TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#UAE

ጠ/ሚ መሀመድ ሁሴን ሮብሌ ዩኤኢ ይገኛሉ።

የሶማሊያ ጠ/ሚር መሀመድ ሁሴን ሮበል በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የስራ ጉብኝት ላይ እንደሚገኙ አል ዓይን ኒውስ ዘግቧል።

ጠ/ሚ ሮብሌ በትናንትናው ዕለት ወደ አቡዳቢ ያቀኑ ሲሆን ከአገሪቱ አመራሮች ጋር በመወያየት ላይ መሆናቸውን ዘገባው ይገልፃል።

ባለፉት ቀናት የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ፣ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድን እንዲሁም ትላንት የእስራኤል ፕሬዜዳንት አይዛክ ሄርዞግን ተቀብላ አስተናግዳለች።

ከየሀገራቱ መሪዎች ጋርም በተለያዩ ጉዳዮች መክራለች።

ፎቶ : #SomaliPM

@tikvahethiopia