#ሀገራዊምክክር #ሀገራዊመግባባት
በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግር ለሥራው እንቅፋት እንደሆኑበት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኮሚሽኑ አንጀዳ ቀረፃ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ተመስገን አብዲሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፦
- የጸጥታ ችግር በአንዳንድ ቦታዎች በተለይ በአማራ ክልል አሁን፣ በኦሮሚያ ክልል ቀድሞና አሁንም አንዳንድ ቦታዎች መኖሩ እንደ አንድ እንቅፋት የሚታይ ነው።
- ኮቦታ ቦታ ተዘዋውሮ ተሳታፊዎችን ከቦታ ቦታ ማምጣት በጣም አዳጋች ነው የሚሆነው የጸጥታ ችግር ባለበት።
- የጸጥታ ችግር ባለበት አገራዊ ምክክር እንቅፋት ያጋጥመዋል። ስለዚህ ቅድሚያ እንግዲህ እነዚህ የጸጥታ ችግሮችን እንዴት እንፈታለን ? እንዴት መፈታት አለባቸው ? የሚሉትን ጭምር ቁጭ ብለን እየተወያዬን ኮሚሽኑ የመፍትሄ አቅጣጫዎችንም እያስቀመጠ በዚያ ልክ እየሄደ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ኮሚሽኑ ላይ ስለሚነሳው በተለይም የገለልተኝነት ጥያቄና ሌሎች ቅሬታዎች ለኮሚሽን የቅሬታ አያያዝ አስተባባሪና የኦሮሚያ ክልል ተሳታፊ ልየታ ቡድን መሪ አቶ ብዙነህ አሰፋ ጥያቄ አቅርቦ ነበር።
ምላሻቸውም ፦
* ' ኮሚሽኑ ነፃ አካል አይደለም፣ የመንግሥት ጥገኛ ነው ' የሚል አስተሳሰብ በተወሰኑ አካላት ዘንድ እንዳለ እንገነዘባለን። ያነን የሚያራምዱት በብዛት የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ናቸው።
* 'ለዚህ ሀሳብ መነሻ የሆናቸው ነገር ' ኮሚሽኑ ሲመሠረት በበቂ አልተሳተፍንም እኛ ' ከሚል የሚመነጭ ይመስለኛል። ይሄ ቅሬታ የተወሰኑ እውነታዎች ሊኖሩት ይችላሉ። በአብዛኛው ግን በጥላቻ እና ጥርጣሬ ላይ የተመሠረተ ነው።
* እውነት ነው። ኮሚሽኑ ሲቋቋም ሰፊ ሚና የተጫወተው መንግሥት ነው ግን የኮሚሽን መሪዎች የተመረጡበት ሂደት ደግሞ ከሞላ ጎደል ህዝባዊ እና ገለልተኛ ነው የነበረው።
* የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሲቋቋም በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀሳብ ልዩነት ማደራደር የተቋቋመ ተቋም አይደለም። በኢትዮጵያ ውስጥ በህዝብ እና በህዝብ፣ በህዝብ እና በመንግሥት፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሀገርን ደህንነት ስጋት ላይ ሊጥሉ የሚችሉ መሠረታዊ ልዩነቶች መንስኤ መለየትና ልዩነቶቹን ለመፈታት ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግበት ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የተቋቋመ ኮሚሽን ነው።
ያንብቡ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-16
@tikvahethiopia
በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግር ለሥራው እንቅፋት እንደሆኑበት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኮሚሽኑ አንጀዳ ቀረፃ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ተመስገን አብዲሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፦
- የጸጥታ ችግር በአንዳንድ ቦታዎች በተለይ በአማራ ክልል አሁን፣ በኦሮሚያ ክልል ቀድሞና አሁንም አንዳንድ ቦታዎች መኖሩ እንደ አንድ እንቅፋት የሚታይ ነው።
- ኮቦታ ቦታ ተዘዋውሮ ተሳታፊዎችን ከቦታ ቦታ ማምጣት በጣም አዳጋች ነው የሚሆነው የጸጥታ ችግር ባለበት።
- የጸጥታ ችግር ባለበት አገራዊ ምክክር እንቅፋት ያጋጥመዋል። ስለዚህ ቅድሚያ እንግዲህ እነዚህ የጸጥታ ችግሮችን እንዴት እንፈታለን ? እንዴት መፈታት አለባቸው ? የሚሉትን ጭምር ቁጭ ብለን እየተወያዬን ኮሚሽኑ የመፍትሄ አቅጣጫዎችንም እያስቀመጠ በዚያ ልክ እየሄደ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ኮሚሽኑ ላይ ስለሚነሳው በተለይም የገለልተኝነት ጥያቄና ሌሎች ቅሬታዎች ለኮሚሽን የቅሬታ አያያዝ አስተባባሪና የኦሮሚያ ክልል ተሳታፊ ልየታ ቡድን መሪ አቶ ብዙነህ አሰፋ ጥያቄ አቅርቦ ነበር።
ምላሻቸውም ፦
* ' ኮሚሽኑ ነፃ አካል አይደለም፣ የመንግሥት ጥገኛ ነው ' የሚል አስተሳሰብ በተወሰኑ አካላት ዘንድ እንዳለ እንገነዘባለን። ያነን የሚያራምዱት በብዛት የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ናቸው።
* 'ለዚህ ሀሳብ መነሻ የሆናቸው ነገር ' ኮሚሽኑ ሲመሠረት በበቂ አልተሳተፍንም እኛ ' ከሚል የሚመነጭ ይመስለኛል። ይሄ ቅሬታ የተወሰኑ እውነታዎች ሊኖሩት ይችላሉ። በአብዛኛው ግን በጥላቻ እና ጥርጣሬ ላይ የተመሠረተ ነው።
* እውነት ነው። ኮሚሽኑ ሲቋቋም ሰፊ ሚና የተጫወተው መንግሥት ነው ግን የኮሚሽን መሪዎች የተመረጡበት ሂደት ደግሞ ከሞላ ጎደል ህዝባዊ እና ገለልተኛ ነው የነበረው።
* የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሲቋቋም በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀሳብ ልዩነት ማደራደር የተቋቋመ ተቋም አይደለም። በኢትዮጵያ ውስጥ በህዝብ እና በህዝብ፣ በህዝብ እና በመንግሥት፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሀገርን ደህንነት ስጋት ላይ ሊጥሉ የሚችሉ መሠረታዊ ልዩነቶች መንስኤ መለየትና ልዩነቶቹን ለመፈታት ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግበት ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የተቋቋመ ኮሚሽን ነው።
ያንብቡ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-16
@tikvahethiopia