#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 4 " ቀጨኔ አካባቢ " አንድ ድርጅት የቡና ገለባ ከሻገተ ለውዝ ጋር በመቀላቀል የምግብ ዘይት ሲያመርት ተገኝቷል።
ድርጅቱ ሊገኝ የቻለው የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ባደረጉት መደበኛ ክትትል መሆኑን የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደር እና ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል።
በተቋሙ ላይ ቅኝት ሲደረግ፦
- ዘይት ማምረቻው የጤና ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት የሌለው፤
- ለግብዓትነት የሚጠቀምባቸው ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተጠበቀ፤
- የንጽህና አጠባበቅ መስፈርቶችን ያላሟላ ሆኖ ተገኝቷል።
የቡና ገለባን #ከተበላሸ_ለውዝ ጋር በመቀላቀልም የምግብ ዘይት ሲያመርት ነው የተገኘው።
ይህ ድርጅት የተጠቀመባቸው ግብዓቶች ተገቢ ካለመሆናቸው በተጨማሪ በቀላሉ የሚበላሹና አፍላ ቶክሲን በመፍጠር ለተለያዩ የካንሰር በሽታ አጋላጭ መሆናቸው ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ፤ ድርጅቱ የተጠቀመባቸው ጥሬ እቃዎችና ባዕድ ግብዓቶች እንዲወገዱ እንደተደረገ እና በጉዳዩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ገልጿል።
ባለስልጣን መ/ቤቱ የድርጅቱን ስም አልገለፀም።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 4 " ቀጨኔ አካባቢ " አንድ ድርጅት የቡና ገለባ ከሻገተ ለውዝ ጋር በመቀላቀል የምግብ ዘይት ሲያመርት ተገኝቷል።
ድርጅቱ ሊገኝ የቻለው የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ባደረጉት መደበኛ ክትትል መሆኑን የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደር እና ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል።
በተቋሙ ላይ ቅኝት ሲደረግ፦
- ዘይት ማምረቻው የጤና ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት የሌለው፤
- ለግብዓትነት የሚጠቀምባቸው ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተጠበቀ፤
- የንጽህና አጠባበቅ መስፈርቶችን ያላሟላ ሆኖ ተገኝቷል።
የቡና ገለባን #ከተበላሸ_ለውዝ ጋር በመቀላቀልም የምግብ ዘይት ሲያመርት ነው የተገኘው።
ይህ ድርጅት የተጠቀመባቸው ግብዓቶች ተገቢ ካለመሆናቸው በተጨማሪ በቀላሉ የሚበላሹና አፍላ ቶክሲን በመፍጠር ለተለያዩ የካንሰር በሽታ አጋላጭ መሆናቸው ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ፤ ድርጅቱ የተጠቀመባቸው ጥሬ እቃዎችና ባዕድ ግብዓቶች እንዲወገዱ እንደተደረገ እና በጉዳዩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ገልጿል።
ባለስልጣን መ/ቤቱ የድርጅቱን ስም አልገለፀም።
@tikvahethiopia