TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ታግተዋል!

45 #ኢትዮጵያውያን#ኤርትራውያን እና #ሶማሊያውያን ስደተኞች በሊቢያ ናስማ በተባለ ቦታ በሕገ-ወጥ የሰው አዘዋዋሪ ታግተው እንደሚገኙ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል። ከታገቱ አንዱ «በተዘጋ ቤት ውስጥ ነው ያለንው። በጣም መጥፎ ሁኔታ ላይ ነው ያለንው» ብሏል። ስደተኞቹ እንደሚሉት የሜድትራኒያን ባሕርን በማቋረጥ አውሮፓ ለመግባት ጉዞ የጀመሩት በአንድ ኤርትራዊ የሰው አሸጋጋሪ አማካኝነት ነበር።

ኤርትራዊው ለሊቢያዊ አስረክቧቸው መጥፋቱንም ይገልፃሉ፤ ከ45 ስደተኞች 7ቱ ሴቶች 38 ወንዶች ናቸው። አንዲት ኢትዮጵያዊት «ባሕር ልሻገር ብዬ ነው የመጣሁት። 6100 ዶላር ክፈይ ተብዬ ከፍያለሁ። ከዚያ በኋላ ስልኩን አጥፍቶ ለሊቢያዊ ትቶን ሔደ። ሊቢያዊው ደግሞ 3500 ዶላር ጨምሩና ከዚህ ቤት ላስወጣችሁ ብሎናል፤ አሁን አቅሙም ያለው ሰው የለም» ብላለች።

Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia