#update ሜቴክ⬇️
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን የከተማውን የትራንስፖርት እጥረት ለማቃለል ለብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ትዕዛዝ ከሰጣቸው 850 አውቶብሶች 700ዎቹን እስካሁን እንዳልተረከበ ተሰምቷል። ለአውቶብሶቹ 3.4 ቢሊዮን ብር #ተከፍሏል ነው የተባለው፡፡
የባለስልጣን መ/ቤቱ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ ወ/ሮ እፀገነት አበበ ዛሬ ለሸገር FM 102.1 ሲናገሩ፣ ከሜቴክ ጋር የአውቶብሶቹን ስራ ውል የገባነው በሰኔ ወር 2009 ዓ/ም ሲሆን አውቶብሶቹን መረከብ የነበረብን ሰኔ 2010 ነበር ብለዋል፡፡
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አውቶብሶቹን በቃሌ መሰረት ያላስረከብኩት በውጪ ምንዛሬ ችግር ነው ብሎናል ያሉት ወ/ሮ እፀገነት ከዚህ ወር ጀምሮ ግን ቀስ በቀስ ቀሪ 700 አውቶብሶቹን ሊያስረክበን ቃል ገብቶልናል ብለዋል፡፡
#ሜቴክ ለአውቶብሶቹ መስሪያ የሚያስፈልገውን እቃዎች አስቀድሞ ገዝቷል፣ በተባለው ጊዜም ያደርስልናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ ወ/
ሮ እፀገነት ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን የከተማውን የትራንስፖርት እጥረት ለማቃለል ለብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ትዕዛዝ ከሰጣቸው 850 አውቶብሶች 700ዎቹን እስካሁን እንዳልተረከበ ተሰምቷል። ለአውቶብሶቹ 3.4 ቢሊዮን ብር #ተከፍሏል ነው የተባለው፡፡
የባለስልጣን መ/ቤቱ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሀላፊ ወ/ሮ እፀገነት አበበ ዛሬ ለሸገር FM 102.1 ሲናገሩ፣ ከሜቴክ ጋር የአውቶብሶቹን ስራ ውል የገባነው በሰኔ ወር 2009 ዓ/ም ሲሆን አውቶብሶቹን መረከብ የነበረብን ሰኔ 2010 ነበር ብለዋል፡፡
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አውቶብሶቹን በቃሌ መሰረት ያላስረከብኩት በውጪ ምንዛሬ ችግር ነው ብሎናል ያሉት ወ/ሮ እፀገነት ከዚህ ወር ጀምሮ ግን ቀስ በቀስ ቀሪ 700 አውቶብሶቹን ሊያስረክበን ቃል ገብቶልናል ብለዋል፡፡
#ሜቴክ ለአውቶብሶቹ መስሪያ የሚያስፈልገውን እቃዎች አስቀድሞ ገዝቷል፣ በተባለው ጊዜም ያደርስልናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ ወ/
ሮ እፀገነት ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia