደረጋሉ።

በLegal aim unit ሪፖርት መሠረት በ2023 አዲስ አበባን ጨምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ በቢሯችን ሪፖርት የተደረጉ ከ4,000 በላይ የፆታዊ ጥቃቶች ተፈጽመዋል። በዚህ ደግሞ ችግሩ ምን ያህል አሳሳቢ እየሆነና እየሰፋ እንደሄደ ማየት እንችላለን።

ሁሉም አካላት በትብብር መስራት ያለውን Finding ማሳወቅ፣ እንዲሁም ደግሞ መፍትሄ መፈለግ፣ ያለውን ጋፕ መድፈን ላይ በትብብር መሰራት አለበት።

ኢትዮጵያ የተለያዩ ፆታዊ ጥቃቶችን በተመለከተ ያጸደቀቻቸው ሕጎች ቢኖሩም አፈጻጸሙ ላይ መሠረታዊ የሆኑ ችግሮች አሉ። ለዚህም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ትኩረት ሊሰጡበት ይገባል።

የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ሴቶች ማኀበር የተለያዩ ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን በመከታተል ሪፖርት የሚያደርግ፣ ከፆታዊ ጥቃት ነፃ የሆነች አገር ለመፍጠር የሚታትር፣ በሁለት ከተማ አስተዳደሮችና በ6 የክልል ከተሞች 55 በሚሆኑ ወረዳዎች የድጋፍ አገልግሎት የሚሰጡ ሴክሽኖች ያሉት፣ ከተቋቋመ ከ28 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ተቋም ነው።

መረጃውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#EOTC

ቅዱስ ፓትርያርኩ " የሃይማኖት አባቶች ከፓለቲካ ገለልተኛ በመሆን ሁሉን በፍቅርና በእኩልነት ማቀራረብ ይገባቸዋል " ሲሉ በ11ኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸው ተናገሩ።

ፓለቲከኞቾም ባልዋሉበት እና ባልተፈቀደላቸው ቦታ በቤተክርስቲያን ጉዳይ ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

ቅዱስነታቸው " የዘመናችን ትውልድ ከተግባር ይልቅ አስመሳይ ሆኖ መታየትን ከቅድስና ይልቅ ነውረ ኃጢአትን፤ ከትሕትና ይልቅ ትዕቢትን የተለማመደ ለሃይማኖትም ሆነ ለማኅበረ ሰብ ጤና ያልተመቸ ትውልድ እንደሆነ በግልጽ ይታያል ሲሉ ተግሳጽ አሰምተዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቀነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት 11ኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸውን አስመልክቶ ምን አሉ ?

- ያለንበት ዘመን ለእግዚአብሔር ክብርን የነሣ፤ ከፍቅርና ከአንድነት የራቀ ራስ ወዳድነትና በቃኝ አለማለትን የወረረው፤ በዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ የተዋጠ ትውልድ የታየበት ዘመን ነው።

- የዘመናችን ትውልድ ከተግባር ይልቅ አስመሳይ ሆኖ መታየትን ከቅድስና ይልቅ ነውረ ኃጢአትን፤ ከትሕትና ይልቅ ትዕቢትን የተለማመደ ለሃይማኖትም ሆነ ለማኅበረሰብ ጤና ያልተመቸ ትውልድ እንደሆነ በግልጽ የሚታይ ነው፤ ይህን አደገኛ አዝማሚያ በማስተዋል ካልታረመ ሂዶ ሂዶ የእግዚአብሔርን ቁጣ ማስከተሉ አይቀርምና እንደ እግዚአብሔር ጥሪ ወደ እሱ ብንመለስ ይሻላል።

- እኛ የሃይማኖት አባቶችም አልጫ የሆነውን የዘመናችንን ትውልድ በትጋት አስተምረን በቈራጥነት ገሥጸንና መክረን ወደ እግዚአብሔር ካልመለስነው ከቁጣው አንድንም። ቅዱስ መጽሐፍ እንዳስተማረን አስተምረነው የማይመለስ ከሆነ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል! እኛ ባለማስተማራችን የሚጎዳ ትውልድ ካለ ግን እኛ የደሙ ተጠያቂዎች መሆናችንን በማያሻማ ሁኔታ ተገልጾአልና ነው፤ የእኛ ኃላፊነት እስከዚህ ድረስ ከባድ መሆኑን ባንዘነጋውም እንደ ዓለሙ በልዩ ልዩ ደካማ አስተሳሰቦችና ተግባራት እየተሰናከልን መሆናችን የአደባባይ ምሥጢር ከሆነ ውሎ አድሮአል።

- እኛ የሃይማኖት አባቶች ዓለም ሲሳሳት ከመገሠጽ ይልቅ አብሮ ማጨብጨብ ተለማምደናል፤ ባናጨበጭብም ዝምታን መርጠናል ነገር ግን ኃላፊነቱን የተረከብነው ጥፋት ሲፈጸም ዝም ብሎ ለማየት አልነበረም፤ ከዓለሙ ጋር አብሮ ለማጨብጨብ ወይም አድማቂ ለመሆንም አልነበረም፤ ከቅዱስ ወንጌሉ መሠረተ ሐሳብ ፍንክች ሳንል ፦
* የእውነት፥
* የፍትሕ የሰላም፥
* የፍቅር፥
* የዕርቅ የይቅርታ የአንድነት፥
* የስምምነት ጠበቃ መሆናችንን ማሳየት ነበረብን፣ ሰውን ሁሉ በእኩልነት በመቀበልና የሁሉም እኩል አባቶች መሆናችንን በተግባር ማስመስከር ይገባን ነበር፤ የተዛባውን በማረም ትውልዱን ለማዳን ያደረግነው ጥረት የሚያረካ እንዳልሆነ ታዛቢው ሁሉ አይቶብናል፡፡

- ለፈተና የተጋለጡ ልጆቻችን ሁሉ የዜግነት የሃይማኖትና የሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር ሰላም ፍቅር፥ ፍትሕ አንድነት በሀገር እንዲነግሥ ሁሉም ድንበሩን ጠብቆ ሕዝቡን የሚያገለግልበት ዓመት እንዲሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ በርትተን መሥራት አለብን። ይህንን ብናደርግ በእውነትም ወደ እግዚአብሔር ተመልሰናል ማለት ነው፤ እኛ ከተመለስን እሱም ወደ እኛ መመለሱ አይጠረጠርም፤ ስለዚህ አሁንም ወደእሱ እንመለስ፡፡

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ " ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን 2 ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ ! " - ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በታሪካዊቷ ዓድዋ ከተማ በነበረው የዓድዋ ድል በዓል  ላይ እምባ እየተናነቃቸው 😭 ንግግር አድርገው ነበር። እሳቸው በእንባ ንግግር ሲያደርጉ የበዓሉ ታዳሚ ህዝብ ከፍተኛ የሀዘን ስሜቱ ከፊቱ ይነበብ እንደነበር በስፍራው…
#ኢትዮጵያ

" የአንድ ሀገር ልጆች እየተገዳደሉ ናቸው !! "

ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዓድዋ በዓል ላይ የተናገሩት ፦

" ከአንዱ ሳናገገም ሌሎች ችግሮችም በሀገራችን አሉ።

በመካከላችን ድልድይ ሳይሆን ግንብ የመገንባት አካሄድም አለ።

ዛሬ በሌሎች ክልሎች ንፁሃን እየሞቱ ናቸው።

በአማራ ክልል እንደዚሁ ከውጭ የመጣን ጠላት ሳይሆን የአንድ ሀገር ልጆች እየተገዳደሉ ናቸው። ህዝቡም በከፍተኛ አደጋ ላይ እየተጣለ ነው።

በሌሎችም እንደዚሁ ኦሮሚያም የሚሞተው ንፁህ ሰው መሞት የሌለበት ነው።

ይሄ ሁላችንም አያገባኝም ሳይሆን ፤ እኔ ላይ አይደርስም ሳይሆን ፤ የት ይደርሳሉም ሳይሆን ሁላችንም ነቅተን ይሄን ያለንን ጀግኖች አባቶቻችን እናቶቻችን የሰጡንን ነፃነት ፣ አንገታችንን ከፍ እንድናደርግ የረዳንን ባንድነት የመስራትን እንደገና ማደስ ያስፈልጋል፤ ይህ ከታሪካችን ጋር መታረቅ ማለት ነው።

ይሄን አደራ ማለት እፈልጋለሁ። "

@tikvahethiopia
ወጋገን ባንክ !

በማንኛውም ጊዜ እና ቦታ በሞባይል ስልክዎ ወጋገን ሞባይል መተግበሪያን ከፕለይስቶር ወይም ከአፕስቶር በማውረድ ምቾትዎ ተጠብቆ ሂሳብዎን ያንቀሳቅሱ፡፡ አገልግሎቱን ለማግኘት የወጋገን ባንክ ሂሳብ በመክፈት የወጋገን የሞባይል ባንክ አገልግሎት *866# ይመዝገቡ፡፡

ከዚያም ቀጣዩን ሂደት ይከተሉ፤
(ሀ) መተግበሪያውን ከአፕስቶር ወይም ጎግል ፕሌይስቶር በማውረድ ስልክዎ ላይ ይጫኑ፤
(ለ) ወደ *866# በመደወል ተራ ቁጥር 8ኛ ላይ የሚገኘውን “Activate Your Mobile Application” የሚለውን ይምረጡ፤
(ሐ) በአጭር ፅሁፍ መልዕክት አገልግሎቱን ማስጀመሪያ የአንድ ጊዜ የይለፍ ቃል (Activation Code) ሲደርስዎት መተግበሪያው ላይ ይህንኑ ሚስጥራዊ ቁጥር ያስገቡ፤
(መ) የሚስጥር ቁጥር በመቀየር አገልግሎቱን መጠቀም መጀመር ይችላሉ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በ866 ነፃ የስልክ መስመር ወደ ደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ይደውሉ፣ ይስተናገዱ፡፡

Download now:
Android:https://play.google.com/store/apps/details?id=com.act.wegagen&hl
IOS:https://apps.apple.com/in/app/wegagen-mobile/id6472656143
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ ሰለሞን ባረጋ ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ አምጥቷል። በግላስኮ ዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በወንዶች 3 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያ በአትሌት ሰለሞን ባረጋ አማካኝነት የነሃስ ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች። ጌትነት ዋለ 4ኛ ወጥቷል። ኢትዮጵያ በዚህ ርቀት በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ላይ የወርቅ ሜዳሊያ ሳታሸንፍ ስትቀር ከ3 ተከታታይ ውድድሮች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ሰለሞን ባረጋ…
#ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ሆና አጠናቀቀች።

በዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም ደግሞ 5 በመሆን አጠናቃለች።

ከማርች 1-3/2024 በእንግሊዝ ግላስጎ ሲካሄድ የ19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሲካሄድ ነበር። በሻምፒዮናው ከ130 በላይ አገሮች የተውጣጡ ከ650 በላይ አትሌቶቸ ተሳትፈዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በ800 ሜትር፣ በ1500 ሜትር እና በ3000 ሜትር በሴትና በወንድ  በአጠቃላይ በ8 ሴቶች እና በ5 ወንዶች በድምሩ በ13 አትሌቶች ተሳትፋለች።

በዚህም #በሴቶች 800 ሜትር ፅጌ ዱጉማ እና በሴቶች 1500 ሜትር ፍሬወይኒ ሀይሉ #የወርቅ፣ በሴቶች 3000 ሜትር ጉዳፍ ፀጋይ የብር እንዲሁም #በወንዶች 3000 ሜትር ሰለሞን ባረጋ የነሃስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።

ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በሁለት ወርቅ አንድ ነሀስ በአንድ ብር በአጠቃላይ በአራት ሜዳሊያዎች በሜዳልያ ሰንጠረዡ   ከአፍሪካ 1ኛ  ከዓለም 5ኛ ደረጃን በመያዝ ጨርሳለች።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

@tikvahethiopia
#ቅሬታ

የፓስፖርት ጉዳይ ...

ከፓስፖርት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች አሰፈላጊው ማስተካከያ እንዲደረግ አሳሰቡ።

" የተሰራ ፓስፖርት ለመስጠት ህዝቡ እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተንገላታ ይገኛል። " ያሉት ለቲክቫህ መልዕክታቸውን ያደረሱ ወገኖች ፤ በቀን የሚሰጠው ፓስፖርት ውስን ነው ብለዋል።

" በቀኑ ስለማይሰጥም ባስቀመጡት ቀን ተገልጋዩ እየተመላለሰ መከራ እየበላ ነው። " ሲሉ ሁኔታውን ገልጸውታል።

በተለይ ጎተራ አካባቢ ሌሊት ወረፋ ለመያዝ ብር  የሚጠይቁ እንዳሉ ፤ አንዳንዱ ከፍሎ ወረፋ እንደሚይዝ የሌለው ደግሞ ሌሊት ሂዶ ከገባ በኋላ ሰልፋን ይበትኑና ቀኑን ሙሉ በህዝብ ሲጫወቱ ውለው 10 ሰዓት ላይ በዱላ ደብድበው እንደሚያስወጡ በምሬት ገልጸዋል።

" በቀጣዩ ሳምንትም እንደዛው። " ሲሉ አክለዋል።

" የብዙ ሰው ቪዛ እየተቃጠለበት ለብዙ ወጪ እየተዳረገ " መሆኑን የሚገልፁት እነዚህ ወገኖች " በየወረዳው ቢበትኑ እንዲሁ። በፊደል ተራ በተለቀቀበት ቀን ቢሰጡ/they mix it/  ጥሩ ነው። የህዝብ እንግልት ግድ የሚሰጠው ካለ መፍትሄ ይፈልግ !! " ሲሉ አሳስበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቅሬታ የፓስፖርት ጉዳይ ... ከፓስፖርት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች አሰፈላጊው ማስተካከያ እንዲደረግ አሳሰቡ። " የተሰራ ፓስፖርት ለመስጠት ህዝቡ እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተንገላታ ይገኛል። " ያሉት ለቲክቫህ መልዕክታቸውን ያደረሱ ወገኖች ፤ በቀን የሚሰጠው ፓስፖርት ውስን ነው ብለዋል። " በቀኑ ስለማይሰጥም ባስቀመጡት ቀን ተገልጋዩ እየተመላለሰ መከራ እየበላ…
#ፓስፖርት

ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው።

የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል።

ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ።

አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ አሠራር ዘርግቻለሁ ቢልም አሁንም በርካታ ተገልጋዮችን አገልግሎቱ ደጃፍ ላይ መመልከት አልቀረም።

ተገልጋዮች ዐሻራ ለመስጠት እና ፎቶ ለመነሳት በመ/ቤቱ መገኘት ግዴታቸው በመሆኑ ከተለያዩ አካባቢዎች መጥተው በወረፋው ምክንያት ላልተፈለገ እንግልት ይዳረጋሉ።

እንግልቱ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ከእንቅልፍ ተነስቶ ረዥም ሰልፍ ከመሰለፍ ይጀምራል።

በሌቦች መዘረፍም የሚያጋጥም ክስተት መሆኑን ተገልጋዮች በምሬት ይናገራሉ።

ለአላስፈላጊ እንግልት እና ወጪ ተዳርገናል የሚሉ ተገልጋዮች ሃሳባቸውን አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት በበይነ መረብ አማካኝነት ከተመዘገቡ ወራት እንዳለፋቸው ይገልጻሉ።

ተገልጋዮቹ አገልግሎቱ አካባቢ ወረፋ ለመያዝ ስንሞክር " እኔ ቅድሚያ ወረፋ ልያዝላችሁ ክፈሉኝ " በሚሉ ደላሎች እንዋከባለን ይላሉ።

እነሱ እንደሚሉት የመሥሪያ ቤቱን ሰልፍ አሰላፊዎች ወከባና ዱላ አልፎ ውስጥ መግባት መቻል መታደል ነው።

ተገልጋዮቹ በሌሊት ለመነሳት ሲሉ በአካባቢው ለአልጋ ኪራይ ከፍለው እንደሚያድሩና ለአላስፈላጊ ወጪም እንደሚዳረጉም ይገልጻሉ።

ሰልፉ ረዝሞ ወረፋ ሳይደርሳቸው ከቀረም ቅጣት እንደማይቀርላቸው ይናገራሉ።

በርካታ አገልግሎት ፈላጊ ሕዝብ በተገቢው መንገድ ከማስተናገድ ይልቅ በዱላ በመደብደብ ሥርዓት ለማስያዝ ሲሞከር ይታያል። ወደ መግቢያ በሩ ተጠግቶ መረጃ ማግኘት የማይታሰብ ነው።

የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ተስተካክሏል ይባል እንጂ አሁንም ችግሮቹ እንደነበሩ ናቸው ይላሉ ተገልጋዮች።

የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ሳይዘምን እንደዘመነ አድርጎ ማስተዋወቅም ፍጹም ተገቢነት እንደሌለውና ሕዝብ በለውጥ እንዳያምን እንደሚያደርግም ያስገነዝባሉ።

ሰሞኑን የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱን ለመመልከት በመ/ቤቱ የተገኙት የኢፕድ ጋዜጠኞች መረጃ ለመሰብሰብ ያደረጉት ሙከራ በፖሊሶች ክልከላ ተደርጎበታል።

የተቋሙ ኮሙኒኬሽን ዳሬክተር ወ/ሮ ማስተዋል ገዳ ምን ምላሽ ሰጡ ?

- ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ በሚመጡበት ወቅት በክብር መስተናገድ እንዳለባቸው እናውቃለን። ተገልጋዮችን በአግባቡ ባለማስተናገድ የዲሲፕሊን ችግር ያለባቸው ሠራተኞች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው።

- ተገልጋዮች ቅሬታ ሲኖራቸው ቅሬታ ለተቋሙ ማቅረብ አለባቸው።

- አዲስ ፓስፖርት ፈልገው በድረ ገጽ ሲያመለክቱ ፎቶግራፍ የሚነሱበትን እና ዐሻራ የሚሰጡበትን ቀንና ሰዓት የሚያሳውቅ በመሆኑ ተገልጋዮች በሰዓቱ ብቻ ቢመጡ ሰልፉ ሊቀንስ ይችላል። የተቀጠሩ ተገልጋዮች ሳይስተናገዱ አይቀሩም።

- በአካባቢው መጨናነቅ የሚፈጠረው ቀጠሮ ባላቸው ተገልጋዮች ብቻ ሳይሆን " ፓስፖርት ዘግይቶብናል "  ብለው ለመጠየቅ በሚመጡ ተገልጋዮች ነው። አንድ ጉዳይ ለመጨረስ ከአንድ በላይ ሰው ስለሚመጣ ነው።

- የሌሊት ሰልፉ ከአገልግሎቱ እውቅና ውጪ ነው። ለሰልፉ ሰዓት የመገደቡን ጉዳይ በቀጣይ በጋራ የሚታይ ነገር ነው።

- ተገልጋዮች ለአስቸኳይ ፓስፖርት በሕገ ወጥ ደላሎች በኩል ለማስጨረስ ከመሞከር ይልቅ እራሳቸው በጥቂት ቀናት መጨረስ ይችላሉ።

ያንብቡ https://telegra.ph/EPA-03-04

ይህ መረጃ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው።

ፎቶ፦ Tikvah Family

@tikvahethiopia