#Soufflet
60 ሚሊዮን ዩሮ ወጪ ተደርጎበት የተገነባው " ሱፍሌት ማልት ኢትዮጵያ " የተሰኘ ብቅል አምራች ፋብሪካ ዛሬ ተመረቀ።
የብቅል ፋብሪካው የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ስር በሚተዳደረው በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ነው የተገነባው።
በዛሬው የምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ፤ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ፤ የፋብሪካው አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ፋብሪካው 10 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን በአመት 60 ሺህ ቶን ብቅል የማምረት አቅም አለው ተብሏል።
በግብርና ላይ የሚሰራ " ኢንቪቮ ግሩፕ " በተባለ የፈረንሳይ 🇫🇷 ኩባንያ ስር የሚገኘው ሱፍሌት ማልት በ38 ሀገራት የተለያዩ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ፤ 90 የኢንዱስትሪ መንደሮች እና 13 ሺህ ሰራተኞች አሉት።
ኢንቪቮ ግሩፕ በተለያዩ ሀገሪት በገነባቸው 28 የብቅል ማምረቻዎች አማካኝነት በየአመቱ 2.6 ሚሊዮን ቶን ብቅል ለአለም ገበያ እያቀረበ ይገኛል።
መረጃው የኢትዮ ንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ ነው።
@tikvahethiopia
60 ሚሊዮን ዩሮ ወጪ ተደርጎበት የተገነባው " ሱፍሌት ማልት ኢትዮጵያ " የተሰኘ ብቅል አምራች ፋብሪካ ዛሬ ተመረቀ።
የብቅል ፋብሪካው የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ስር በሚተዳደረው በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ነው የተገነባው።
በዛሬው የምረቃ ስነስርዓት ላይ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ፤ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ፤ የፋብሪካው አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ፋብሪካው 10 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን በአመት 60 ሺህ ቶን ብቅል የማምረት አቅም አለው ተብሏል።
በግብርና ላይ የሚሰራ " ኢንቪቮ ግሩፕ " በተባለ የፈረንሳይ 🇫🇷 ኩባንያ ስር የሚገኘው ሱፍሌት ማልት በ38 ሀገራት የተለያዩ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ፤ 90 የኢንዱስትሪ መንደሮች እና 13 ሺህ ሰራተኞች አሉት።
ኢንቪቮ ግሩፕ በተለያዩ ሀገሪት በገነባቸው 28 የብቅል ማምረቻዎች አማካኝነት በየአመቱ 2.6 ሚሊዮን ቶን ብቅል ለአለም ገበያ እያቀረበ ይገኛል።
መረጃው የኢትዮ ንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ ነው።
@tikvahethiopia