TIKVAH-ETHIOPIA
#EthioTelecom ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ መንፈቅ ዓመት 33.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጿል። ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ “ሊድ” የተሰኘ የሦስት ዓመት አዲስ የእድገት ስትራቴጂውን በ2015 በጀት ዓመት መጀመሪያ ካስተዋወቀ በኋላ የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ሪፖርቱን ዛሬ አቅርቧል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈታሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ኢትዮ ቴሌኮም በ2015…
ተጨማሪ መረጃዎች ፦
(ኢትዮ ቴሌኮም)
#DevicePenetration 📱
በኢትዮጵያ 31 ሚሊየን (46%) ዜጎች የዘመናዊ ስልክ ( SmartPhone) ተጠቃሚዎች መሆናቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል። ከዚህ ውጭ ያሉ (Basic Feature Phone) ተጠቃሚዎች ደግሞ 47.5 ሚሊዮን መድረሳቸውን ነው የተገለጸው። ዳታ የሚጠቀሙ መሳሪያዎች (Data Devices) ደግሞ 1.2 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።
#NetProfit 💶
ኢትዮ ቴሌኮም በ2022 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት መሰረት 9 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልጿል።
በያዝነው በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ሪፖርቱ መሰረት ደግሞ 8.18 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል።
ይህም በግማሽ ዓመቱ የተገኘ ትልቅ ውጤት መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ አስታውቀዋል።
ለዚህም ኩባንያው የያዘው የወጪ ቁጠባ ስትራቴጂ ትልቅ ድርሻ ተጫውቷል ተብሏል። በዚህም በግማሽ በጀት ዓመቱ 3.5 ቢሊዮን ብር የወጪ ቁጠባ ማድረጉን አስታውቀዋል።
#TeleBirr
የቴሌ ብር ደንበኞች 27.2 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን 217 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ነው የተጠቀሰው። ይህም ከ193 ሚሊዮን የዝውውር ብዛት (Transaction Volume) የተገኘ ነው።
ከኢንተርናሽናል ሬሚታንስ ደግሞ 1.6 ሚሊዮን ዶላር ዝውውርም የተፈጸመ ሲሆን ይህም ከ44 ሀገራት (Remitance Countries) የተገኘ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ 98.8 ኤጀንቶች፤ 372 ሱቆች፤ 18 ባንኮች፤ 25.5 ሺህ ሻጮች በመተግበሪያው ተመዝግበው እንደሚገኙ በግማሽ ዓመት ሪፖርቱ ተጠቅሷል።
@tikvahethiopia
(ኢትዮ ቴሌኮም)
#DevicePenetration 📱
በኢትዮጵያ 31 ሚሊየን (46%) ዜጎች የዘመናዊ ስልክ ( SmartPhone) ተጠቃሚዎች መሆናቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል። ከዚህ ውጭ ያሉ (Basic Feature Phone) ተጠቃሚዎች ደግሞ 47.5 ሚሊዮን መድረሳቸውን ነው የተገለጸው። ዳታ የሚጠቀሙ መሳሪያዎች (Data Devices) ደግሞ 1.2 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።
#NetProfit 💶
ኢትዮ ቴሌኮም በ2022 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርት መሰረት 9 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልጿል።
በያዝነው በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ሪፖርቱ መሰረት ደግሞ 8.18 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል።
ይህም በግማሽ ዓመቱ የተገኘ ትልቅ ውጤት መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ አስታውቀዋል።
ለዚህም ኩባንያው የያዘው የወጪ ቁጠባ ስትራቴጂ ትልቅ ድርሻ ተጫውቷል ተብሏል። በዚህም በግማሽ በጀት ዓመቱ 3.5 ቢሊዮን ብር የወጪ ቁጠባ ማድረጉን አስታውቀዋል።
#TeleBirr
የቴሌ ብር ደንበኞች 27.2 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን 217 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ነው የተጠቀሰው። ይህም ከ193 ሚሊዮን የዝውውር ብዛት (Transaction Volume) የተገኘ ነው።
ከኢንተርናሽናል ሬሚታንስ ደግሞ 1.6 ሚሊዮን ዶላር ዝውውርም የተፈጸመ ሲሆን ይህም ከ44 ሀገራት (Remitance Countries) የተገኘ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ 98.8 ኤጀንቶች፤ 372 ሱቆች፤ 18 ባንኮች፤ 25.5 ሺህ ሻጮች በመተግበሪያው ተመዝግበው እንደሚገኙ በግማሽ ዓመት ሪፖርቱ ተጠቅሷል።
@tikvahethiopia