TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#እግድ

" የማህበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ቴሌቪዥን ጣቢያ " በመንግስት #በጊዜያዊነት ታገደ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዛሬ እሁድ በፃፈው ደብዳቤ " ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ " ን በጊዜያዊነት እንዳገደ አሳውቋል።

ባለስልጣን መ/ቤቱ ፤ ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ዛሬ በግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም " ሰበር ዜና " በሚል ባሰራጨው መግለጫ ከሐይማኖት መገናኛ ብዙኃን ሚና ውጪ በሆነ አግባብ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያካሄደውን ስብሰባ የሚያውክና ህዝብን ለግጭት የሚያነሳሳ መልዕክት ማሰራጨቱን አረጋግጫለሁ ብሏል።

ይህም የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን የሚተላለፍና በሀገር ሁለንተናዊ ሰላም ላይ ጉዳት ሊያስከትል የሚችል እንደሆነም ገልጿል።

ከጉዳዩ አጣዳፊነትና ሊያስከትለው ከሚችለው ጉዳት አንፃር በቀጣይ በባለሥልጣኑ ቦርድ ታይቶ ዘላቂ ውሳኔ እስከሚሰጥበት ጊዜ ድረስ የጣቢያው ፈቃድ በጊዜያዊነት የታገደ መሆኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡

ማህበረ ቅዱሳ ቴሌቪዥን ጣቢያ በመገናኛ መረቡ " ሰበር ዜና " በሚል ያሰራጨው " ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ችግርን ለመቅረፍ በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ " በኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደት ላይ አወጥቶታል ያለውን መግለጫ ነው።

https://www.facebook.com/100069179198602/posts/pfbid0kKRZfaiNWQpCJpyUSuuNWtyXNHahgy1DZH4DUMudijNXNbcu8N7G1CGUP73Y6e9dl/?app=fbl

የግንቦት 2015 ዓ/ም ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከቀናቶች በፊት ተጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን በየዕለቱ በቤተክርስቲያኗ ቴሌቪዥን ዕለታዊ መረጃዎች/ውሳኔዎች ሲተላለፉ ነበር ፤  እስከ ዛሬ ድረስ ጉባኤው መቋጫ አግንኝቶ #በቅዱስ_ሲኖዶስ በኩል ለምዕመኑ የተሰጠ አጠቃላይ መግለጫ የለም።

@tikvahethiopia