TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኢራን

የኢራን ፕሬዝዳንት የሆኑት ኢብራሂም ራኢሲ ሲጓዙበት የነበረ ሄሊኮፕተር " #በአደገኛ_ሁኔታ " መሬት ላይ ማራፉን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

የሀገሪቱ ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሂሊኮፕተሩ በአደገኛ ሁኔታ አርፎበታል ወደተባለበት ስፍራ ላይ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንዳለ ገልጿል።

የነፍስ አድን ሠራተኞች ወደ ቦታው ለመድረስ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲል አሳውቋል።

ፕሬዝዳንቱ ሀገራቸው ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ የተገነቡ ሁለት ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ ወደ ሰሜን ምዕራቧ የአገሪቱ ከተማ ታብሪዝ እያመሩ ነበር።

ሄሊኮፕተሩ አርፎበታል በተባለው ስፍራ ላይ ባለው ከባድ ጭጋግ ምክንያት የነፍስ ማዳን ፍለጋ ሥራው አስቸጋሪ እንደሆነ ተነግሯል።

Credit - FARS

@tikvahethiopia