TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
•መምህራን ለሁለት ዓመት ደሞዝ አልተከፈላቸውም!
•3.7 ሚሊየን ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ የመሆን ስጋት ተደቅኖባቸዋል!


#YEMEN

ጦርነት ባልተለያት የመን ውስጥ የሚገኙ ሁለት ሚሊየን ህፃናት ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት የህፃናት መርጃ ድርጅት(ዩኒሴፍ) አስታውቋል። ከእነዚህም ውስጥ አንድ አራተኛ የሚሆኑት ከፈረንጆቹ 2015 መጋቢት 2 ጀምሮ ትምህርታቸውን ያቋረጡ መሆናቸውን ገልጿል። #ዩኒሴፍ ባወጣው መግለጫ መምህራን ለሁለት ዓመታት ደመወዝ አለማግኘታቸውን ተከትሎ ሌሎች 3.7 ሚሊየን ህጻናትም ከትምህርት ገበታ ውጭ የመሆን ስጋት ተደቅኖባቸዋል።

በትምህርት ቤቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች፣ መፈናቀል እና ግጭቶች ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ ያደረጉ ምክንያቶች ናቸው ሲሉ በየመን የዩኒሴፍ ተወካይ ሳራ ቤይሶሎ ኛታኒ ተናግረዋል። የህጻናቱ ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆን ልጆች ወደ ጦርነት እንዲገቡ መገደድና ለሌሎች ጫና እየተዳረጉ መሆኑንም ነው የጠቆሙት። እንደ ዩኒሴፍ መረጃ እድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ 1.8 ሚሊየን ህፃናት ለተመጣጠነ ምግብ እጥረት ተጋልጠዋል።

ምንጭ፦ አል ጀዚራ/በENA ይቀረበ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia