#ADWA129
129ኛዉ የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል " በሚል መሪ ኃሳብ እንደሚከበር የሀገር መከላከያ ሰራዊት አስታውቋል።
የመከላከያ ስነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜ/ጀነራል እንዳልካቸው ወ/ኪዳን ፥ " በዓሉን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ኮሚቴ ተቋቁሞ ዝግጅት እየተደረገ ነው " ብለዋል።
ከበዓሉ ቀደም ብሎም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና ሚሲዮኖች ጭምር እንደሚከበር ጠቁመዋል።
" ዓድዋ የጋራ ድል፣ የአንድነት፣ የአላማ ፅናት እንዲሁም የአሸናፊነት ምሳሌ በመሆኑ የአባቶችን አርበኝነት በመያዝ ዘመኑ የሚጠብቅብንን ኃላፊነት መወጣት አለብን " ብለዋል።
#FDREDefenseForce #FMC
@tikvahethiopia
129ኛዉ የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል " በሚል መሪ ኃሳብ እንደሚከበር የሀገር መከላከያ ሰራዊት አስታውቋል።
የመከላከያ ስነ ልቦና ግንባታ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜ/ጀነራል እንዳልካቸው ወ/ኪዳን ፥ " በዓሉን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ኮሚቴ ተቋቁሞ ዝግጅት እየተደረገ ነው " ብለዋል።
ከበዓሉ ቀደም ብሎም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም በኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና ሚሲዮኖች ጭምር እንደሚከበር ጠቁመዋል።
" ዓድዋ የጋራ ድል፣ የአንድነት፣ የአላማ ፅናት እንዲሁም የአሸናፊነት ምሳሌ በመሆኑ የአባቶችን አርበኝነት በመያዝ ዘመኑ የሚጠብቅብንን ኃላፊነት መወጣት አለብን " ብለዋል።
#FDREDefenseForce #FMC
@tikvahethiopia
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙበትን ዓላማ እንዲያስፈፅሙ አሳሰበ።
የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፥ * የኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙበትን ዋና ዓላማ መዘንጋት የለባቸውም " ሲሉ አሳሰቡ።
ሚኒስትሩ ይህን ማሳሰኒያ የሰጡት ዛሬ ከወለጋ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ነው።
" ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ችግር ፈቺ ሥራዎችን መሥራት ይጠበቅባቸዋል " ያሉት ፕ/ር ብርሃኑ ፥ ተቋማቱ በአካባቢ ሳይታጠሩ ለተመሠረቱበት ዓላማ መኖር አለባቸውም ብለዋል፡፡
- የሙስና መንሰራፋት፣
- ግብረ-ገብነት ማጣት
- ዕውቀት የመቀያየር ባሕል በምሁራን ዘንድ መቀዛቀዙን አንስተዋል
እነዚህ ችግሮች ከፍተኛ የትምሕርት ተቋማት የዕውቀት ማዕከል እንዳይሆኑ አድርገዋል ብለዋል።
" ሀገራችን በዘርፈ-ብዙ ችግሮች ውስጥ በመሆኗ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን የመፍትሔ ሐሳብ ማመንጨት ይጠበቅባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ዩኒቨርሲቲዎች የዕውቀት እና የእውነት ማዕከል እንዲሆኑየሪፎርም ሥራ እየተከናወነ ነው " ሲሉም አመልክተዋል።
ተቋማቱ፤ ጥራት ባለው ትምሕርት ትውልድን መቅረጽ እና የማሕበረሰቡን ችግሮች መቅረፍ የሚያስችሉ ምርምሮችን በማድረግ ሀገራዊ ግዴታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም በአጽንኦት አሳስበዋል።
Credit - #FMC
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙበትን ዓላማ እንዲያስፈፅሙ አሳሰበ።
የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፥ * የኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙበትን ዋና ዓላማ መዘንጋት የለባቸውም " ሲሉ አሳሰቡ።
ሚኒስትሩ ይህን ማሳሰኒያ የሰጡት ዛሬ ከወለጋ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ነው።
" ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ችግር ፈቺ ሥራዎችን መሥራት ይጠበቅባቸዋል " ያሉት ፕ/ር ብርሃኑ ፥ ተቋማቱ በአካባቢ ሳይታጠሩ ለተመሠረቱበት ዓላማ መኖር አለባቸውም ብለዋል፡፡
- የሙስና መንሰራፋት፣
- ግብረ-ገብነት ማጣት
- ዕውቀት የመቀያየር ባሕል በምሁራን ዘንድ መቀዛቀዙን አንስተዋል
እነዚህ ችግሮች ከፍተኛ የትምሕርት ተቋማት የዕውቀት ማዕከል እንዳይሆኑ አድርገዋል ብለዋል።
" ሀገራችን በዘርፈ-ብዙ ችግሮች ውስጥ በመሆኗ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን የመፍትሔ ሐሳብ ማመንጨት ይጠበቅባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ዩኒቨርሲቲዎች የዕውቀት እና የእውነት ማዕከል እንዲሆኑየሪፎርም ሥራ እየተከናወነ ነው " ሲሉም አመልክተዋል።
ተቋማቱ፤ ጥራት ባለው ትምሕርት ትውልድን መቅረጽ እና የማሕበረሰቡን ችግሮች መቅረፍ የሚያስችሉ ምርምሮችን በማድረግ ሀገራዊ ግዴታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም በአጽንኦት አሳስበዋል።
Credit - #FMC
@tikvahethiopia