TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ እንዲሁም የመከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ዓድዋ ሲደርሱ የተደረገላቸው አቀባበል።

#ኢትዮጵያ #ዓድዋ128

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በታሪካዊቷ ዓድዋ እየተካሄደ ባለው የዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ባንዴራ የመስቀል ስነ-ሰርዓት ተካሂዷል። የኢትዮጵያ፣ የትግራይ ክልል ፣ የአፍሪካ ህብረት ባንዴራ በፕረዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ እንዲሁም የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ተወካይ በሆኑት ሜጀር ጀነራል ስቴፈን ራድያ ተሰቅሏል። የባንዲራ መስቀል ስነስርዓቱ በኢትዮጵያ 🇪🇹 ህዝብ ብሄራዊ መዝሙር ታጅቦ…
#ዓድዋ128

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ በታሪካዊቷ ዓድዋ እየተካሄደ ባለው ስነስርዓት ላይ ንግግር አድርገዋል።

" ድሉ በድምቀት እንድናከብር ያበቁን አባት አያቶቻችን ስንዘክር የአሁኑ ትውልድ አገርና ህዝብ የሚያሳድግ አንድነት ልማት ስር እንዲሰድ የሚያስችል እንቅስቃሴ በማድረግ መሆን ይገባዋል " ብለዋል።

ድሉ የመላው ኢትዮጵያውን ድል መሆኑን ያስታወሱት ጄነራል ታደሰ ፤ " የአሁኑ ትውልድ የአባት አያቶቹ ክብር በማስቀጠል ለአገርና ህዝብ አንድነት መስራት ይጠበቅበታል " ብለዋል።

ምክትል ፕሬዜዳንቱ ፤ " የ128ኛው የዓድዋ ድል መታሰብያ ስናከብር ደም አፋሳሹ የትግራይ ጦርነት ለማስቆም የተደረገው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተከትሎ ፦
የትግራይ ወሰን አለመከበሩ
ከቄያቸው የተፈናቀሉ እንዲመለሱ አለመደረጉ መዘንጋት አይገባም " ሲሉ ገልጸዋል።

" የፌደራል መንግስት የገባውን ውል እንዲፈፅም አሁንም ጥሪያችን እናቀርባለን " ሲሉ ሌ/ ጀነራል ታደሰ ወረደ መናገራቸውም በዓድዋ የሚገኘው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል መረጃውን አድርሶናል።

#AdwaTikvahFamily

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዓድዋ128 የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ በታሪካዊቷ ዓድዋ እየተካሄደ ባለው ስነስርዓት ላይ ንግግር አድርገዋል። " ድሉ በድምቀት እንድናከብር ያበቁን አባት አያቶቻችን ስንዘክር የአሁኑ ትውልድ አገርና ህዝብ የሚያሳድግ አንድነት ልማት ስር እንዲሰድ የሚያስችል እንቅስቃሴ በማድረግ መሆን ይገባዋል " ብለዋል። ድሉ የመላው ኢትዮጵያውን ድል መሆኑን ያስታወሱት…
" ደማቁ የዓድዋ የድል መታሰብያ በዓልን በእርስ በርስ ግጭት ማቆሸሽ አይገባም " - ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መልእክት አስተለልፈዋል።

ከ3 ዓመት ተኩል በኃላ በትግራይ ታሪካዊትዋ የዓድዋ ከተማ በመገኘት በዓሉን ለማክበር በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል።

ፕረዚደንትዋ #እንባ_እየተናነቃቸው ያለፈውን አስከፊ ጦርነት በማስታወስ ፣ ተፈናቃዮች ያሉበትን አስከፊ ሁኔታ በማንሳት ተናገረዋል።

" አሁን ከገባንበት እንድንወጣ ፈጣሪ ይርዳን ፤ በሃይማኖትና በዘር መከፋፈል ይብቃን " ብለዋል።

የበዓሉ ታዳሚ ህዝብ በፕረዚደንትዋ ስሜታዊ ንግግር እጅግ ስሜቱ መነካቱ ከፊቱ ማንበብ እንደቻለ በስፍራው የነበረው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነግሮናል።

