TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የሁለተኛው ቀን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሲሰጥ ውሏል።

በፀጥታ ችግር ምክንያት ከዚህ ቀደም በተሰጠው ብሄራዊ ፈተና ላይ መቀመጥ ያልቻሉ ተማሪዎች ባሉባቸው የአማራ፣ ኦሮሚያ፣ አፋርና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ከትላንት ጀምሮ ፈተናው መሰጠት መጀመሩ ይታወቃል።

ብሄራዊ ፈተናው ከነገ በስቲያ ይጠናቀቃል።

ፎቶ ፦ ወልዲያ ኮሚኒኬሽን (ዛሬ ጥር 25)

@tikvahethiopia
#OromiaRegion

Biiroon Fayyaa Oromiyaa Hakimoota (GP) baay'inni isaanii 2000 (Kuma lama) ta'e qacaree hojjachiisuu barbaada.

የኦሮሚያ ጤና ጥበቃ ቢሮ ' 2,000 ' የሚሆኑ አዲስ የተመረቁ ሀኪሞችን(GP) በክልሉ ባሉ ሆስፒታሎች በቋሚነት ለመቅጠር እንደሚፈልግ ባወጣው ማስታወቂያ አስታውቋል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ሀኪሞች ተመዝግበው ምደባ መውሰድ ይችላሉ ብሏል።

በዚህም መሰረት፦

👉 የአፋን ኦሮሞ ቋንቋን መናገር፣ ማንበብና መጻፍ የሚችል
👉 ብዛት - 2,000
👉 ደሞዝ - 9,056 ብር
👉 የትምህርት ማስረጃ - ዋናውንና ኮፒ፤
👉 የሞያ ፍቃድ - ዋናውና ኮፒ፤
👉 የምዝገባ ቀን - ማስታወቂያው ከተነገረበት ቀን አንስቶ ላልተወሰነ ጊዜ ባሉ የሥራ ሰዓቶች፤
👉 የምደባ ቀን - በዕጣ የሚወጣ ሲሆን ቀኑ በቀጣይ የሚገለጽ ይሆናል።
👉 የመመዝገቢያ ቦታ - የኦሮሚያ ጤና ቢሮ 3ኛ ፎቅ በሰው ኃብት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በአካል በመገኘት መመዝገብ ይችላሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የጤና ችግር አጋጥሟቸው ሆስፒታል መግባታቸው ተገልጿል። ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 6 በመስቀል አደባባይ ጉዳይ ሊያደርግ ያሰበው ስብሰባ በቅዱስነታቸው አለመገኘት ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉ ተነግሯል። ቅዱስነታቸው ፥ በገጠማቸው የጤና ችግር ምክንያት ሆስፒታል ስለገቡና…
#Update

ቋሚ ሲኖዶስ ሰላማዊ እና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የቤተክርስቲያንን መብት ለማስከበር እንደሚሰራ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የመስቀል አደባባይ፣ የጃንሜዳና ልሎች የቤተክርስቲያን ይዞታዎች ጉዳይ በተመለከተ ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጋር ለመነጋገር ዛሬ ይዞት በነበረው ቀጠሮ ዙሪያ ባካሔደው ስብሰባ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የሚደረገው ውይይት ቋሚ ሲኖዶስ በሚያስቀምጠው አቅጣጫና ጊዜ ቀጠሮ መሰረት በተለዋጭ ቀጠሮ የሚካሔድ ይሆናል ብሏል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ከሚቀጥለው ቀጠሮ ጀምሮ ሕጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የቤተክርስቲያኒቱ ጥያቄ ሕጋዊ ምላሽ እስከሚያገኝ ድረስ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበኩሉ ዛሬ የመስቀል አደባባይን አስመልክቶ የአዲስ አበባ አስተዳደር ፤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ለመወያየት ቀጠሮ ይዞ እንደነበር አስታውሷል።

የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ቀጠሮ በተያዘበት ቦታና ሰአት የተገኙ ቢሆንም ቅዱስ ሲኖዶሱ በላከው መልእክት ዛሬ በስብሰባው ላይ መገኘት ባለመቻላቸው ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲያዝ በመጠየቅ የዛሬው ስብሰባ ሳይካሄድ ቀርቷል ብሏል።

የአዲስ አበባ አስተዳደር ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጋር ለመወያየት እና አብሮ ለመስራት በማንኛውም ሁኔታና ሰአት ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

ከላይ ያሉት መረጃዎች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ህዝብ ግንኙነት እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተገኙ ሲሆን የዛሬው ስብሰባ ለምን እንደቀረ የተሰጠ ግልፅ ማብራሪያ ማግኘት አልቻልንም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Abyei #UNISFA

ተመድ ሜ/ጄነራል ቤንጃሚን ኦሉፊሚ ሳውየርን የአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ሃይል አዛዥ አድርጎ ሾሟል።

ሜ/ጄነራል ቤንጃሚን ኦሉፊሚ ዜግነታቸው ናይጄሪያዊ ሲሆኑ በኢትዮጵያዊው ሜጀር ጀነራል ከፍያለው አምዴ ተሰማ ምትክ ነው በቦታ የተሾሙት።

ሜ/ጀነራል ከፍያለው አምዴ በአብዬ ግዛት የነበረውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ሲመሩ እንደነበር ይታወቃል።

አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ሜ/ጄነራል ከፍያለው አምዴ የአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ኃይል አዘዥ ሆነው ከተሸሙበት ጊዜ አንስቶ ላሳዩት ትጋት፣ የሰጡት አግልግሎትና ውጤታማ አመራር ምስጋና አቅርበዋል።

ሱዳን በአብየ ግዛት ያለው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል ከስፍራው እንዲወጣ ጥያቄ ማቅረቧ ይታወሳል።

ከሳምንታት በፊት ተመድ በአብዬ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይል የመተካቱ ሂደት በየካቲት ወር እንደሚጀመር መግለፁ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

‘‘... ኢትዮጵያ ለእኛ ለአፍሪካውያን እና ለመላው ጥቁር ሕዝቦች እናታችን ናት፤ የነጻነታችን ትእምርት/Symbol የሆነች አገርም ናት።

ስለሆነም አዲስ አበባ 'የፓን አፍሪካን መዲና' (የአፍሪካ አንድነት ከተማ) መባሏ ከዚህ ታሪካዊ ሐቅ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ " - (የናይጄሪያው ሳንዴይ ኦብዘርቨር/ጁላይ 23፣ 1972)

#TadeleDerseh

ፎቶ፦ ፎቶግራፈር - አቡቲ እንግዳሸት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የኬንያንው ፕሬዜዳንት ተማፅኖ ....

በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት መቋጫ ያገኝ ዘንድ ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ከሚነገርላቸው ሀገራት ጎረቤታችን ኬንያ አንዷ ናት።

የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ከዚህ በፊት ለግጭቱ መቆሚያ መፍትሄ እንደመጣ ጥሪ ሲያቀርቡ እንደበር አይዘነጋም።

ትላንት ለሊት የተ.መ.ድ ዋና ፀሀፊት አንቶኒዮ ጉተሬዝን መልዕክት ተንተርሰው በኢትዮጵያ ግጭት እንዲቆም ተማፅነዋል።

ኬንያታ ምን አሉ ?

