TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ግንቦት 20, 1983 ዓ/ም👆

ከላይ ባለው ፎቶ የሕወሓት ሊቀመንበር #መለስ_ዜናዊ እና የደኅንነቱ ሹም #ክንፈ_ገብረ_መድኅን ወደ ግዮን ሆቴል ሲገቡ ይታያሉ።

የሚሊተሪ ለብሶ የሚታየው የቀድሞው ጦር (ደርግ) መኮንን የነበረው ኮሎኔል አስራት ነው። ኮሎኔል አስራት በሕወሓት ከተማረከ በኋላ ከኢህአዴግ ጋር ተሰልፎ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት መምሪያ ሀላፊነት ደረጃ ድረስ ሲሰራ የነበረ፤ በኋላም የግርማዊ ዐፄ ኃይለሥላሴ አስከሬን ከኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ጽ/ቤት ለማውጣት የተዋቀረውን ግብረ ኃይል ያስተባበረ ነው።

አብዮት ልጇን ትበላለችና ኮሎኔል አስራት የቀይ ሽብር ተዋናይ ነበር ተብሎ ወደ ወህኒ ቤት የወረደ ሲሆን፤ በወህኒ ቤትም እያለ "በህመም" ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት የተለየ መሆኑ ታውቋል።

ግንቦት 20 ዛሬ 28ኛ አመቱ ሲታሰብ በፎቶው ላይ የምናያቸው ሶስቱም አመራሮች በሕይወት የሉም።

Via #PetrosAshenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia