TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#UpdateSport ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ #ባምላክ_ተሰማ የ2018 የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ የመልሱን የዋንጫ ጨዋታ የፊታችን #አርብ በቱኒዚያው ኤስፔራንስ እና በግብፁ አል ሃህሊ መካከል ቱኒዝ ላይ የሚደረገው ከባዱን ፍልሚያ በመሀል ዳኝነት እንዲመሩት ካፍ ወስኗል። አርቢተር ባምላክ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ VAR -ቪዲዮ ህግ ተግባራዊ በማድረግ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ አርቢትር ይሆናሉ።

ምንጭ፦ ethio kickoff
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባምላክ_ተሰማ

ማራቶን በአንድ ርምጃ ይጀመራል እንዲሉ የዛሬው የአፍሪካ ቁንጮ ኢንተርናሽናል አርቢትር የቀድሞዎቹን የኢትዮጵያ ምርጥ ተጫዋቾች የሆኑትን እነ ሙሉጌታ ከበደን (ወለዬው) ለመዳኘት ወደ ሜዳ ሲያመራ ልዩ ስሜት ተሰምቶት ነበር። እነሆ ዛሬ ከአመታት በኋላ የአህጉራችን አፍሪካ ኮኮቦችን እየመራ የአህጉሪቱን ታላቅ ውድድር ፍፃሜ ለመዳኘት ፊት አውራሪ ዳኛ ሆኖ ተመርጧል።

ባምላክ የፊታችን አርብ በካይሮ ስታዲዬም ታላቁ ሊቨርፑልን ለአውሮፓ ሻምፒዮንነት ያበቃውን ሳዲዮ ማኔን እና የፔፕ ጋርዲዮላን ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም የክላውዲዮ ራኒዬሪን ሌስተር ሲቲን ለእንግሊዝ ሻምፒዮንነት ያበቃው ሪያድ ማህሬዝን እየመራ ወደ ሜዳ ይገባል።

በአላማና መንፈሰ ጠንካራነት የተገነባው የባምላክ ጉዞ በአለም ዋንጫ ትውልድ አህጉሩን አፍሪካን ወክሎ የወርቅ ኳስ አሸናፊዎቹን ከመዳኘት የሚያግደው እንደማይኖር መናገር ይቻላል። በአለም አቀፍ የእግር ኳስ መድረክ ጥሩ ተጫዋች አይውጣብሽ የተባለች የሚመስለው ሃገራችን አሁን ስሟን የሚያስጠራ ጥሩ አጫዋች አግኝታለች።

Via #PetrosAshenafi

@tsegabwolde @tikvahethiopia