- የተመድ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ያቀረቡትን ጥሪ እንደሚጋሩ አስታውቀዋል።

- በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው ግጭት ውስጥ የሚሳተፉ አካላት ሁሉ ጦርነቱን እንዲያቆሙም ተማፅነዋል።

- የቀጠለው ግጭት የኢትዮጵያን ህዝብ እየዘረፈ እና የዚህ ታላቅ ህዝብ ባህልና ስልጣኔ ውስጥ ያለውን ክብር እያሳጣ ነው” ሲሉም ተናግረዋል።

- አስተማማኝ ሰላም የሚሰፍነው እንዲሁም የተረጋጋች ኢትዮጵያን እውን የምትሆነው ሁሉም የኢትዮጵያ አካላት ዘላቂ በሆነና በሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች ዘንድ ተቀባይነት ባለው መንገድ ፈተናዎችን ማለፍ ሲችሉ ብቻ ነው ብለዋል።

- ሁሉንም ያሳተፈና በመስማማት መንፈስ የሚካሄደው ሀገራዊ ውይይት፤ በግጭቱ ምክንያት ለተጎዱ በመላ ኢትዮጵያ የሚገኙ ማህበረሰቦች ያለውን ሸክም ከማቅልለ አንጻር ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል።

- የኢትዮጵያ፣ የቀጠናውና የአህጉሪቱ ብልፅግና፤ ዘላቂ በሆነ ሰላም እና ደህንነት ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት። አንድ ላይ ሆነን የተሻለ ዓለም መፍጠር እንችላለን ብለዋል።

ምንጭ፦ State House Kenya

@tikvahethiopia
#Borana

የኢትዮጵያጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስጣናት በቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ ጉብኝት እያደረጉ ነው።

የጠ/ሚ ፅ/ቤት ጉብኝቱ ፥ " በድርቅ የተጎዱ ማህበረሰቦችን ተግዳሮቶች በጥልቀት ለመገምገም " እንደሆነው ገልጿል።

ፅ/ቤቱ የዝናብ ውሀ እጥረት መከሰቱ የእንስሳት መኖ እጥረት እና የውሃ አቅርቦት ውስንነትን ጨምሮ በርካታ ፈታኝ ሁኔታዎችን ማስከተሉን አሳውቋል።

በሌላ መረጃ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ያቤሎ ኢፋ ቦሩ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤትን መጎብኘታቸው ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#GamoZone

በጋሞ ዞን የሰዓት እላፊ ማሻሻያ ተደረገበት።

የጋሞ ዞን ኮማንድ ፖስት #ለተሽከርካሪዎች የሠዓት ማሻሻያ ማድረጉን ትላንት ምሽት አሳውቋል።

ኮማንድ ፖስቱ የዞኑ ሠላም እንዲጠበቅ ለማድረግ በቂ የሆነ የሕዝባዊ ሠራዊት በመሠልጠኑ እንዲሁም የህብረተሰቡ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዳይገደብ የሠዓት ማሻሻያ ማድረጉ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልጿል።

በዚሁ መሠረት፦

- ለባለሁለት እግር ሞተር ሳይክል እስከ ምሽቱ 3:00 ሠዓት

- ለባለሦስት እግር ባጃጅ እስከ ምሽቱ 4:00 ሠዓት ማሻሻያ ማድረጉን የዞኑ ኮማንድ ፖስት ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray , #Mekelle 📍 የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በመቐለ ከተማ ለሚገኙ ሆስፒታሎች ወሳኝ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችን ማከፋፈል መጀመሩን ትላንት አሳውቋል። ድርጅቱ ባለፈው ሳምንት የመጀመሪያዎቹን አምስት በረራዎች ማጠናቀቁን ገልፆ በነበሩት በረራዎች ኢንሱሊንን ጨምሮ እጅግ አስቸኳይና አስፈላጊ መድሃኒቶችን ማጓጓዙን ገልጿል። ይኸው ተግባር በዚህ ሳምንትም እንደሚቀጥል አሳውቋል። @tikvahethiopia
#Tigray , #Mekelle📍

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በዚህ ሳምንት 2 በረራዎችን ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ በማድረግ የህክምና ቁሳቁሶችን አድርሷል።

ባለፈው ሳምንት በ5 በረራዎች እጅግ አስፈላጊ የህክምና ቁሳቁሶችን ወደ ትግራይ ክልል መቐለ ማጓጓዙና ማከፋፈል መጀመሩን መግለፁ ይታወሳል።

በዚህ ሳምንት ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና ከቀይ መስቀል የቀረቡ መድሃኒቶችና ሌሎች የህክምና አቅርቦቶችን በመያዝ 2 ተጨማሪ በረራዎች ወደ ትግራይ ክልል ተደርገዋል።

በዚህ ሳምንት በቀሩት ቀናት እና በሚቀጥሉት ሳምንታት ተመሳሳይ በረራዎች እንደሚደረጉ እና ይህም ቀጣይነት ያለው እርዳታ እንደሚሆን የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታውቋል።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ላለፉት ወራት የህክምና አቅርቦት ማድረግ እንዳልቻለ ገልፆ አሁን እየተደረጉ ያሉት እጅግ በጣም አስቸኳይ ለሰዎች ህይወት አድን የሚሆኑ አቅርቦቶች ናቸው ብሏል።

ከዚህ በተሻለ በርካታ የህክምና ቁሳቁሶች እና መድሃኒቶችን ለማድረስ ከአየር ላይ በረራ በተጨማሪ በየብስ ለማጓጓዝ መታሰቡን ይህን ተግባራዊ ለማድረግም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ከትግራይ ክልል በተጨማሪ በአፋር ክልል እና አማራ ክልል ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ገልጿል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
#Bank_of_Abyssinia

የአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግን በመጠቀም ካሉበት ሆነው የቪዛ ካርድዎን ማዘዝ የሚችሉ ሲሆን፣ ካርድዎ ሲደርስ በአቅራቢያዎ ከሚገኙት የአቢሲንያ ባንክ ቅርንጫፎቻችን መውሰድ ይችላሉ።

ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ የሚያገኙበትን የአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግን በመጠቀም ህይዎትዎን ያቅልሉ።

የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻነል ይቀላቀሉ! https://yangx.top/BoAEth
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU2022Summit እስካሁን የየት ሀገር ሚኒስትሮች ገቡ ? ነገ ለሚጀምረው የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች የሚሳተፉበት የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈፃሚ ም/ቤት ስብሰባ የተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ናቸው። እስካሁን የገቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ፦ 🇿🇼 ፍሬድሪክ ሻቫ (ዝምባብዌ) 🇸🇹 ኤዲቴ ራሞስ ቴንዡዋ (የሳዖቶሜና ፒሪንሲፔ) 🇨🇲 ሌዡን ቤላ ቤላ (ካሜሩን) 🇹🇩 ማህማት ዜኑ…
#AU2022Summit

የአፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በ35ተኛዉ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና በ40ኛዉ የስራ አስፈፃሚዎች ምክር ቤት ለመሳተፍ አዲስ አበባ እየገቡ ናቸው።

እስካሁን የገቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ፦

🇿🇼 ፍሬድሪክ ሻቫ (ዝምባብዌ)
🇸🇹 ኤዲቴ ራሞስ ቴንዡዋ (የሳዖቶሜና ፒሪንሲፔ)
🇨🇲 ሌዡን ቤላ ቤላ (ካሜሩን)
🇹🇩 ማህማት ዜኑ ሸሪፍ (ቻድ)
🇨🇮 ካንዲያ ካሚስኮ ካማራ (ኮትዲቯር)
🇸🇴 አብዲሳድ ሙሴ አሊ (ሶማሊያ)
🇨🇬 ዢያን ክላውዴ ጋኮሶ (የሪፐብሊክ ኮንጎ)
🇳🇪 ሀሱሚ ማሹዱ (ኒጀር ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
🇿🇦 ዶ/ር ናለዲ ፓንዶር (ደቡብ አፍሪካ)
🇸🇳 አሲታ ቶል ሳል (ሴኔጋል)
🇲🇷 እስማኤል ኡልድ ሼክ አህመድ (ሞሪታኒያ)
🇩🇯 ሙሀሙድ አሊ የሱፍ (ጂቡቲ)
🇱🇾 ናጅላ አልማንጉሽ (ሊቢያ)
🇳🇬 ጃፍሬ ኦኖማ (ናይጄሪያ)
🇦🇴 ቲቴአን ቶኒያ (አንጎላ)
🇺🇬 ኦሪም ሄነሪ ኦክሎ (ዩጋንዳ - የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ)
🇲🇼 ናይሲ ቴምቦ (ማላዊ)
🇩🇿 አምባሳደር ራምታን ላማምራ (አልጀሪያ)
🇬🇦 ሙበሌት ቡቤያ (ጋቦን)
🇲🇦 ቦሪታ ናስር (ሞሮኮ)
🇹🇳 ኦተማን ጃርዲ (ቱኒዚያ)
🇲🇬 ፖትሪክ ራአጆልንት (ማዳጋስካር)
🇨🇻 ማሪያና ዳጃምላ (ኬፕ ቨርዲ)
🇧🇮 አልበርት ሻንግሮ (ቡሩንዲ)
🇬🇶 ሲሞኔ ኦዮኖ ኢሶኔ (ኢኳቶሪያል ጊኒ)
🇰🇲 ዶህር ዶል ከማል (ኮሞሮስ)
🇸🇿 ቱሊሲሌ ድላድላ (ስዋህቲኒ)
🇰🇪 ረይሼል ኦማሞ (ኬኒያ)
🇲🇿 ቬሮኒካ ማካሞ ንዶቮ (ሞዛምቢክ)
🇹🇬 ኮምላን ኢዱ ሮበርት (ቶጎ)
🇿🇲 ስታንሌይ ካኩቦ (ዛምቢያ)
🇧🇼 ሌሞሀንግ ኪዌፔ (ቦትስዋና)
🇬🇲 ሳፊ ሳንካሬ (ጋምቢያ)
🇳🇦 ኔቱምቦ ናንዲ ንዳይትዋህ (ናሚቢያ - ም/ ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
🇪🇷 ኦስማን ሳሌህ (ኤርትራ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፅጌሬዳ_ግርማይ የተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይን ግድያ በተመለከተ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለቲክቫህ መረጃ ሰጥቷል። ሰኞ ዕለት ህይወቷ ያለፈው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይን በመግደል የተጠረጠረ ተማሪ ትላንት ከሰዓት ፍርድ ቤት ቀርቧል። ትላንት ፍርድ ቤት ቀርበው ምስክርነት የሰጡ የተጠርጣሪው #ሁለት_ጓደኞቹ የሚከተለውን ብለዋል :- "ተማሪ ፅጌሬዳ ከተጠርጣሪ ወንጀለኛው ጋር ግንኙነት…
#Update

የተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ።

በምትማርበት ተቋም አርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ ውስጥ በሰው እጅ በአሳዛኝ ሁኔታ የተገደለችው የ20 ዓመቷ ወጣት ፅጌሬዳ ግርማይ ስርዓተ ቀብሯ ተፈፅሟል።

የፅጌሬዳ ስርዓተ ቀብር የተፈፀመው በዳንሻ ከተማ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ነው።

ሰኞ ጥር 23 /2014 ምሽት ላይ በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተገደለችው ፅጌሬዳ ግርማይ የሁለተኛ ዓመት የሆቴል እና ቱሪዝም ማኔጅመት ተማሪ ነበረች።

የወጣቷን ህይወት እንደቀጠፈ የተጠረጠረው ተማሪ ከትላንት በስቲያ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ቀጣይ ቀጠሮ መስጠቱን መግለፃችን ይታወሳል።

ውድ ቤተሰቦቻችን @tikvahuniversity (ቲክቫህ ኢትዮጵያ) የተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይን የፍርድ ሂደት እስከመጨረሻው ድረስ ተከታትሎ ለማሳወቅ ጥረት ያደርጋል።

የፎቶ ባለቤት ፦ የሄኖክ ታደለ

@tikvahethiopia