ኢትዮ ቴሌኮም የኢንተርኔት አገልግሎቱ በመጠባበቂያ መስመሮች ብቻ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
ተቋሙ ከሀገር ውጭ በሚገኙ ከፍተኛ ባንድዊድዝ ተሸካሚ ዓለም አቀፍ ባህር ጠለቅ የኢንተርኔት መገናኛ መስመሮች ላይ አጋጥሞኛል ባለው ችግር ምክንያት የኢንተርኔት አገልግሎቱ በመጠባበቂያ መስመሮች ብቻ እየሰራ መሆኑ አሳውቋል።
በዚህም የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ ወይም የፍጥነት መቀነስ ሊያጋጥም እንደሚችል በመግለፅ ይቅርታ ጠይቋል።
አገልግሎቱን በፍጥነት ለማስቀጠል ከአገልግሎት አቅራቢዎቹ ጋር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ መሆኑና ደንበኞቹ በትዕግስት እንዲጠብቁት ጠይቋል።
@tikvahethiopia
ተቋሙ ከሀገር ውጭ በሚገኙ ከፍተኛ ባንድዊድዝ ተሸካሚ ዓለም አቀፍ ባህር ጠለቅ የኢንተርኔት መገናኛ መስመሮች ላይ አጋጥሞኛል ባለው ችግር ምክንያት የኢንተርኔት አገልግሎቱ በመጠባበቂያ መስመሮች ብቻ እየሰራ መሆኑ አሳውቋል።
በዚህም የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ ወይም የፍጥነት መቀነስ ሊያጋጥም እንደሚችል በመግለፅ ይቅርታ ጠይቋል።
አገልግሎቱን በፍጥነት ለማስቀጠል ከአገልግሎት አቅራቢዎቹ ጋር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ መሆኑና ደንበኞቹ በትዕግስት እንዲጠብቁት ጠይቋል።
@tikvahethiopia
የዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ጥያቄ ምንድነው ? ፤ የትምህርት ሚኒስቴር ምላሽስ ?
• " እንደዚህ ዓይት ውሳኔ ላይ የተደረሰው አጠቃላይ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ኃላፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው " - የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት ፍቅረስላሴ አካሉ (ለአዲስ ስታንዳርድ)
• " ማህበራችን የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ አላቀረበም " - ዶ/ር በፍቃዱ ዘለቀ (ለዶቼ ቨለ)
• " መምህራን የሚያነሷቸውን ጥያቄዎችን ህጋዊ ከሆነው #የኢትዮጵያ_መምህራን_ማህበር ጋር ብቻ በመነጋገር የሚፈታ ነው " - ወይዘሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል (ከትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እየሰሩ ያሉ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ከህዳር 26 ቀን 2015 ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ የሚገልፅ ፅሁፍ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ከሰሞኑን ተሰራጭቷል።
መምህራኑና ቴክኒካል ረዳቶቹ አድማ እንደሚያደርጉ የተገላፀበት ይኸው ፅሁፍ ለትምህርት ሚንስቴር እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፃፉን የሚገልፅ ሲሆን " ያቀረብነው ጥያቄ ምላሽ አላገኘም " በሚል ምክንያትነው አድማው ይደረጋል የሚለው።
ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ቃላቸውን ለ " አዲስ ስታንዳርድ " ሚዲያ የሰጡ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ተከታዩን ብለዋል ፦
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት ፍቅረስላሴ አካሉ ፦
" እንደዚህ ዓይት ውሳኔ ላይ የተደረሰው አጠቃላይ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ኃላፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው።
ስራ የማቆሙ ሃሳብ ሁሉም መምህራን የሚጋሩት ነው። በቀጣይ የዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር መግለጫ ያወጣል። "
የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ መምህር ጥላሁን ረጋ ፦
" የመምህራን ደሞዝ አነስተኛ በመሆኑ በአገሪቱ ያለውን የኑሮ ውድነት መቋቋም አልተቻለም።
በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ ላሉ መምህራን የሚደርሳቸው የተጣራ ደሞዝ 8 ሺህ 5 መቶ ብር ብቻ ነው። ይህ እንዲሻሻልልን የጠየቅን ቢሆንም እስካሁን ድረስ አልተመለሰልንም።
መንግስት የመምህራንን ጥያቄ ባለመመለሱና ችላ በማለቱ በትምህርት ጥራቱ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያደረሰ ነው። ከምስራቅ አፍሪካ በኢኮኖሚ ትልቅ ሆና ለመምህራን ዝቅተኛ ደሞዝ የምትከፍል ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት።
የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በሙሉ ስራ ለማቆም ዝግጁ ናቸው። "
አንድ ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ የዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህር ፦
" የመምህራን ማህበር #ለጥያቄዎቻችን ትኩረት መስጠት ባለመቻሉ ከሁሉም ዩኒቨርሲቲ የተውጣጡ መምህራን ተመካክረንበት ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች በኩል መግለጫችንን ይፋ አድርገናል።
መምህራን ወር በደረሰ ቁጥር የቤት ኪራይ ምን እከፍላለሁ ልጆቼን ምን አበላለሁ እያለ በመጨናነቅ ለማስተማር በቂ ዝግጀት ስለማያደርግ የትምርት ጥራቱ ላይ ተፅኖ እያደረሰ ነው። "
(መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶች የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉ የሚገልፀው ፅሁፍ በዚህ የተያያዘ ነው ፦ https://telegra.ph/University-11-29
የኢትዮጵያ የዩኒቨርስቲዎች መምህራን እና ቴክኒክ ረዳቶች ማኅበር ለዶቼ ቨለ ሬድዮ በሰጠው ቃል በዩኒቨርሲቲዎች መምህራን የፊታችን ሰኞ ኅዳር 26 ቀን/2015 ይደረጋል የተባለውን የሥራ ማቆም አድማ
እኔ አልጠራሁትም ሲል አስታውቋል።
ፕሬዜዳንቱ ዶክተር በፍቃዱ ዘለቀ ፤ የመምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ማኅበር የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ አላቀረበም ብለዋል። ተናግረዋል።
ዶክተር በፍቃዱ ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ ሲሆን የሚመሩት ማኅበር ለኢትዮጵያ መንግሥት የቀረቡት 14 ጥያቄዎች በእርግጥም ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች መሆናቸውን ቢያረጋግጡም የሥራ ማቆም አድማ ግን አልጠራንም ሲሉ ገልጸዋል።
ማኅበሩ ይህንን ያደረጉት " የማናውቃቸው የተደራጁ አካላት ናቸው " ብሏል። ይህን ያደረጉ ያላቸውንም አካላት እንደሚከስ ለዶቼቫለ ሬድዮ አሳውቋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ " መምህራን የሚያነሷቸውን የተለያዩ ጥያቄዎች ለመፍታት ከመምህራን ማህበር ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑን " ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ትላንት ለህ/ተ/ም/ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተናግረዋል።
መምህራኑ ባነሱት ጉዳይ አስተያያታቸውን ለቲክቫህ የሰጡት የትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አመለወርቅ ህዝቅኤል በበኩላቸው ፤ መመህራን የሚያነሷቸውን ጥያቄዎችን ህጋዊ ከሆነው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ጋር ብቻ በመነጋገር የሚፈታ መሆኑን አመልክተዋል።
@tikvahethiopia
• " እንደዚህ ዓይት ውሳኔ ላይ የተደረሰው አጠቃላይ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ኃላፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው " - የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት ፍቅረስላሴ አካሉ (ለአዲስ ስታንዳርድ)
• " ማህበራችን የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ አላቀረበም " - ዶ/ር በፍቃዱ ዘለቀ (ለዶቼ ቨለ)
• " መምህራን የሚያነሷቸውን ጥያቄዎችን ህጋዊ ከሆነው #የኢትዮጵያ_መምህራን_ማህበር ጋር ብቻ በመነጋገር የሚፈታ ነው " - ወይዘሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል (ከትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እየሰሩ ያሉ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ከህዳር 26 ቀን 2015 ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ የሚገልፅ ፅሁፍ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ከሰሞኑን ተሰራጭቷል።
መምህራኑና ቴክኒካል ረዳቶቹ አድማ እንደሚያደርጉ የተገላፀበት ይኸው ፅሁፍ ለትምህርት ሚንስቴር እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፃፉን የሚገልፅ ሲሆን " ያቀረብነው ጥያቄ ምላሽ አላገኘም " በሚል ምክንያትነው አድማው ይደረጋል የሚለው።
ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ቃላቸውን ለ " አዲስ ስታንዳርድ " ሚዲያ የሰጡ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ተከታዩን ብለዋል ፦
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት ፍቅረስላሴ አካሉ ፦
" እንደዚህ ዓይት ውሳኔ ላይ የተደረሰው አጠቃላይ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ኃላፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው።
ስራ የማቆሙ ሃሳብ ሁሉም መምህራን የሚጋሩት ነው። በቀጣይ የዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር መግለጫ ያወጣል። "
የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ መምህር ጥላሁን ረጋ ፦
" የመምህራን ደሞዝ አነስተኛ በመሆኑ በአገሪቱ ያለውን የኑሮ ውድነት መቋቋም አልተቻለም።
በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ ላሉ መምህራን የሚደርሳቸው የተጣራ ደሞዝ 8 ሺህ 5 መቶ ብር ብቻ ነው። ይህ እንዲሻሻልልን የጠየቅን ቢሆንም እስካሁን ድረስ አልተመለሰልንም።
መንግስት የመምህራንን ጥያቄ ባለመመለሱና ችላ በማለቱ በትምህርት ጥራቱ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያደረሰ ነው። ከምስራቅ አፍሪካ በኢኮኖሚ ትልቅ ሆና ለመምህራን ዝቅተኛ ደሞዝ የምትከፍል ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት።
የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በሙሉ ስራ ለማቆም ዝግጁ ናቸው። "
አንድ ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ የዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህር ፦
" የመምህራን ማህበር #ለጥያቄዎቻችን ትኩረት መስጠት ባለመቻሉ ከሁሉም ዩኒቨርሲቲ የተውጣጡ መምህራን ተመካክረንበት ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች በኩል መግለጫችንን ይፋ አድርገናል።
መምህራን ወር በደረሰ ቁጥር የቤት ኪራይ ምን እከፍላለሁ ልጆቼን ምን አበላለሁ እያለ በመጨናነቅ ለማስተማር በቂ ዝግጀት ስለማያደርግ የትምርት ጥራቱ ላይ ተፅኖ እያደረሰ ነው። "
(መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶች የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉ የሚገልፀው ፅሁፍ በዚህ የተያያዘ ነው ፦ https://telegra.ph/University-11-29
የኢትዮጵያ የዩኒቨርስቲዎች መምህራን እና ቴክኒክ ረዳቶች ማኅበር ለዶቼ ቨለ ሬድዮ በሰጠው ቃል በዩኒቨርሲቲዎች መምህራን የፊታችን ሰኞ ኅዳር 26 ቀን/2015 ይደረጋል የተባለውን የሥራ ማቆም አድማ
እኔ አልጠራሁትም ሲል አስታውቋል።
ፕሬዜዳንቱ ዶክተር በፍቃዱ ዘለቀ ፤ የመምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች ማኅበር የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ አላቀረበም ብለዋል። ተናግረዋል።
ዶክተር በፍቃዱ ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ ሲሆን የሚመሩት ማኅበር ለኢትዮጵያ መንግሥት የቀረቡት 14 ጥያቄዎች በእርግጥም ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን እና ቴክኒካል ረዳቶች መሆናቸውን ቢያረጋግጡም የሥራ ማቆም አድማ ግን አልጠራንም ሲሉ ገልጸዋል።
ማኅበሩ ይህንን ያደረጉት " የማናውቃቸው የተደራጁ አካላት ናቸው " ብሏል። ይህን ያደረጉ ያላቸውንም አካላት እንደሚከስ ለዶቼቫለ ሬድዮ አሳውቋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ፤ " መምህራን የሚያነሷቸውን የተለያዩ ጥያቄዎች ለመፍታት ከመምህራን ማህበር ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑን " ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ትላንት ለህ/ተ/ም/ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተናግረዋል።
መምህራኑ ባነሱት ጉዳይ አስተያያታቸውን ለቲክቫህ የሰጡት የትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አመለወርቅ ህዝቅኤል በበኩላቸው ፤ መመህራን የሚያነሷቸውን ጥያቄዎችን ህጋዊ ከሆነው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ጋር ብቻ በመነጋገር የሚፈታ መሆኑን አመልክተዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የወደዱትን የሥዕል ሥራ ይምረጡ!
በሪድም ዘጀነሬሽን አዘጋጅነት ወደ 80 የሚጠጉ ወጣቶችን ያሳተፈውና በ16 ቡድኖች የተከናወነው የሥዕል ውድድር አሸናፊ በነገው ዕለት በይፋ ይገለጻል።
ወጣቶቹ ወጣት ሰዓሊያን አወንታዊ የሰላም ግንባታ፤ የአብሮነትና የግጭት አፈታት እንዲሁም ዕርቀ ሰላም ላይ ያተኮረ መልዕክታቸውን በሥዕላቸው አስተላልፈዋል።
አሸናፊው የሚለየው በዳኞች 70 በመቶ ውጤትና የቲክቫህ ቤተሰቦች 30 በመቶ ድምጽ ነው። ተወዳዳሪዎቹ ሥዕሎቻቸውን እንዲሁም የስዕሉ ጽንሰ ሀሳብ የያዘ መግለጫ አዘጋጅተው አቅርበዋል።
እርሶም የሥዕል ሥራዎቹን በመመልከት ለወደዱት የሥዕል ሥራ ድምጽ https://redeem.tikvahethiopia.net/ ላይ በመግባት ይስጧቸው።
@tikvahethiopia
በሪድም ዘጀነሬሽን አዘጋጅነት ወደ 80 የሚጠጉ ወጣቶችን ያሳተፈውና በ16 ቡድኖች የተከናወነው የሥዕል ውድድር አሸናፊ በነገው ዕለት በይፋ ይገለጻል።
ወጣቶቹ ወጣት ሰዓሊያን አወንታዊ የሰላም ግንባታ፤ የአብሮነትና የግጭት አፈታት እንዲሁም ዕርቀ ሰላም ላይ ያተኮረ መልዕክታቸውን በሥዕላቸው አስተላልፈዋል።
አሸናፊው የሚለየው በዳኞች 70 በመቶ ውጤትና የቲክቫህ ቤተሰቦች 30 በመቶ ድምጽ ነው። ተወዳዳሪዎቹ ሥዕሎቻቸውን እንዲሁም የስዕሉ ጽንሰ ሀሳብ የያዘ መግለጫ አዘጋጅተው አቅርበዋል።
እርሶም የሥዕል ሥራዎቹን በመመልከት ለወደዱት የሥዕል ሥራ ድምጽ https://redeem.tikvahethiopia.net/ ላይ በመግባት ይስጧቸው።
@tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ
የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ፤ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት የመለያ ቁጥር (0000039688) የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀምው አሳስቧል።
ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የገባ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት (NIDO FORTIFIED 400g Full Cream Milk Powder, Batch No. 0000039688) የተባለው ምርት መያዣ ዕቃው (ጣሳው) ላይ የተፃፈው ድብቅ ጽሁፍ (Barcode) ሲነበብ የምርቱ የመጠቀሚያ ጊዜ እ.ኤ.አ 09/2021 የሚል ሲሆን ከምርት መያዣ እቃው (ጣሳው) ላይ የተፃፈው ደግሞ እ.ኤ.አ 01/2024 እንደሆነ ያሳያል፡፡
በመሆኑም በድብቅ ጽሁፉ (Barcode) የሚወጣው የምርቱ ሙሉ መረጃ ላይ የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት መሆኑን የሚያሳይ ስለሆነ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት የመለያ ቁጥር (0000039688) የሆነውን ምርት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀምው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ፤ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት የመለያ ቁጥር (0000039688) የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀምው አሳስቧል።
ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የገባ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት (NIDO FORTIFIED 400g Full Cream Milk Powder, Batch No. 0000039688) የተባለው ምርት መያዣ ዕቃው (ጣሳው) ላይ የተፃፈው ድብቅ ጽሁፍ (Barcode) ሲነበብ የምርቱ የመጠቀሚያ ጊዜ እ.ኤ.አ 09/2021 የሚል ሲሆን ከምርት መያዣ እቃው (ጣሳው) ላይ የተፃፈው ደግሞ እ.ኤ.አ 01/2024 እንደሆነ ያሳያል፡፡
በመሆኑም በድብቅ ጽሁፉ (Barcode) የሚወጣው የምርቱ ሙሉ መረጃ ላይ የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት መሆኑን የሚያሳይ ስለሆነ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት የመለያ ቁጥር (0000039688) የሆነውን ምርት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀምው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተጠናቋል
በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 5ኛ ዓመት የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ ተጠናቆ መፅሀፍቱ ታሽጎ ተልኳል።
ካለው የተማሪ ቁጥር አንፃር ማድረግ የቻልነው እጅግ ጥቂት ቢሆንም በቀጣይ ወራት ተጨማሪ ዘመቻ በማድረግ ከቤተሰባችን አባላት ቤት መፅሀፍ በመውሰድ ተጨማሪ ለመላክ ጥረት እናድረጋለን።
በዚህ ስራ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ያለማንም የጀርባ አጋዥ / አካል በራሳቸው መፅሀፍ ያበረከቱ ፣ ያስላኩ፣ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።
የአዲስ አበባ አባላት በዚህ ዙር ከ7 ሺህ መፅሀፍ በላይ አበርክተዋል።
@tikvahethiopia
በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 5ኛ ዓመት የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ ተጠናቆ መፅሀፍቱ ታሽጎ ተልኳል።
ካለው የተማሪ ቁጥር አንፃር ማድረግ የቻልነው እጅግ ጥቂት ቢሆንም በቀጣይ ወራት ተጨማሪ ዘመቻ በማድረግ ከቤተሰባችን አባላት ቤት መፅሀፍ በመውሰድ ተጨማሪ ለመላክ ጥረት እናድረጋለን።
በዚህ ስራ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ያለማንም የጀርባ አጋዥ / አካል በራሳቸው መፅሀፍ ያበረከቱ ፣ ያስላኩ፣ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።
የአዲስ አበባ አባላት በዚህ ዙር ከ7 ሺህ መፅሀፍ በላይ አበርክተዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጠናቋል በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 5ኛ ዓመት የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ ተጠናቆ መፅሀፍቱ ታሽጎ ተልኳል። ካለው የተማሪ ቁጥር አንፃር ማድረግ የቻልነው እጅግ ጥቂት ቢሆንም በቀጣይ ወራት ተጨማሪ ዘመቻ በማድረግ ከቤተሰባችን አባላት ቤት መፅሀፍ በመውሰድ ተጨማሪ ለመላክ ጥረት እናድረጋለን። በዚህ ስራ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ያለማንም…
#እናመሰግናለን
በኮቪድ ወረርሽኝ እንዲሁም በጦርነት ምክንያት ለ2 ዓመት ተቋርጦ የነበረው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የ5ኛው ዓመት የመማሪያ መፅሀፍትን ማሰባሰብ ዘመቻ ተጠናቆ መፅሀፍቱን ለት/ቤቶች አድርሰናል።
በአጠቃላይ የተሰበሰበው መፅሀፍ እንዲከፋፈል ያደረግነው ፦
- መርሳ 2ኛ ደረጃና ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት ፣ ውርጌሳ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሲሪንቃ ሁለተኛ ደረጃ እና ሙሉ ሳይክል ት/ቤት እነዚህ በአማራ ክልል በጦርነት ቀጠና የነበሩ ት/ቤቶች ሲሆን የመማሪያ መፅሀፍት እጥረት እንዳለባቸው ከአካባቢው ቤተሰቦቻችን በደረሰን መረጃ ለሶስቱም ከተሰበሰበው መፅሀፍ አከፋፍለናል። ለእነዚህ ት/ቤቶች በቀጣይም ተጨማሪ ለመላክ ታቅዷል።
- ዶሮ ግብርና ወደዪ ሜዳ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አጋዥ እና በቀድሞው ካሪኩለም የታተሙ መፅሀፍትን የላክን ሲሆን በአዲሱ ካሪኩለም የታተሙትን ኮፒ ለመላክ እየተዘጋጀን ነው። በተላኩት መፅሀፍት ውስጥ የልጆች መማሪያ የሚሆኑ የተረት መፅሀፍት አሉበት።
- ማላካ ፣ ኢርባኖ ፣ ህዳሴ የተባሉ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ት/ቤቶቹ የሚገኙት በደቡብ ክልል ከጅንካ ከተማ በ50 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ሲሆን በስፍራው ያሉ ቤተሰቦቻችን በመማሪያ መፅሀፍ ግብዓት እጥረት ሳቢያ በት/ቤቶቹ በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና የሚፈለገውን ያህል ውጤት አይመዘገብም ብለውናል። በዚህም ለሶስቱም ከተሰበሰበው መፅሀፍ በማካፈል ልከናል። ካለው ተማሪ ብዛት በቀጣይ ዙርም ተጨማሪ ለመላክ አቅደናል።
- ቤተሰብ የህዝብ ቤተመፅሀፍ አ/አ ከተማ መካኒሳ አካባቢ የተከፈተ አዲስ ቤተመፅሀፍ ሲሆን መፅሀፍ እንደሚያስፈልጋቸው በገለፁልን መሰረት ተመልክተን ከተሰበሰበው መፅሀፍ አካፍለናል ፤ በተጨማሪ 10 ሺህ ብር ሰጥተናል። በቀጣይ ተጨማሪ መፀሀፍ ለመስጠት ታቅዷል።
- ፈንታው ድንቁ መታሰቢያ አፀደ ህፃናት እና 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት #ቆቦ የሚገኝ ሲሆን በጦርነት ወቅት ለህትመት የሚገለገሉበት ኮምፒዩተር በመሰረቁ 2 ኮምፒዪተርና መፅሀፍትን ልከናል።
(መፅሀፍቱ የተበረከተው ከአዲስ አበባ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ነው፤ መፅሀፍ ያበረከቱ ቤተሰቦቻችን ስም ዝርዝራቸው በ @tikvahuniversity ላይ ይገኛል ፤ በዚህ ዙር በየቤቱ እየተኬደ ከተሰበሰበው መፅሀፍ በተጨማሪ ከመቶ ሺ ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መፅሀፍት በቤተሰቡ ስም ተገዝተው ተጨምረዋል)
ያጋጠሙ ችግሮች ፦ በዚህ ዙር #በየቤቱ መፅሀፍ ለማሰባሰብ እንዲሁም መፅሀፉን ለመላክ ከገጠመ የትራንስፖርት ችግር ውጭ ሁሉንም በቤተሰቡ አቅም ለማድረግ ተሞክሯል።
በቀጣይ ፦ አሁን የጎደሉትን መሙላት እና ተጨማሪ መላክ እንዱሁም በጦርነት የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን ለመድረስ ታስቧል።
ከአንድ ወር በኃላ በድጋሚ ሌላ ዙር በየቤቱ መፅሀፍ ለማሰባሰብ የሚሰራ ሲሆን በዚህ ዙር በቲክቫህ ላይ ማስታወቂያ የሚያሰሩ / መልዕክት የሚያስናግሩ ሁሉም ድርጅቶች የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ የሚያደርጋቸው የማስታወቂያ / መልዕክት ለቤተሰቡ መላኪያ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል።
ከመማሪያ መፅሀፍ በተጨማሪ ፦
👉 #ንፁህ_ወረቀቶችን (ኮፒ ለማድረግ) ፣
👉 ያገለገሉ በየቤቱ ያሉ ኮምፒዩተሮችን ፣ ታብሌቶችን
👉 ከከተማ ለወጡት ትምህርት ቤቶች ከመማሪያ መፅሀፍ በተጨማሪ አስተማሪ እና ጥላቻ የማይዘሩ የልብ ወለድና ሌሎች መፅሀፍትን የምናሰባስብ ይሆናል።
(ከዚህ ቀደም በነበሩ 4 ዓመታት በየዓመቱ የነበረውን የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ባለው ችግር በየአንድ እና ሁለት ወር ለማድረግ ይሰራል)
እንደ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የምናድረገው እጅግ በጣም ጥቂት ቢሆንም ይህን ለማስፋት እንሰራለን ፤ ሁሉም በያለበት #የራሱን ጥቂት አስተዋፆ ማድረግ ከቻለ ብዙሃንን መድረስ ይቻላል። ለማድረግ አቅም ቢያንሰን እንኳን ለወገናችን በጎ በማሰብ ችግሩን እንካፈለው።
#TikvahFamily❤️
0919743630
0703313630
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በኮቪድ ወረርሽኝ እንዲሁም በጦርነት ምክንያት ለ2 ዓመት ተቋርጦ የነበረው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የ5ኛው ዓመት የመማሪያ መፅሀፍትን ማሰባሰብ ዘመቻ ተጠናቆ መፅሀፍቱን ለት/ቤቶች አድርሰናል።
በአጠቃላይ የተሰበሰበው መፅሀፍ እንዲከፋፈል ያደረግነው ፦
- መርሳ 2ኛ ደረጃና ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት ፣ ውርጌሳ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሲሪንቃ ሁለተኛ ደረጃ እና ሙሉ ሳይክል ት/ቤት እነዚህ በአማራ ክልል በጦርነት ቀጠና የነበሩ ት/ቤቶች ሲሆን የመማሪያ መፅሀፍት እጥረት እንዳለባቸው ከአካባቢው ቤተሰቦቻችን በደረሰን መረጃ ለሶስቱም ከተሰበሰበው መፅሀፍ አከፋፍለናል። ለእነዚህ ት/ቤቶች በቀጣይም ተጨማሪ ለመላክ ታቅዷል።
- ዶሮ ግብርና ወደዪ ሜዳ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አጋዥ እና በቀድሞው ካሪኩለም የታተሙ መፅሀፍትን የላክን ሲሆን በአዲሱ ካሪኩለም የታተሙትን ኮፒ ለመላክ እየተዘጋጀን ነው። በተላኩት መፅሀፍት ውስጥ የልጆች መማሪያ የሚሆኑ የተረት መፅሀፍት አሉበት።
- ማላካ ፣ ኢርባኖ ፣ ህዳሴ የተባሉ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ት/ቤቶቹ የሚገኙት በደቡብ ክልል ከጅንካ ከተማ በ50 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ሲሆን በስፍራው ያሉ ቤተሰቦቻችን በመማሪያ መፅሀፍ ግብዓት እጥረት ሳቢያ በት/ቤቶቹ በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና የሚፈለገውን ያህል ውጤት አይመዘገብም ብለውናል። በዚህም ለሶስቱም ከተሰበሰበው መፅሀፍ በማካፈል ልከናል። ካለው ተማሪ ብዛት በቀጣይ ዙርም ተጨማሪ ለመላክ አቅደናል።
- ቤተሰብ የህዝብ ቤተመፅሀፍ አ/አ ከተማ መካኒሳ አካባቢ የተከፈተ አዲስ ቤተመፅሀፍ ሲሆን መፅሀፍ እንደሚያስፈልጋቸው በገለፁልን መሰረት ተመልክተን ከተሰበሰበው መፅሀፍ አካፍለናል ፤ በተጨማሪ 10 ሺህ ብር ሰጥተናል። በቀጣይ ተጨማሪ መፀሀፍ ለመስጠት ታቅዷል።
- ፈንታው ድንቁ መታሰቢያ አፀደ ህፃናት እና 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት #ቆቦ የሚገኝ ሲሆን በጦርነት ወቅት ለህትመት የሚገለገሉበት ኮምፒዩተር በመሰረቁ 2 ኮምፒዪተርና መፅሀፍትን ልከናል።
(መፅሀፍቱ የተበረከተው ከአዲስ አበባ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ነው፤ መፅሀፍ ያበረከቱ ቤተሰቦቻችን ስም ዝርዝራቸው በ @tikvahuniversity ላይ ይገኛል ፤ በዚህ ዙር በየቤቱ እየተኬደ ከተሰበሰበው መፅሀፍ በተጨማሪ ከመቶ ሺ ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው መፅሀፍት በቤተሰቡ ስም ተገዝተው ተጨምረዋል)
ያጋጠሙ ችግሮች ፦ በዚህ ዙር #በየቤቱ መፅሀፍ ለማሰባሰብ እንዲሁም መፅሀፉን ለመላክ ከገጠመ የትራንስፖርት ችግር ውጭ ሁሉንም በቤተሰቡ አቅም ለማድረግ ተሞክሯል።
በቀጣይ ፦ አሁን የጎደሉትን መሙላት እና ተጨማሪ መላክ እንዱሁም በጦርነት የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን ለመድረስ ታስቧል።
ከአንድ ወር በኃላ በድጋሚ ሌላ ዙር በየቤቱ መፅሀፍ ለማሰባሰብ የሚሰራ ሲሆን በዚህ ዙር በቲክቫህ ላይ ማስታወቂያ የሚያሰሩ / መልዕክት የሚያስናግሩ ሁሉም ድርጅቶች የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ የሚያደርጋቸው የማስታወቂያ / መልዕክት ለቤተሰቡ መላኪያ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል።
ከመማሪያ መፅሀፍ በተጨማሪ ፦
👉 #ንፁህ_ወረቀቶችን (ኮፒ ለማድረግ) ፣
👉 ያገለገሉ በየቤቱ ያሉ ኮምፒዩተሮችን ፣ ታብሌቶችን
👉 ከከተማ ለወጡት ትምህርት ቤቶች ከመማሪያ መፅሀፍ በተጨማሪ አስተማሪ እና ጥላቻ የማይዘሩ የልብ ወለድና ሌሎች መፅሀፍትን የምናሰባስብ ይሆናል።
(ከዚህ ቀደም በነበሩ 4 ዓመታት በየዓመቱ የነበረውን የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ባለው ችግር በየአንድ እና ሁለት ወር ለማድረግ ይሰራል)
እንደ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የምናድረገው እጅግ በጣም ጥቂት ቢሆንም ይህን ለማስፋት እንሰራለን ፤ ሁሉም በያለበት #የራሱን ጥቂት አስተዋፆ ማድረግ ከቻለ ብዙሃንን መድረስ ይቻላል። ለማድረግ አቅም ቢያንሰን እንኳን ለወገናችን በጎ በማሰብ ችግሩን እንካፈለው።
#TikvahFamily❤️
0919743630
0703313630
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#MoE
የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
መውጫ ፈተና በሁሉም መደበኛና መደበኛ ባልሆኑ መርሀግብሮች የሚመረቁ ተማሪዎችን እንደሚመለከትና ፈተናውን በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ገልጸዋል።
የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ከመደበኛ ተማሪዎች ባሻገር #የማታና #የርቀት ተመራቂ ተማሪዎችን እንደሚመለከት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በመውጫ ፈተና ዙሪያ ለመንግስትና ለግል ዩኒቨርስቲዎች የተዘጋጀ የምክክር መድረክ ሲከፍቱ እንዳሉት መውጫ ፈተና በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ለሚማሩ የቀን ፣የማታና የርቀት መርሀ ግብር ተመራቂዎች ይሰጣል።
ከዚህ ዓመት ጀምሮ በመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ የሚደረገውን የመውጫ ፈተና በኦንላይን ለመስጠት መታቀዱንም ዶክተር ሳሙኤል ጠቁመዋል።
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የመሠረተ ልማት አቅሞቻቸውን ከወዲሁ በማረጋገጥ ለፈተናው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር ) በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ ባሻገር የተማሪዎችንና የተቋማቱን ብቃት ለማሳደግ እንደሚያስችል ጠቁመዋል።
በምክክር መድረኩ ሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተገኝተዋል።
በምክክር መድረኩም በመውጫ ፈተና ዙሪያ እየተደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት ፣ የመሠረተ ልማትና የ2015 ምሩቃን መረጃዎች ቀርበው ውይይት ተደርጓል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
መውጫ ፈተና በሁሉም መደበኛና መደበኛ ባልሆኑ መርሀግብሮች የሚመረቁ ተማሪዎችን እንደሚመለከትና ፈተናውን በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ገልጸዋል።
የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ከመደበኛ ተማሪዎች ባሻገር #የማታና #የርቀት ተመራቂ ተማሪዎችን እንደሚመለከት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በመውጫ ፈተና ዙሪያ ለመንግስትና ለግል ዩኒቨርስቲዎች የተዘጋጀ የምክክር መድረክ ሲከፍቱ እንዳሉት መውጫ ፈተና በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ለሚማሩ የቀን ፣የማታና የርቀት መርሀ ግብር ተመራቂዎች ይሰጣል።
ከዚህ ዓመት ጀምሮ በመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ የሚደረገውን የመውጫ ፈተና በኦንላይን ለመስጠት መታቀዱንም ዶክተር ሳሙኤል ጠቁመዋል።
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የመሠረተ ልማት አቅሞቻቸውን ከወዲሁ በማረጋገጥ ለፈተናው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር ) በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ ባሻገር የተማሪዎችንና የተቋማቱን ብቃት ለማሳደግ እንደሚያስችል ጠቁመዋል።
በምክክር መድረኩ ሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተገኝተዋል።
በምክክር መድረኩም በመውጫ ፈተና ዙሪያ እየተደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት ፣ የመሠረተ ልማትና የ2015 ምሩቃን መረጃዎች ቀርበው ውይይት ተደርጓል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
#Ethiopia
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ #ኢትዮጵያ ይገኛሉ።
የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በትዊተር ገፃቸው ባሰራጩት መልዕክት ፤ ከአንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንዲሁም ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሐመት ጋር ውይይት እንዳደረጉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውይይቱ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተደረገ መሆኑና ውጤታማ ውይይት እንደሆነ አመልክተዋል።
" ትብብራችንን እንደሚጠናከር አልጠራጠርም " ሲሉም ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ #ኢትዮጵያ ይገኛሉ።
የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በትዊተር ገፃቸው ባሰራጩት መልዕክት ፤ ከአንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንዲሁም ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሐመት ጋር ውይይት እንዳደረጉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውይይቱ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የተደረገ መሆኑና ውጤታማ ውይይት እንደሆነ አመልክተዋል።
" ትብብራችንን እንደሚጠናከር አልጠራጠርም " ሲሉም ገልፀዋል።
@tikvahethiopia