" የችግሮቻችን ምንጭ እውቀን ከስሩ ለማድረቅ መስራት አለብን " ያሉት ፕሬዜዳንቷ ፤ " ከእርስ በርስ ጦርነት ጊዚያዊ አሸናፊ እንጂ ዘላቂ አሸናፊ የለም ፤ ስለሆነም ከዚሁ በመቆጠብ በአንድነት ቆመን አገራችን ከውጭ ወራሪ መታደግ ይገባናል " ብለዋል።

" ኢትዮጵያውያን የዓድዋ የድል ዘላቂ እንዲሆን ከተፈለገ ወንድም ወንድሙ ላይ ጦር ከማንሳት መቆጠብ አለብን " ሲሉ አሳስበዋል።

" የሃሳብ ልዩነታችን ከጠብመንጃ በመለስ በጠረጴዛ ውይይት የመፍታት ልማድ ሳይሆን ባህል መፍጠር አለብን። ያለፈው ይብቃ ከስህቶቻችን እንማር " ብለዋል።

በሌሎች ክልሎች የሚታየው ገጭትም በሰላም እንዲፈታ መስራትና መተባበር አለበን ሲሉ ተናግረዋል።

ደማቁን የዓድዋ የድል መታሰብያ በዓል በአርስ በርስ ግጭት ማቆሸሽ አይገባም ማለታቸውንም በስፍራው የሚገኘው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ገልጾልናል።

#TikvahFamilyAdawa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ደማቁ የዓድዋ የድል መታሰብያ በዓልን በእርስ በርስ ግጭት ማቆሸሽ አይገባም " - ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መልእክት አስተለልፈዋል። ከ3 ዓመት ተኩል በኃላ በትግራይ ታሪካዊትዋ የዓድዋ ከተማ በመገኘት በዓሉን ለማክበር በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል። ፕረዚደንትዋ #እንባ_እየተናነቃቸው ያለፈውን አስከፊ ጦርነት በማስታወስ ፣ ተፈናቃዮች ያሉበትን አስከፊ ሁኔታ…
#ትግራይ

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ 😢

" ጠላት ሊወረን ሲመጣ የኢትዮጵያ ህዝብ በዘር ፣ በሃይማኖት ፣ በፆታ ሳይለያይ የመሪውን ዳግማዊ አጼ ሚኒሊክን ጥሪ በመቀበል ተሰባስቦ በመዝመት በነዚህ ተራሮች እና ኮረብታዎች ታሪክ እንዳልሰራ ሁሉ ለራሱ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ፤ ለአፍሪካ አህጉራችን እንዲሁም ለመላው የተጨቆነ ህዝብ ተስፋ የሰጠ ሳለ በዚህች መሬት፦
- ወንድም በወንድሙ ላይ ቃታ የሳበበት የተጋደለበት
- ንፁሃን የተገደሉበት
- ብዙዎች የተሰደዱበት
- በርካቶች በገዛ ሀገራቸው የተንከራተቱበት፣ የተፈናቀሉበት
- ንብረት የወደመበት
- #ሴቶች_የተደፈሩበት ሁኔታ ታሪክ ጅብዱ በተሰራበት ምድር እንዲያይ ያደረግነው። እነዚህ ተራራዎች ለዚህም እማኝ እንዲሆኑ ያደረግነው።

እነዚህ ተራሮች መናገር ቢችሉ እንዲነግሩን የምንፈልገው ግን የህዝባችንን ጀግንነት፣ ታሪክ ሰሪነት፣ አንድነት ነው፤ ምስክሮቻችን ናቸው።

በትግራይ ጦርነቱ እንደጀመረ ሰሞን መጥቼ ነበር። ከጦርነቱ ሁለት ወር በፊት እዚህ ነበርኩ። የጦርነት ደህና ገፅታ የለውም እጅግ አስከፊውን ግን አላየሁም ብዬ ነው የማስበው። "

#TikvahFamilyAdawa

@tikvahethiopia
#Ethiopia 🇪🇹

ኢትዮጵያ በግላስኮ በ2024 የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና እየተሳተፈች ትገኛለች።

ከደቂቃዎች በላይ የፍፃሜ ውድድር ይካሄዳል።

ኢትዮጵያ የምትሳተፍባቸው ውድድሮች የትኞቹ ናቸው ?

🇪🇹 ምሽት 5:15 ➡️ 3000ሜ ሴቶች ፍፃሜ (ሂሩት መሸሻ ፣ ለምለም ሀይሉ እና ጉዳፍ ፀጋይ)

🇪🇹 ምሽት 5:40 ➡️ 3000ሜ ወንዶች ፍፃሜ (ጌትነት ዋለ እና ሰለሞን ባረጋ)

ውድድሩን በምን መመልከት ይቻላል ?

በDSTV " ቻናል 239 " ወይም ልዩ ቻናል 2 ላይ መከታተል ይቻላል።

ቲክቫህ ስፖርት👇
https://yangx.top/+VvwzStMNcNHmhK0x 
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ❤️ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአትሌት ጉዳፍ ፀጋይ አማካኝነት በግላስኮ የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች። ጉዳፍ ውድድሯን 2ኛ ሆና አጠናቃለች። Via @tikvahethsport ፎቶ ፦ ፋይል @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

ሰለሞን ባረጋ ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ አምጥቷል።

በግላስኮ ዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በወንዶች 3 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያ በአትሌት ሰለሞን ባረጋ አማካኝነት የነሃስ ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች።

ጌትነት ዋለ 4ኛ ወጥቷል።

ኢትዮጵያ በዚህ ርቀት በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ላይ የወርቅ ሜዳሊያ ሳታሸንፍ ስትቀር ከ3 ተከታታይ ውድድሮች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

ሰለሞን ባረጋ ከሁለት ዓመታት በፊት በዚሁ ውድድር ሲያሸንፍ ዮሚፍ ቀጀልጃ በ2016 እና 2018 የዚህ ውድድር አሸናፊ ነበር።

Via @tikvahethsport

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ 😢 ፦ " ጠላት ሊወረን ሲመጣ የኢትዮጵያ ህዝብ በዘር ፣ በሃይማኖት ፣ በፆታ ሳይለያይ የመሪውን ዳግማዊ አጼ ሚኒሊክን ጥሪ በመቀበል ተሰባስቦ በመዝመት በነዚህ ተራሮች እና ኮረብታዎች ታሪክ እንዳልሰራ ሁሉ ለራሱ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ፤ ለአፍሪካ አህጉራችን እንዲሁም ለመላው የተጨቆነ ህዝብ ተስፋ የሰጠ ሳለ በዚህች መሬት፦ - ወንድም በወንድሙ ላይ ቃታ የሳበበት የተጋደለበት…
#ትግራይ

" ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን 2 ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ ! " - ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በታሪካዊቷ ዓድዋ ከተማ በነበረው የዓድዋ ድል በዓል  ላይ እምባ እየተናነቃቸው 😭 ንግግር አድርገው ነበር።

እሳቸው በእንባ ንግግር ሲያደርጉ የበዓሉ ታዳሚ ህዝብ ከፍተኛ የሀዘን ስሜቱ ከፊቱ ይነበብ እንደነበር በስፍራው የነበረው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ምን አሉ ?

" ዛሬ ወደ ትግራይ ስመለስ በህሊናዬ የሚመጡብኝ ብዙ ትዝታዎች አሉብኝ።

ይቅርታ አድርጉልኝና አጋጣሚውን ተጠቅሜ ማንሳት እፈልጋለሁ።

በትምህርት ቤት ውስጥ ተጠልለው ከነበሩ ወገኖች መካከል አንዷ ፈንጠር ብላ የተቀመጠች አንዲት ሴት ለማነጋገር ሞክሬ ነበር።

በተፈናቃዮች ካምፕ ጉብኝት ልብን የሚሰብር  ነው። ከቤት ንብረታቸው ወጥተው ፣ ክብራቸውን አጥተው ቁጭ ብለው ጉብኝት .. እኛ ደግሞ እንመጣለን ልናያቸው።

ታዲያ ያችን ሴት ጠጋ ብዬ ሳነጋግራት፤ በጥሩ አልመለሰችልኝም። ጥቂት ያመጣሁትን እቃ እንድታከፋፍልልኝ ነበር ልጠይቃት የነበረው ' ያንቺን እቃ አልፈልግም ' አለችኝ።

በሆስፒታል እና በመጠለያ ጣቢያቸው ሄጄ ያየዋቸዋን ሴቶች በእጅጉ አስባቸዋለሁ። እቺን ሴትዮ ለምንድነው የምትመልሽልኝ ስላት ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን ሁለት ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ መልስ የለኝም ፤ አይመልስም ብቻ ነው ያልኳት።

ጦርነቱ ተዛምቶ በአፋር ክልል ሰመራ ሆስፒታል ህክምና ላይ የነበሩ የተማረኩ የህወሓት ታጋይ ሴቶችን አግኝቻቸዋለሁ ሳናግራቸው ያሉኝ ከልቤ አይጠፋም ፤ ቦታቸው እዛ አልነበራም ትምህርት ቤት ነው።

ያሉኝ ' እኛ መመለስ የምንፈልገው ወደ ትምህርት ቤት ነው ' ይሄንን ወግቼ ያንን አሸንፌ የሚል ዓላማ አልነበራቸውም። በክፍላቸው ግርግዳ ላይ የፃፉት የለጠፉት የአፋር ህዝብ እንዴት ደግ እንደሆነ ነው። ኢትዮጵያዊ ለኢትዮጵያዊ እንዴት እንደሚረዳዳ ነው።

ሌሎችም አሉ ብዙ እርጉዝ ሆነው ሶስት ልጅ ወልደው ሲንከራተቱ የነበሩ ... ለማንኛውም ብዙ መንከራተት ነበር።

ዛሬ እዚህ ቆሜ የትግራይ እናቶች ያሳለፉትን #ሰቆቃ በእውነቱ እረዳለሁ ለማለት ነው ይሄን ሁሉ የምናገረው። እግዚአብሔር ብርታቱን ይስጥዎ !!

ዞሮ ዞሮ የማንኛውም ግጭት መጨረሻው ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ የሰላም ስምምነት መፈረሙ አይቀርምና ይህ ሳይሆን ተጨራርሰን ተጨካክነን ፣ ዘርና ሃይማኖት መለያያ አድርገን ሃይማኖቶችን ከፋፍለን ሳይሆን በቅድሚያ መከላከል እንዳለብን መገንዘብ አለብን።

የዓድዋ ባለቤቶች እንዳልሆንን ገፅታችንን አጉድፈን አበላሽተናል። "

#TikvahFamilyAdawa

@tikvahethiopia
ማንችስተር ሲቲ ወይስ ማንችስተር ዩናይትድ (#ይገምቱ!) https://vm.tiktok.com/ZMMNQqowU/

ለ10 የቲክቶክ ተከታዮቻችንን የሚያሽልም

1. ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የቲክቶክ ቻናል ይከተሉ (#FOLLOW)።
2. ግምትዎን ብሃሳብ መስጫው (#COMMENT) ላይ ያስቀምጡ::
3. ቪዲዮውን ላይክ (#LIKE) እንዲሁም ሼር (#SHARE) ያድርጉ። https://vm.tiktok.com/ZMMNQqowU/
4. ውጤት ማስተካከል እና ከላይ የተጠቀሱትን ህግጋቶች የማያከብሩ ከውድድሩ #ውጭ ይሆናሉ።
5. ክ 10 በላይ ትክክለኛ መላሾች የሚለዩት #በዕጣ ይሆናል።

መልካም ዕድል!

#GlobalBankEthiopia #OurSharedSuccess #BankInEthiopia #GBE #MCMU #EPL #MUTD #MCITY