TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#Tigray

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ በክልሉ ከ2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለረሃብ #መጋለጡን አሳወቀ።

እስከ አሁን 25 ህፃናት የሚገኙባቸው 400 ሰዎች በራብ ምክንያት ሞተዋልም ብሏል። 

በክልሉ ያጋጠመው የድርቅ አደጋ ለመከላከል ያለመ 22 አባላት ያሉት ከተለያዩ የህብረተሰብ ልፍሎች የተውጣጣ " አፋጣኝ ምላሽ ለትግራይ " የተሰኘ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ተሰምቷል።

የ " አፈጣኝ ምላሽ ለትግራይ " ግብረ ሃይል ሰብሳቢ የሆኑት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ሲሆኑ  ዛሬ ለጋዜጠኞች መገለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ በአሁኑ ሰአት ለረሃብ አደጋ የተጋለጠው ከ2 ሚሊዮን ትግራዋይ ህይወት ለመታደግ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኝ የክልሉ ተወላጅና ወዳጅ እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል።

የ " አፈጣኝ ምላሽ ለትግራይ " ግብረ ሃይል ድጋፍ የሚያግዙ ግለሰቦችና ደርጅቶች የሚገለገሉባቸው ሶስት የባንክ የሂሳብ ቁጥሮች የከፈተ ሲሆን ቁጥሮቹ ፦

* አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ 👉00112180095-49

* ወጋገን ባንክ 👉 1001077411101

* የኢትዮጵያ  ንግድ ባንክ 👉 1000592420809 መሆናቸውን የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
                                    
@tikvahethiopia