TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ጀርመን #ባለሞያ ሰራተኞችን ልትቀበል ነው።

የጀርመን ምክር ቤት በተለያዩ ሙያ የሰለጠኑ ከአዉሮፓ ህብረት (EU) ሃገራት ዉጭ የሆኑ ሰራተኞች ወደ ጀርመን እንዲገቡ የሚፈቅደዉን አዲስ ደንብ ዛሬ ማፅደቁ ተነግሯል።

አዲሱ ደንብ ባለሙያዎች፣ የጀርመንኛና የእንግሊዝኛ ቋንቋ እስከቻሉ ድረስ ያለ ብዙ ዉጣ ዉረድ ወደ ጀርመን እንዲገቡና ጀርመን ዉስጥ እንዲሰሩ የሚፈቅድ ነው ተብሏል።

ይህ ደንብ በጀርመን ለሚገኙ በርካታ ስደተኞች እድል የሚሰጥ ሴሆን በካናዳ ደንብና አሰራር መሠረት የተቀረፀ እንደሆነ ተነግሯል።

ደንቡ በተለይ እንደ መስተንግዶ፣ ጤና፣ ግንባታና ቴክኖሎጂን በመሳሰሉ መስኮች ጀርመን ያለባትን የባለሙያ እጥረት ለማቃለል ይረዳል ተብሏል።

መረጃው የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia