TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ሰርቪስ ምንድነው ?
የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ምን አሉ ?
" በዚህ አመት ከቻልንና ለሚቀጥለው ዓመት ተግባራዊ ማድረግ ከቻልን ጥሩ ነው ካልቻልን ግን በእርግጠኝነት በ2019 ዓ/ም የምንጀምረው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ሰርቪስ የሚባል ፕሮግራም ነው።
ድሮ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች [እንደ እኔ እድሜ የጠገባችሁ ካላችሁ ታውቁታላችሁ] የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች 3ኛ ዓመት ሲጨርሱ 4ኛ ዓመት ከመግባታቸው በፊት ለ1 ዓመት በነፃ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ለማገልገልም ለራሳቸውም ተግባራዊ ትምህርት እንዲያገኙ በየክልሉ ሄደው በየሙያቸው ይሰሩ ነበር ለ1 ዓመት።
Basic ወጪያቸው ብቻ ከፍሎ ከዚያ ሲመለሱ 4ኛ ዓመት ይሆናሉ ብዙ ጥቅም ነበረው አንደኛ ተመልሰው ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ 4ኛ ዓመት የበለጠ በስለው ነው የሚገቡት ስለማህበረሰባቸው አውቀው ነው የሚገቡት ፤ ብዙ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን ከዛ በኃላ እነኚህ ሰርቪስ የወጡ ልጆች ሲያስተምሩ አስተማሪነትን ወደውት እዛው በአስተማሪነት የቀሩ ብዙ ሰዎች አሉ።
ይሄን ፕሮግራም እንጀምራለን " ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥለው ዓመት ወይም በ2019 ዓ/ም ተግባራዊ ለማድረግ ባቀደው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ሰርቪድ ፕሮግራም የዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ከመመቀራቸው በፊት በየክልሉ ሄደው ማህበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ ይደረጋሉ።
4 ዓመት ተምረው የሚጨርሱ 3ኛ ዓመት ፤ በ5 ዓመት ተምረው የሚጨርሱ 4ኛ ዓመት ላይ ወጪያቸው ተከፍለ አገልግሎት ይሰጣሉ። ይህ አዲስ የሚጀምረው ፕሮግራም በተለይ የመምህራንን እጥረት ለመቅረፍም አንዱ መንገድ ተደርጎ ተወስዷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
ቪድዮ፦ ኢቢሲ
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ምን አሉ ?
" በዚህ አመት ከቻልንና ለሚቀጥለው ዓመት ተግባራዊ ማድረግ ከቻልን ጥሩ ነው ካልቻልን ግን በእርግጠኝነት በ2019 ዓ/ም የምንጀምረው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ሰርቪስ የሚባል ፕሮግራም ነው።
ድሮ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች [እንደ እኔ እድሜ የጠገባችሁ ካላችሁ ታውቁታላችሁ] የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች 3ኛ ዓመት ሲጨርሱ 4ኛ ዓመት ከመግባታቸው በፊት ለ1 ዓመት በነፃ ያስተማራቸውን ማህበረሰብ ለማገልገልም ለራሳቸውም ተግባራዊ ትምህርት እንዲያገኙ በየክልሉ ሄደው በየሙያቸው ይሰሩ ነበር ለ1 ዓመት።
Basic ወጪያቸው ብቻ ከፍሎ ከዚያ ሲመለሱ 4ኛ ዓመት ይሆናሉ ብዙ ጥቅም ነበረው አንደኛ ተመልሰው ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ 4ኛ ዓመት የበለጠ በስለው ነው የሚገቡት ስለማህበረሰባቸው አውቀው ነው የሚገቡት ፤ ብዙ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን ከዛ በኃላ እነኚህ ሰርቪስ የወጡ ልጆች ሲያስተምሩ አስተማሪነትን ወደውት እዛው በአስተማሪነት የቀሩ ብዙ ሰዎች አሉ።
ይሄን ፕሮግራም እንጀምራለን " ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥለው ዓመት ወይም በ2019 ዓ/ም ተግባራዊ ለማድረግ ባቀደው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ሰርቪድ ፕሮግራም የዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ከመመቀራቸው በፊት በየክልሉ ሄደው ማህበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ ይደረጋሉ።
4 ዓመት ተምረው የሚጨርሱ 3ኛ ዓመት ፤ በ5 ዓመት ተምረው የሚጨርሱ 4ኛ ዓመት ላይ ወጪያቸው ተከፍለ አገልግሎት ይሰጣሉ። ይህ አዲስ የሚጀምረው ፕሮግራም በተለይ የመምህራንን እጥረት ለመቅረፍም አንዱ መንገድ ተደርጎ ተወስዷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
ቪድዮ፦ ኢቢሲ
@tikvahethiopia
“ የብድር ጣሪያው አለመነሳት በኢኮኖሚ ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ” - የፋይናንስ ባለሙያ
የብሔራዊ ባንክ፣ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ፣ ባለፈው ሳምንት ሁለተኛ ስብሰባውን በማካሔድ የተለያዩ ምክረ ሀሳቦችን ሰጥቷል፡፡
በኮሚቴው ውሳኔዎ ተፅዕኖ ዙሪያ አስተያየት እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አንድ የፋይናንስ ባለሙያ፣ “ ውሳኔው በስራ ፈጠራና በገቢ ማመንጨት በኩል ዋጋ ያስከፍለናል ” ብለዋል፡፡
በቡና ባንክ ዋና የስትራቴጂ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ሙሉነህ አያሌው በሰጡን የግል አስተያየት፣ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበት እየቀነሰ መምጣቱን እንደገለፀ አውስተው፣ ነገር ግን፣ “ መልሶ ያንሰራራል ” የሚል ስጋት ስላለው፣ ቀድሞ የነበሩትን ገደቦች አላነሳም ይላሉ፡፡
ከኮሚቴው ውሳኔዎች አንዱ፣ ቀደም ሲል በባንኮች የብድር ዕድገት ላይ የተቀመጠው የ18 በመቶ ገደብ በነበረበት እንዲቀጥል የሚያደርግ ነው፡፡ ይህ ውሳኔ የባንኮችን የማበደር ዕድል ይቀንሳል ይላሉ፡፡
ይህን በምሳሌ ሲያስረዱም ፥ “ አንድ ባንክ ባለፈው ሰኔ ወር 2016 ላይ የብድር መጠኑ 100 ቢሊዮን ከደረሰ፣ የሚቀጥለው ሰኔ ላይ 2017 ላይ 118 ቢሊዮን ነው ማድረስ የሚችለው ማለት ነው፡፡ ለዛውም፣ የሰበሰበው ብድር ተቀንሶ፣ ያልሰበሰበው ብድር ተደምሮ ነው እዛ መድረስ አለበት የሚባለው፡፡ በዚህ ስሌት ባንኩ ባለፈው አመት የሰጠው ብድር ብቻ ሳይሆን ከተመሰረተ ጀምሮ የሰጠው ብድርም ሊሆን ይችላል፡፡ እስካልተሰበሰበ ድረስ በብድርነት ይያዛል፡፡ ባንኩ ያልሰበሰበው ነባር ብድርና የሰጠው አዲስ ብድር ተደምሮ ነው የሚሰላው፡፡ በብድር ወለዱ ብቻም ጣሪያው ላይ ሊደርስ ይችላል፡፡ አንድ ባንክ፣ ባለፈው አመት 100 ቢሊዮን ብድር ከነበረውና የዚህ ወለዱ 18 ከመቶ ከሆነ፣ በዚህ አመት ምንም ብድር ሳይሰጥ የአምናው ብድር ብቻውን 118 ቢሊዮን ይሆናል፡፡ ሳያበድርም ሳይሰበስብም ጣሪያውን ሊደርስበት ይችላል ” ብለዋል።
አቶ ሙሉነህ አያሌው የዚህ ተፅዕኖው ምን እንደሆነ እንዲህ ሲሉ አስረድተዋል።
“ ይህ ውሳኔ የኢኮኖሚ ዕድገቱን ያቀዘቅዘዋል፡፡ በስራ እድል ፈጠራ እና በገቢ ማመንጨት በኩል ዋጋ ያስከፍለናል፡፡ የብድር አቅርቦት መኖር፣ ሰዎች ተበድረው ስራ እንዲሰሩና የስራ እድል እንዲፈጥሩ ያበረታታል፡፡ የብድር አቅርቦት ከሌለ ኢንቨስትመንት ይዳከማል፣ የስራ ዕድል አይኖርም፣ ሰዎች ገቢ አያመነጩም ማለት ነው፡፡ ያ ባለመሆኑ ይህንን ዋጋ ነው እየከፈልን ነው ያለነው፡፡ ”
የብድር አቅርቦቱ ውስን ስለሆነ፣ ባንኮች የብድር አሰጣጥ ላይ ጠበቅ ያሉ መስፈርቶችን ይጠቀማሉ ብለዋል፣ ባለሙያው፡፡
እሳቸው እንደሚሉት፣ አንድ እቃ ከገበያ ሲጠፋ፣ አለያም አቅርቦቱ ሲቀንስ ዋጋው እንደሚወደደው፣ የባንኮች ብድርም በተመሳሳይ አቅርቦቱ ሲቀንስ ዋጋው (ወለዱ) ይወደዳል፡፡ አቶ ሙሉነህ ይህን እንዲህ በማለት አብራርተዋል፡፡
“ ገበያው ውስጥ የሚኖረው ብድር ትንሽ ነው፣ የተበዳሪ ብዛት ደግሞ ብዙ ነው፡፡ ስለዚህ ባንኮች ያለቻቸውን ትንሽ የብድር ገንዘብ ለጨረታ ያቀርቡዋታል ማለት ነው፡፡ ያለቻቸውን ውስን ብድር ለመስጠት ጠበቅ ያለ መመዘኛ ያስቀምጣሉ፡፡
አንደኛው መመዘኛ የብድር ዋጋ (ወለዱን) ማስወደድ ነው፡፡ ሌላኛው መስፈርት ደግሞ “አስተማማኝ ተበዳሪ ” የሚል ይሆናል፡፡ ብድራቸውን በእርግጠኝነት ይመልሳሉ ለሚባሉ፣ ለተመረጡ ተበዳሪዎች ብቻ ያቀርባሉ፡፡ ይህ ማለት የስጋት መጠኑ ወደ ዜሮ ለተጠጋ ተበዳሪ ነው፡፡ ትንሽ ስጋት ላለበት ተበዳሪ አይሰጡም፡፡ ስጋቱን የምትቀንሰው ለብድር መያዣ በሚቀርበው ዋስትና (ለምሳሌ ቤት ወይም መኪና) ነው፡፡
የቤትና የመኪና ዋስትና ይዘው ከሚመጡ ተበዳሪዎች መካከል፣ የቤት ዋስትና የሚያቀርበው ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡ መሬት ላይ ያለ ነገር ወድቆ አይወድቅም ተብሎ ስለሚታመን ነው፡፡ መኪና ዋጋው እየቀነሰ ስለሚሔድና አደጋዎችም ስለሚኖሩ ከቤት በላይ ተመራጭ ዋስትና ሊሆን አይችልም፡፡ ከዚህ ውጪ ደግሞ፣ የንግድ ፍላጎታቸውን ያያሉ፡፡
ለምሳሌ ዳያስፖራ ለሆኑና በኤክስፖርት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ተበዳሪዎች በውጭ ምንዛሪ ስለሚከፍሉ ቅድሚያ ሊያገኙ ይችላሉ፡፡ ብድሬን በብር እከፍላለኹ የሚለው ተመራጭ አይሆንም፡፡ ባንኮቹ ያላቸው የብድር ገንዘብ ውስን ስለሆነ፣ ከንግድ አንፃር የትኛው ያዋጣናል ይላሉ፣ ጠበቅ ያለ የብድር መመዘኛም ያወጣሉ፡፡ ”
በዚህ ኹኔታ ተጎጂ የሚሆኑት ዘርፎች የትኞቹ ናቸው ?
“ የአምራቹ ዘርፍ የትርፍ ህዳጉ ጠባብ ነው፡፡ እንደ ግብርና እና ማኑፋክቸሪንግ የመሰሉ ዘርፎች በዚህ ውስጥ የሚካተቱ ናቸው፡፡ እነዚህ ብዙ ኢንቨስትመንት ስለማይስቡ ይጎዳሉ፡፡ ይህን ውስን የብድር አቅርቦትን የመሳብ ዕድል አይኖራቸውም፡፡ ሰፊ የትርፍ ህዳግ ያላቸው ቢዝነሶች ግን አሁንም አዋጭ ስለሆኑ ብድር ሊያገኙ ይችላሉ፡፡”
መፍትሔውስ ምንድነው ?
“ የብድር ጣሪያው ገንዘብ እንዳይፈጠር አድርጓል፡፡ ብድር ተሰጥቶ ወለድ ካልተሰበሰበ ገንዘብ አይፈጠርም፣ ባንኮች ተቀማጭ አያገኙም፡፡ የብድር ጣሪያውን ማንሳት ብቻም መፍትሔ ሊሆን አይችልም፡፡ የብድር ጣሪያው ቢነሳም ባንኮች በቂ ብድር ያቀርባሉ ማለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት አለባቸው፡፡ ለእጥረቱ ትልቁ መነሻ የሆነው የቁጠባ አቅም መዳከሙ ነው፡፡ ጥቅል የሀገር ውስጥ ቁጠባ በተከታታይ አመታት እየቀነሰ ነው የመጣው፣ ገንዘብ እየተቆጠበ አይደለም ማለት ነው፡፡ ሌሎች በርካታ ምክንያቶችንም መጥቀስ ቢቻልም፣ የቁጠባ መዳከም የባንኮችን የጥሬ ገንዘብ ክምችት አቅም አዳክሞታል፡፡ ይህ በጣም አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡ ወደ ባንኮች የሚመጣው ተቀማጭ ገንዘብ የቁጠባ ውጤት ነው፡፡ ይህ ካልተስተካከለ ችግር ነው፡፡”
ብሔራዊ ባንክ የባንክ ለባንክ የገንዘብ ግብይት በመፍቀድና፣ ንግድ ባንኮች ከብሔራዊ ባንክ የአጭር ጊዜ ብድር እንዲወስዱ በመፍቀድ፣ ያለባቸውን የገንዘብ እጥረት ለመፍታት እየሰራ ቢሆን፣ ይህ ግን ዘላቂ መፍትሔ አይሆንም ብለዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የብሔራዊ ባንክ፣ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ፣ ባለፈው ሳምንት ሁለተኛ ስብሰባውን በማካሔድ የተለያዩ ምክረ ሀሳቦችን ሰጥቷል፡፡
በኮሚቴው ውሳኔዎ ተፅዕኖ ዙሪያ አስተያየት እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አንድ የፋይናንስ ባለሙያ፣ “ ውሳኔው በስራ ፈጠራና በገቢ ማመንጨት በኩል ዋጋ ያስከፍለናል ” ብለዋል፡፡
በቡና ባንክ ዋና የስትራቴጂ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ሙሉነህ አያሌው በሰጡን የግል አስተያየት፣ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበት እየቀነሰ መምጣቱን እንደገለፀ አውስተው፣ ነገር ግን፣ “ መልሶ ያንሰራራል ” የሚል ስጋት ስላለው፣ ቀድሞ የነበሩትን ገደቦች አላነሳም ይላሉ፡፡
ከኮሚቴው ውሳኔዎች አንዱ፣ ቀደም ሲል በባንኮች የብድር ዕድገት ላይ የተቀመጠው የ18 በመቶ ገደብ በነበረበት እንዲቀጥል የሚያደርግ ነው፡፡ ይህ ውሳኔ የባንኮችን የማበደር ዕድል ይቀንሳል ይላሉ፡፡
ይህን በምሳሌ ሲያስረዱም ፥ “ አንድ ባንክ ባለፈው ሰኔ ወር 2016 ላይ የብድር መጠኑ 100 ቢሊዮን ከደረሰ፣ የሚቀጥለው ሰኔ ላይ 2017 ላይ 118 ቢሊዮን ነው ማድረስ የሚችለው ማለት ነው፡፡ ለዛውም፣ የሰበሰበው ብድር ተቀንሶ፣ ያልሰበሰበው ብድር ተደምሮ ነው እዛ መድረስ አለበት የሚባለው፡፡ በዚህ ስሌት ባንኩ ባለፈው አመት የሰጠው ብድር ብቻ ሳይሆን ከተመሰረተ ጀምሮ የሰጠው ብድርም ሊሆን ይችላል፡፡ እስካልተሰበሰበ ድረስ በብድርነት ይያዛል፡፡ ባንኩ ያልሰበሰበው ነባር ብድርና የሰጠው አዲስ ብድር ተደምሮ ነው የሚሰላው፡፡ በብድር ወለዱ ብቻም ጣሪያው ላይ ሊደርስ ይችላል፡፡ አንድ ባንክ፣ ባለፈው አመት 100 ቢሊዮን ብድር ከነበረውና የዚህ ወለዱ 18 ከመቶ ከሆነ፣ በዚህ አመት ምንም ብድር ሳይሰጥ የአምናው ብድር ብቻውን 118 ቢሊዮን ይሆናል፡፡ ሳያበድርም ሳይሰበስብም ጣሪያውን ሊደርስበት ይችላል ” ብለዋል።
አቶ ሙሉነህ አያሌው የዚህ ተፅዕኖው ምን እንደሆነ እንዲህ ሲሉ አስረድተዋል።
“ ይህ ውሳኔ የኢኮኖሚ ዕድገቱን ያቀዘቅዘዋል፡፡ በስራ እድል ፈጠራ እና በገቢ ማመንጨት በኩል ዋጋ ያስከፍለናል፡፡ የብድር አቅርቦት መኖር፣ ሰዎች ተበድረው ስራ እንዲሰሩና የስራ እድል እንዲፈጥሩ ያበረታታል፡፡ የብድር አቅርቦት ከሌለ ኢንቨስትመንት ይዳከማል፣ የስራ ዕድል አይኖርም፣ ሰዎች ገቢ አያመነጩም ማለት ነው፡፡ ያ ባለመሆኑ ይህንን ዋጋ ነው እየከፈልን ነው ያለነው፡፡ ”
የብድር አቅርቦቱ ውስን ስለሆነ፣ ባንኮች የብድር አሰጣጥ ላይ ጠበቅ ያሉ መስፈርቶችን ይጠቀማሉ ብለዋል፣ ባለሙያው፡፡
እሳቸው እንደሚሉት፣ አንድ እቃ ከገበያ ሲጠፋ፣ አለያም አቅርቦቱ ሲቀንስ ዋጋው እንደሚወደደው፣ የባንኮች ብድርም በተመሳሳይ አቅርቦቱ ሲቀንስ ዋጋው (ወለዱ) ይወደዳል፡፡ አቶ ሙሉነህ ይህን እንዲህ በማለት አብራርተዋል፡፡
“ ገበያው ውስጥ የሚኖረው ብድር ትንሽ ነው፣ የተበዳሪ ብዛት ደግሞ ብዙ ነው፡፡ ስለዚህ ባንኮች ያለቻቸውን ትንሽ የብድር ገንዘብ ለጨረታ ያቀርቡዋታል ማለት ነው፡፡ ያለቻቸውን ውስን ብድር ለመስጠት ጠበቅ ያለ መመዘኛ ያስቀምጣሉ፡፡
አንደኛው መመዘኛ የብድር ዋጋ (ወለዱን) ማስወደድ ነው፡፡ ሌላኛው መስፈርት ደግሞ “አስተማማኝ ተበዳሪ ” የሚል ይሆናል፡፡ ብድራቸውን በእርግጠኝነት ይመልሳሉ ለሚባሉ፣ ለተመረጡ ተበዳሪዎች ብቻ ያቀርባሉ፡፡ ይህ ማለት የስጋት መጠኑ ወደ ዜሮ ለተጠጋ ተበዳሪ ነው፡፡ ትንሽ ስጋት ላለበት ተበዳሪ አይሰጡም፡፡ ስጋቱን የምትቀንሰው ለብድር መያዣ በሚቀርበው ዋስትና (ለምሳሌ ቤት ወይም መኪና) ነው፡፡
የቤትና የመኪና ዋስትና ይዘው ከሚመጡ ተበዳሪዎች መካከል፣ የቤት ዋስትና የሚያቀርበው ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡ መሬት ላይ ያለ ነገር ወድቆ አይወድቅም ተብሎ ስለሚታመን ነው፡፡ መኪና ዋጋው እየቀነሰ ስለሚሔድና አደጋዎችም ስለሚኖሩ ከቤት በላይ ተመራጭ ዋስትና ሊሆን አይችልም፡፡ ከዚህ ውጪ ደግሞ፣ የንግድ ፍላጎታቸውን ያያሉ፡፡
ለምሳሌ ዳያስፖራ ለሆኑና በኤክስፖርት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ተበዳሪዎች በውጭ ምንዛሪ ስለሚከፍሉ ቅድሚያ ሊያገኙ ይችላሉ፡፡ ብድሬን በብር እከፍላለኹ የሚለው ተመራጭ አይሆንም፡፡ ባንኮቹ ያላቸው የብድር ገንዘብ ውስን ስለሆነ፣ ከንግድ አንፃር የትኛው ያዋጣናል ይላሉ፣ ጠበቅ ያለ የብድር መመዘኛም ያወጣሉ፡፡ ”
በዚህ ኹኔታ ተጎጂ የሚሆኑት ዘርፎች የትኞቹ ናቸው ?
“ የአምራቹ ዘርፍ የትርፍ ህዳጉ ጠባብ ነው፡፡ እንደ ግብርና እና ማኑፋክቸሪንግ የመሰሉ ዘርፎች በዚህ ውስጥ የሚካተቱ ናቸው፡፡ እነዚህ ብዙ ኢንቨስትመንት ስለማይስቡ ይጎዳሉ፡፡ ይህን ውስን የብድር አቅርቦትን የመሳብ ዕድል አይኖራቸውም፡፡ ሰፊ የትርፍ ህዳግ ያላቸው ቢዝነሶች ግን አሁንም አዋጭ ስለሆኑ ብድር ሊያገኙ ይችላሉ፡፡”
መፍትሔውስ ምንድነው ?
“ የብድር ጣሪያው ገንዘብ እንዳይፈጠር አድርጓል፡፡ ብድር ተሰጥቶ ወለድ ካልተሰበሰበ ገንዘብ አይፈጠርም፣ ባንኮች ተቀማጭ አያገኙም፡፡ የብድር ጣሪያውን ማንሳት ብቻም መፍትሔ ሊሆን አይችልም፡፡ የብድር ጣሪያው ቢነሳም ባንኮች በቂ ብድር ያቀርባሉ ማለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት አለባቸው፡፡ ለእጥረቱ ትልቁ መነሻ የሆነው የቁጠባ አቅም መዳከሙ ነው፡፡ ጥቅል የሀገር ውስጥ ቁጠባ በተከታታይ አመታት እየቀነሰ ነው የመጣው፣ ገንዘብ እየተቆጠበ አይደለም ማለት ነው፡፡ ሌሎች በርካታ ምክንያቶችንም መጥቀስ ቢቻልም፣ የቁጠባ መዳከም የባንኮችን የጥሬ ገንዘብ ክምችት አቅም አዳክሞታል፡፡ ይህ በጣም አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡ ወደ ባንኮች የሚመጣው ተቀማጭ ገንዘብ የቁጠባ ውጤት ነው፡፡ ይህ ካልተስተካከለ ችግር ነው፡፡”
ብሔራዊ ባንክ የባንክ ለባንክ የገንዘብ ግብይት በመፍቀድና፣ ንግድ ባንኮች ከብሔራዊ ባንክ የአጭር ጊዜ ብድር እንዲወስዱ በመፍቀድ፣ ያለባቸውን የገንዘብ እጥረት ለመፍታት እየሰራ ቢሆን፣ ይህ ግን ዘላቂ መፍትሔ አይሆንም ብለዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ወደ ቀድሞው ካምፓኒ ሊመልሱን ነው። መንግስት በፍጥነት የማያስወጣን ከሆነ ላለመመለሳችን ምንም ዋስትና የለንም " - ከ730 በላይ ዜጎች በማይናማር
በማይናማር በታገቱበት ወቅት ሲሰሩት የነበረውን አስከፊ ስራ እንዲያቆሙ ተደርገው ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ከወር በላይ የመንግስትን ምላሽ ሲጠባበቁ የነበሩ ከ730 በላይ ኢትዮጵያውያን ቀድሞ ወደነበሩበት የእገታ ቦታ ሊወሰዱ በመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ኢትዮጵያውያኑ ዛሬስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ?
“ወደ ሀገራችን ለመውጣት ዛሬ ነገ እያልን ወደ ካምፓኒ ተመለሱ ተባልን።
ከመጥፎው ስራ አውጥተውን የነበሩት ሚሊታሪዎቹ 'መንግስታችሁ የማይፈልጋችሁ ከሆነ ወደ ቀድሞው ካምፓኒ ተመለሱ፣ እናንተን ቁጭ አድርገን የምንመግበው የለንም' ብለውናል።
የኢትዮጵያ መንግስት እኛን የመመለስ አቅም የለውም ወይ? መልሱ አዎ ከሆነ ተመልሰን እዛ ከምንገባ እዚሁ እራሳችንን እናጠፋለን የመጨረሻ አማራጫችን እሱ ነው። ዛሬ ተስፋ ቆርጠናል፤ ጭንቀታችን በርትቷል ስለዚህ መልስ እንፈልጋለን።
ተገደን የማጭበርበር ስራ የነበርንና በሚሊተሪ ድጋፍ ነጻ የወጣን 735 ኢትዮጵያውያን በማይናማር ሁለት ሚሊተሪ ካምፖች ሆነን የሀገራችን ምላሽና የማጓጓዝ ስራ በመጠበቅ ሁለተኛ ወራችን እያገባደድን ነው።
ይህም ከካምፓኒ ለመውጣት ስንጠየቅ ከነበረው 5000 ዶላር ነጻ ያደረገንና የኢትዮጵያ መንግስትም ስካም ፓርኮቹ ድረስ ገብቶ ዜጎቹን ለማውጣት ተፈጥሮበት የነበረውን ፈተና ያቀለለ ምቹ አጋጣሚ ነበር።
በቆየንባቸው የሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የወላጆች ኮሚቴ ሂደቱ እየተሰራበት እንደሆነ በሚደርሱን መረጃዎች እየተጽናናን ቆይተናል።
በቆይታችን ሚሊተሪው የተያዘውን ምግብ ቢያቀርብም ከሃይማኖታችንና ከሀገራችን የአመጋገብ ባህል ጋር ፈጽሞ የማይሄድ በመሆኑ በውድ ዋጋ በሽያጭ የሚያቀርቧቸውን ምግቦች እየገዛን እንጠቀም ነበር።
አሁን ግን ሁላችንም እጃችን ላይ የነበረንን ገንዘብ ጨርሰን ምግብና መድኃኒት ምንገዛበት የሌለን በመሆኑ ለረሃብና ለጤና ችግር ተጋልጠናል።
ከቀዶ ጥገና ተደርጎላቸው ማገገም ያልቻሉ፤ በተፈጥሮ አደጋው ተጎድተው ደም አሁንም የሚፈሳቸው፤ በአንጀትና አንገት ህመሞች ራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ ማይችሉ ህሙማን ባሉበት ህክምና በማይገኝበት ጠረፍ ላይ መሆናችን ከዚህ እንድንወጣ ለሚዲያዎችና ለመንግሥት ተቋማት እያሳወቅን የቆየን መሆኑም ይታወቃል።
ይህ ሁሉ ችግር ያልፋል ብለን በኢትዮጵያ መንግስት እና ኢምባሲዎቹ እየተሰሩ ያሉ እኛን የመመለስ ስራ በተስፋ እየጠበቅን ባለንበት ወቅት ሁላችንንም ያስደነገጠ እና ተስፋችን የቀማን ችግር ተከስቷል።
ከአረመኔያዊ አያያዝ አውጥቶ ካምፕ ውስጥ ያስገባን ሚሊተሪ የሀገራችን ምላሽ እየተጠባበቀ ቢቆይም በኢትዮጵያ መንግስትና በኤምባሲዎች የሚሰራው እኛን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ እጅጉን ስለተጓተተ፣ ከ29 ሀገራት ዜጎች እኛ ብቻ በመቅረታችን ሚሊተሪው በኢትዮጵያ መንግሥት ተስፋ ቆርጦ ወደ ካምፓኒዎች እንደሰንመለስ እያዋከበን ነው።
ይህም በብዙዎቻችን ላይ ትልቅ ሽብርና መደናገጥ የፈጠረ አደገኛ ክስተት ሆኖ ለጭንቀት ዳርጎናል።
በመሆኑም፣ ሚዲያዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ኤምባሲዎች ለዚህ አደገኛ ሂደት ፈጣን ምላሽ በመስጠት ወደ ሀገራችን መመለስ ካልቻሉ መመለስ የማንችለው የ735 ወጣቶች ህይወት አደጋ ውስጥ እየገባ እንደሆነ ለማሳወቅ እንፈልጋለን” ሲሉ ተማጽነዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በማይናማር በታገቱበት ወቅት ሲሰሩት የነበረውን አስከፊ ስራ እንዲያቆሙ ተደርገው ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ከወር በላይ የመንግስትን ምላሽ ሲጠባበቁ የነበሩ ከ730 በላይ ኢትዮጵያውያን ቀድሞ ወደነበሩበት የእገታ ቦታ ሊወሰዱ በመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ኢትዮጵያውያኑ ዛሬስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ?
“ወደ ሀገራችን ለመውጣት ዛሬ ነገ እያልን ወደ ካምፓኒ ተመለሱ ተባልን።
ከመጥፎው ስራ አውጥተውን የነበሩት ሚሊታሪዎቹ 'መንግስታችሁ የማይፈልጋችሁ ከሆነ ወደ ቀድሞው ካምፓኒ ተመለሱ፣ እናንተን ቁጭ አድርገን የምንመግበው የለንም' ብለውናል።
የኢትዮጵያ መንግስት እኛን የመመለስ አቅም የለውም ወይ? መልሱ አዎ ከሆነ ተመልሰን እዛ ከምንገባ እዚሁ እራሳችንን እናጠፋለን የመጨረሻ አማራጫችን እሱ ነው። ዛሬ ተስፋ ቆርጠናል፤ ጭንቀታችን በርትቷል ስለዚህ መልስ እንፈልጋለን።
ተገደን የማጭበርበር ስራ የነበርንና በሚሊተሪ ድጋፍ ነጻ የወጣን 735 ኢትዮጵያውያን በማይናማር ሁለት ሚሊተሪ ካምፖች ሆነን የሀገራችን ምላሽና የማጓጓዝ ስራ በመጠበቅ ሁለተኛ ወራችን እያገባደድን ነው።
ይህም ከካምፓኒ ለመውጣት ስንጠየቅ ከነበረው 5000 ዶላር ነጻ ያደረገንና የኢትዮጵያ መንግስትም ስካም ፓርኮቹ ድረስ ገብቶ ዜጎቹን ለማውጣት ተፈጥሮበት የነበረውን ፈተና ያቀለለ ምቹ አጋጣሚ ነበር።
በቆየንባቸው የሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የወላጆች ኮሚቴ ሂደቱ እየተሰራበት እንደሆነ በሚደርሱን መረጃዎች እየተጽናናን ቆይተናል።
በቆይታችን ሚሊተሪው የተያዘውን ምግብ ቢያቀርብም ከሃይማኖታችንና ከሀገራችን የአመጋገብ ባህል ጋር ፈጽሞ የማይሄድ በመሆኑ በውድ ዋጋ በሽያጭ የሚያቀርቧቸውን ምግቦች እየገዛን እንጠቀም ነበር።
አሁን ግን ሁላችንም እጃችን ላይ የነበረንን ገንዘብ ጨርሰን ምግብና መድኃኒት ምንገዛበት የሌለን በመሆኑ ለረሃብና ለጤና ችግር ተጋልጠናል።
ከቀዶ ጥገና ተደርጎላቸው ማገገም ያልቻሉ፤ በተፈጥሮ አደጋው ተጎድተው ደም አሁንም የሚፈሳቸው፤ በአንጀትና አንገት ህመሞች ራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ ማይችሉ ህሙማን ባሉበት ህክምና በማይገኝበት ጠረፍ ላይ መሆናችን ከዚህ እንድንወጣ ለሚዲያዎችና ለመንግሥት ተቋማት እያሳወቅን የቆየን መሆኑም ይታወቃል።
ይህ ሁሉ ችግር ያልፋል ብለን በኢትዮጵያ መንግስት እና ኢምባሲዎቹ እየተሰሩ ያሉ እኛን የመመለስ ስራ በተስፋ እየጠበቅን ባለንበት ወቅት ሁላችንንም ያስደነገጠ እና ተስፋችን የቀማን ችግር ተከስቷል።
ከአረመኔያዊ አያያዝ አውጥቶ ካምፕ ውስጥ ያስገባን ሚሊተሪ የሀገራችን ምላሽ እየተጠባበቀ ቢቆይም በኢትዮጵያ መንግስትና በኤምባሲዎች የሚሰራው እኛን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ እጅጉን ስለተጓተተ፣ ከ29 ሀገራት ዜጎች እኛ ብቻ በመቅረታችን ሚሊተሪው በኢትዮጵያ መንግሥት ተስፋ ቆርጦ ወደ ካምፓኒዎች እንደሰንመለስ እያዋከበን ነው።
ይህም በብዙዎቻችን ላይ ትልቅ ሽብርና መደናገጥ የፈጠረ አደገኛ ክስተት ሆኖ ለጭንቀት ዳርጎናል።
በመሆኑም፣ ሚዲያዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ኤምባሲዎች ለዚህ አደገኛ ሂደት ፈጣን ምላሽ በመስጠት ወደ ሀገራችን መመለስ ካልቻሉ መመለስ የማንችለው የ735 ወጣቶች ህይወት አደጋ ውስጥ እየገባ እንደሆነ ለማሳወቅ እንፈልጋለን” ሲሉ ተማጽነዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" 10ኛ ክፍል ላይ ሀገር አቀፍ ፈተና ሳይወስዱ ወደ 11 የተዘዋወሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ትምህርት ሊሰጣቸው ይገባል፣ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል " - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር በየጊዜው በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ተከትሎ አካሄድኩት ባለው እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ጥናት ዘርፈ ብዙ ችግሮች መገኘታቸውን ገልጿል።
የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ከተካሄደ በኋላ ትምህርት ቤቶች ማስተማር ከሚችሉት በላይ ተማሪዎችን ያስተምራሉ ያለ ሲሆን ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረውን ፈተና በመቅረቱ ሳይፈተኑ 11ኛ ክፍል መግባታቸው ለችግሩ ዋና ተጠቃሽ ምክንያት መሆኑን አመላክቷል።
በትምህርት ቤቶች በሚሰጠው የሞዴል ፈተና እና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው የሀገር አቀፍ ፈተና ሰፊ ልዩነት እንዳለውም ገልጿል።
" በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መካከል የማለፍ ንፅፅር ሲታይ ልዩነት አለ " ያለው ሚኒስቴሩ " የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ ተቋም ይገባሉ፣ ይሁን እንጂ በቂ አይደለም፣ ብዙ ነገሮች መሻሻል እንዳለባቸው ጥናቱ አሳይቶናል " ብሏል።
ጥናቱ ምን አይነት የትምህርት ዘርፍ ችግር ነው ይሄን ያክል ውድቀት ያመጣብን ፣ ከተማሪዎች መውደቅ እና ማለፍ ጋር ተያይዞ የትምህርቱ ባህሪ ምንድን ነው የሚለውን እና በአጠቃላይ በትምህርት ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን የያዘ ነው።
በሁሉም የትምህርት ዘርፍ ላይ ያሉ ችግሮችን ያሳየው ይሄ ጥናት በመጨረሻም የመፍትሄ ሃሳቦችንም አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ምን የመፍትሄ ሃሳብ አቀረበ ?
" ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ላይ ይሰጥ የነበረውን ሀገራዊ ፈተና ሳይወስዱ 11ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ፕሮግራም ያስፈልጋቸዋል። ይሄ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል ፣ ምክንያቱ የሚፈለገውን ያህል እውቀት እና ክህሎት ይዘው አይወጡም።
በገጠር በተለይም በአርብቶ አደሮች አካባቢዎች ላይ ያለው የትምህርት ዘርፍ ልማት አነስተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እጅግ ወደ ኋላ እየቀረ ስለሆነ ማካካሻ መሰራት አለበት።
ሌላው ደግሞ ከትምህርት አመራር፣ መምህራን እና ከአቅም ግንባታ ጋር ተያይዞ ያሉ ጉዳዮች ውጤት በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ ብቻ ትኩረት ተደረጎ የትምህርት አመራሩ አቅም እስካልሰጠ ችግሮቹ ይቀጥላሉ።
ለመምህራን የደመወዝ ጭማሪ ብቻ ሳይሆን መምህሮችን የሚያቅፍ የ insensitive package እስካልመጣ ድረስ ችግሮቹ ይባባሳሉ።
በተጨማሪም በሀብት ክፍፍል ላይ ክፍተት በመኖሩ በትምህርት ዘርፉ ልማት ላይ ተግዳሮት መኖሩን ያሳያል፣ ይሄም መፈታት አለበት " ሲል መፍትሄ ያለውን ሃሳብ አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ጥናቱን ባቀረበበት ወቅት የህዝብ ተወካዮች የተለያዩ አስተያየቶች፣ ጥያቄዎች እና ሃሳቦችን አቅርበዋል።
በጥናቱ ላይ የመፍትሄ ሃሳቦች መቅረባቸው ጥሩ ሁነው ሳለ እንደዚሁ ተወርተው መሬት ላይ ሳይወርዱ ከቀሩ ትርጉም አልባ ናቸው፣ በመሆኑም ሁሉም በአፅንኦት ሊመለከተው እንደሚገባ በተወካዮች ተጠቁሟል።
ከ1 እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚደረገው ድጋፍ አነስተኛ ነው፣ ይሄም አሁን ላለንበት ውጤት ማጣት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል ፤ በጥናቱስ ላይ ለምን ይሄ ሳይካተት ቀረ፣ ምክንያቱም የትምህርት መሰረቱ ከታች ጀምሮ ስለሆነ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስቷል።
የተለያዩ ተማሪዎች በህገወጥ መንገድ ወደተለያዩ ሀገሮች እየተሰደዱ ነው፣ ተማሪዎች ይሄ ሲፈጠር ተረጋግተው መማር እየቻሉ አይደለም፣ ትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር በየጊዜው በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ተከትሎ አካሄድኩት ባለው እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ጥናት ዘርፈ ብዙ ችግሮች መገኘታቸውን ገልጿል።
የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ከተካሄደ በኋላ ትምህርት ቤቶች ማስተማር ከሚችሉት በላይ ተማሪዎችን ያስተምራሉ ያለ ሲሆን ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረውን ፈተና በመቅረቱ ሳይፈተኑ 11ኛ ክፍል መግባታቸው ለችግሩ ዋና ተጠቃሽ ምክንያት መሆኑን አመላክቷል።
በትምህርት ቤቶች በሚሰጠው የሞዴል ፈተና እና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው የሀገር አቀፍ ፈተና ሰፊ ልዩነት እንዳለውም ገልጿል።
" በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መካከል የማለፍ ንፅፅር ሲታይ ልዩነት አለ " ያለው ሚኒስቴሩ " የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት በማምጣት ወደ ከፍተኛ ተቋም ይገባሉ፣ ይሁን እንጂ በቂ አይደለም፣ ብዙ ነገሮች መሻሻል እንዳለባቸው ጥናቱ አሳይቶናል " ብሏል።
ጥናቱ ምን አይነት የትምህርት ዘርፍ ችግር ነው ይሄን ያክል ውድቀት ያመጣብን ፣ ከተማሪዎች መውደቅ እና ማለፍ ጋር ተያይዞ የትምህርቱ ባህሪ ምንድን ነው የሚለውን እና በአጠቃላይ በትምህርት ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን የያዘ ነው።
በሁሉም የትምህርት ዘርፍ ላይ ያሉ ችግሮችን ያሳየው ይሄ ጥናት በመጨረሻም የመፍትሄ ሃሳቦችንም አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ምን የመፍትሄ ሃሳብ አቀረበ ?
" ከዚህ በፊት 10ኛ ክፍል ላይ ይሰጥ የነበረውን ሀገራዊ ፈተና ሳይወስዱ 11ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ልዩ የማካካሻ ፕሮግራም ያስፈልጋቸዋል። ይሄ ካልሆነ ግን መውደቅ ይቀጥላል ፣ ምክንያቱ የሚፈለገውን ያህል እውቀት እና ክህሎት ይዘው አይወጡም።
በገጠር በተለይም በአርብቶ አደሮች አካባቢዎች ላይ ያለው የትምህርት ዘርፍ ልማት አነስተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እጅግ ወደ ኋላ እየቀረ ስለሆነ ማካካሻ መሰራት አለበት።
ሌላው ደግሞ ከትምህርት አመራር፣ መምህራን እና ከአቅም ግንባታ ጋር ተያይዞ ያሉ ጉዳዮች ውጤት በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ ብቻ ትኩረት ተደረጎ የትምህርት አመራሩ አቅም እስካልሰጠ ችግሮቹ ይቀጥላሉ።
ለመምህራን የደመወዝ ጭማሪ ብቻ ሳይሆን መምህሮችን የሚያቅፍ የ insensitive package እስካልመጣ ድረስ ችግሮቹ ይባባሳሉ።
በተጨማሪም በሀብት ክፍፍል ላይ ክፍተት በመኖሩ በትምህርት ዘርፉ ልማት ላይ ተግዳሮት መኖሩን ያሳያል፣ ይሄም መፈታት አለበት " ሲል መፍትሄ ያለውን ሃሳብ አቅርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ጥናቱን ባቀረበበት ወቅት የህዝብ ተወካዮች የተለያዩ አስተያየቶች፣ ጥያቄዎች እና ሃሳቦችን አቅርበዋል።
በጥናቱ ላይ የመፍትሄ ሃሳቦች መቅረባቸው ጥሩ ሁነው ሳለ እንደዚሁ ተወርተው መሬት ላይ ሳይወርዱ ከቀሩ ትርጉም አልባ ናቸው፣ በመሆኑም ሁሉም በአፅንኦት ሊመለከተው እንደሚገባ በተወካዮች ተጠቁሟል።
ከ1 እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚደረገው ድጋፍ አነስተኛ ነው፣ ይሄም አሁን ላለንበት ውጤት ማጣት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል ፤ በጥናቱስ ላይ ለምን ይሄ ሳይካተት ቀረ፣ ምክንያቱም የትምህርት መሰረቱ ከታች ጀምሮ ስለሆነ የሚሉ ጥያቄዎች ተነስቷል።
የተለያዩ ተማሪዎች በህገወጥ መንገድ ወደተለያዩ ሀገሮች እየተሰደዱ ነው፣ ተማሪዎች ይሄ ሲፈጠር ተረጋግተው መማር እየቻሉ አይደለም፣ ትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ በታጣቂዎች በኩል በዚህን ቀን እንመጣለን የሚል ምላሽ የለም። ግን ልዑካናቸውን እንደሚልኩ ተስፋ እናደርጋለን ” - ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ እንደሚካሄድ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
በዚህም፣ በክልሉ 4,480 ተሳታፊዎች በባሕር ዳር ከተማ ለሦስት ቀናት እንደሚመክሩ፣ ሂደቱ በተለያዩ ሁነቶች እስከ ሚያዚያ 6/2017 ዓ/ም እንደሚቆይ ገልጿል።
በቦታው የተገኘው ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች በምክክሩ ለመሳተፍ ይሁንታ አቅርበዋል ? ሲል ለኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ጥያቄ አቅርቧል።
ኮሚሽነር ዮናስ (ዶ/ር) ምን መለሱ?
“ በታጣቂዎች በኩል በዚህን ቀን እንመጣለን የሚል ምላሽ የለም። ግን ልዑካናቸውን እንደሚልኩ ተስፋ እናደርጋለን ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
አክለው፣ “ ልዑካን ቡድን እንዲልኩ ጥሪ አቅርበናል። አሁንም ጥሪ እናቀርባለን። ካቀረቡ ድምፃቸውን ሰምተን ጥያቄዎቻቸውን አድምጠን ለሚመለከተው እናቀርባለን ” ብለዋል።
“ ትጥቅ እንዲፈቱ አንጠይቃቸውም። ከጠየቅንም ስህተት ነው። እኛ አማካሪዎች፤ አባቶች ነን። ትጥቅ የማስፈታት ሥራው የመንግስት ነው ” ሲሉም ተናግረዋል።
በተጨማሪም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ እናትን ጨምሮ የተወሰኑ ፓርቲዎች “መጀመሪያ ጦርነቱ መቆም አለበት” በሚል እሳቤ በክልሉ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት እንደማይሳተፉ ለኮሚሽኑ አሳውቀው ነበር፤ ከዚያ ወዲህ ተነጋገራችሁ? አሁን ይሳተፋሉ? ሲል ኮሚሽነሩን ጠይቋል።
ኮሚሽነር ዮናስ (ዶ/ር)፣ “የተለዬ ለውጥ አላገኘንም። ነገር ግን ያለን አቋም በጣም አዎንታዊ ነው። ምክንያቱም እነዚህ ወገኖቻችን እንዴት እንደሚያግዙን እኔ ምስክር ነኝ። በተለይ በአዲስ አበባው ላይ ስናካሂድ በጣም ደጋፊዎቻችን የነበሩ ሰዎች ናቸው” ሲሉ መልሰዋል።
“ ሀሳባቸው ረድቶናል። ዛሬም ያ ሀሳባቸው አይቋረጥም የሚል እምነት አለን እንደ ኢትዮጵያውያን። ይሄኮ የቤተሰብ ፀብ ነው። ስለዚህ እነርሱም ተመልሰው አሁን እንደቀድሞው እንተባበራለን የሚል እምነት አለን ” ነው ያሉት።
ኮሚሽር መላኩ ወ/ማርያም ምን አሉ ?
በክልሉ የጸጥታ ችግር ከመኖሩ አንጻር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ምን እንደነበር ከጋዜጠኞች ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም ደግሞ፣ “ የተለያዩ ማህበረሰቦች ያለመሸማቀቅና ፍርሃት፤ ፋኖዎች ምናልባት ከማያነሱት በላይ ” ጥያቄዎች እንዳነሱ ገልጸዋል።
“ ህዝቡ የሚያውቅ፣ የሚረዳ፣ ዲሲፕሊንድ ህዝብ ነው። አገሩን የሚወድ ህዝብ ነው። ልዩነት የሚያደርግ አይደለም። ለሌላውም የሚያሳስበው ነው” ብለው፣ “ የተወካዮች ልየታ የተካሄደው ልክ በሌላ አካባቢ እንደተካሄደው ነው ልዩነት የለውም ” ሲሉም ተደምጠዋል።
በክልሉ 263 ወረዳዎች የተሳታፊ ልዬታ እንዳካሄዱ፣ አራት ወረዳዎች እንዳላካሄዱ ገልጸው፣ የአራቱን ወረዳዎች ስም ዝርዝር ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ከ10 ዩኒቨርሲቲዎች 26 መምህራን፣ 2, 232 ተባባሪ አካላትን (385ቱ ሴቶች ናቸው) እንዳሰለጠኑ የተናገሩት ኮሚሽነሩ፣ “በተሳታፊ ልየታ ረገድ ደግሞ 13,900 ወንዶች፣ 5,698 ሴቶች፣ በድምሩ 19,598 ሰዎች በዚህ ሂደት እንዲያልፉ ተደርጓል” ብለዋል።
አክለውም፣ “መላውን አማራኔ ያካለለ ነው ማለት ነው። የቀሩት አራት ወረዳዎች ናቸው በታወቀ ምክንያት” ነው ያሉት።
ኮሚሽነሩ፣ "የሴቶች ተሳትፎ 30.3%፣ አካል ጉዳተኞች ተሳትፎ 5.7፣ የተገለሉ ሰዎች ተሳትፎ 4%፣ የውስጥ ተፈናቃዮች 6.9% ነው" ሲሉም አስረድተዋል።
"የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ሸኔ፣ ፋኖ ምንድን ነው የሚፈልጉት? አዲስ የፓለቲካ ስርዓት እንገንባ፣ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እናምጣ፣ እኩልነትና ነጻነት የሰፈነበት አገር እናድርግ ቁጭ ብለን ተነጋግረን። እዚህ ውጪ ምንድን ነው የሚፈለገው?" ሲሉ ጠይቀዋል።
"መንግስትም ሌሎችም በጠመንጃ የሚያሳኩት ነገር የለም። ሊያሳኩም አይችሉም" ሲሉም ተደምጠዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከነገ ጀምሮ በአማራ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ እንደሚካሄድ ዛሬ በባህር ዳር ከተማ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
በዚህም፣ በክልሉ 4,480 ተሳታፊዎች በባሕር ዳር ከተማ ለሦስት ቀናት እንደሚመክሩ፣ ሂደቱ በተለያዩ ሁነቶች እስከ ሚያዚያ 6/2017 ዓ/ም እንደሚቆይ ገልጿል።
በቦታው የተገኘው ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች በምክክሩ ለመሳተፍ ይሁንታ አቅርበዋል ? ሲል ለኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ጥያቄ አቅርቧል።
ኮሚሽነር ዮናስ (ዶ/ር) ምን መለሱ?
“ በታጣቂዎች በኩል በዚህን ቀን እንመጣለን የሚል ምላሽ የለም። ግን ልዑካናቸውን እንደሚልኩ ተስፋ እናደርጋለን ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
አክለው፣ “ ልዑካን ቡድን እንዲልኩ ጥሪ አቅርበናል። አሁንም ጥሪ እናቀርባለን። ካቀረቡ ድምፃቸውን ሰምተን ጥያቄዎቻቸውን አድምጠን ለሚመለከተው እናቀርባለን ” ብለዋል።
“ ትጥቅ እንዲፈቱ አንጠይቃቸውም። ከጠየቅንም ስህተት ነው። እኛ አማካሪዎች፤ አባቶች ነን። ትጥቅ የማስፈታት ሥራው የመንግስት ነው ” ሲሉም ተናግረዋል።
በተጨማሪም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ እናትን ጨምሮ የተወሰኑ ፓርቲዎች “መጀመሪያ ጦርነቱ መቆም አለበት” በሚል እሳቤ በክልሉ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት እንደማይሳተፉ ለኮሚሽኑ አሳውቀው ነበር፤ ከዚያ ወዲህ ተነጋገራችሁ? አሁን ይሳተፋሉ? ሲል ኮሚሽነሩን ጠይቋል።
ኮሚሽነር ዮናስ (ዶ/ር)፣ “የተለዬ ለውጥ አላገኘንም። ነገር ግን ያለን አቋም በጣም አዎንታዊ ነው። ምክንያቱም እነዚህ ወገኖቻችን እንዴት እንደሚያግዙን እኔ ምስክር ነኝ። በተለይ በአዲስ አበባው ላይ ስናካሂድ በጣም ደጋፊዎቻችን የነበሩ ሰዎች ናቸው” ሲሉ መልሰዋል።
“ ሀሳባቸው ረድቶናል። ዛሬም ያ ሀሳባቸው አይቋረጥም የሚል እምነት አለን እንደ ኢትዮጵያውያን። ይሄኮ የቤተሰብ ፀብ ነው። ስለዚህ እነርሱም ተመልሰው አሁን እንደቀድሞው እንተባበራለን የሚል እምነት አለን ” ነው ያሉት።
ኮሚሽር መላኩ ወ/ማርያም ምን አሉ ?
በክልሉ የጸጥታ ችግር ከመኖሩ አንጻር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ምን እንደነበር ከጋዜጠኞች ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም ደግሞ፣ “ የተለያዩ ማህበረሰቦች ያለመሸማቀቅና ፍርሃት፤ ፋኖዎች ምናልባት ከማያነሱት በላይ ” ጥያቄዎች እንዳነሱ ገልጸዋል።
“ ህዝቡ የሚያውቅ፣ የሚረዳ፣ ዲሲፕሊንድ ህዝብ ነው። አገሩን የሚወድ ህዝብ ነው። ልዩነት የሚያደርግ አይደለም። ለሌላውም የሚያሳስበው ነው” ብለው፣ “ የተወካዮች ልየታ የተካሄደው ልክ በሌላ አካባቢ እንደተካሄደው ነው ልዩነት የለውም ” ሲሉም ተደምጠዋል።
በክልሉ 263 ወረዳዎች የተሳታፊ ልዬታ እንዳካሄዱ፣ አራት ወረዳዎች እንዳላካሄዱ ገልጸው፣ የአራቱን ወረዳዎች ስም ዝርዝር ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ከ10 ዩኒቨርሲቲዎች 26 መምህራን፣ 2, 232 ተባባሪ አካላትን (385ቱ ሴቶች ናቸው) እንዳሰለጠኑ የተናገሩት ኮሚሽነሩ፣ “በተሳታፊ ልየታ ረገድ ደግሞ 13,900 ወንዶች፣ 5,698 ሴቶች፣ በድምሩ 19,598 ሰዎች በዚህ ሂደት እንዲያልፉ ተደርጓል” ብለዋል።
አክለውም፣ “መላውን አማራኔ ያካለለ ነው ማለት ነው። የቀሩት አራት ወረዳዎች ናቸው በታወቀ ምክንያት” ነው ያሉት።
ኮሚሽነሩ፣ "የሴቶች ተሳትፎ 30.3%፣ አካል ጉዳተኞች ተሳትፎ 5.7፣ የተገለሉ ሰዎች ተሳትፎ 4%፣ የውስጥ ተፈናቃዮች 6.9% ነው" ሲሉም አስረድተዋል።
"የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ሸኔ፣ ፋኖ ምንድን ነው የሚፈልጉት? አዲስ የፓለቲካ ስርዓት እንገንባ፣ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እናምጣ፣ እኩልነትና ነጻነት የሰፈነበት አገር እናድርግ ቁጭ ብለን ተነጋግረን። እዚህ ውጪ ምንድን ነው የሚፈለገው?" ሲሉ ጠይቀዋል።
"መንግስትም ሌሎችም በጠመንጃ የሚያሳኩት ነገር የለም። ሊያሳኩም አይችሉም" ሲሉም ተደምጠዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
“ ተደብቆ የተገኘ አሽከርካሪ እስከ 500 ሺሕ ብርና ሦስት አመት እስራት እንዲቀጣ የተቀመጠ ዐዋጅ አለ። ይሄ አግባብ አይደለም ” - ማኀበሩ
አሽከርካሪዎችን በተመለከተ የሚወጡ ህጎች አሳታፊነት የጎደላቸውና አሽከርካሪዎች ሥራ እንዲያቆሙ የሚያደርጉ በመሆናቸው ሊጤኑ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር አሳሰበ።
ግብዓት የሚያጓጓዙ ሹፌሮች በጸጥታ ችግር መንገድ ላይ በሚጉላሉበት፣ የሚጓጓዙበት ሪዘርቭ ነዳጅ እንዳይጭኑ በሚከለከሉበት ሁኔታ በአራትና አምስት ቀናት ከጂቡቲ ወደ መሀል ሀገር ካልደረሱ እስከ 500 ሺሕ ብር የተጣለባቸውን ቅጣት ማኀበሩ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ተቃውሟል።
ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አለ?
የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ዘውዱ፥ “ ህግ ሲወጣ አሳትፉን ብለን ለነዳጅና ኢነርጅ ባለስልጣን በተደጋጋሚ ደብዳቤ አስገብተን ሊያነጋግሩን ፈቃደኞች አይደሉም።
ህግ ሲወጣ ማህበሩ መሳተፍ አለበት። የሚጎዱና ተደራራቢ ህጎችን በማውጣት አሽከርካሪዎች ከስራ እንዲፈናቀሉ እንጅ ህግ እንዲከበር አያደርግም። ያሽከርካሪን ችግር ሳያዳምጡ ህግ ማውጣቱን ማህበሩ አይቀበለውም።
ወንጀለኛ ከሆኑ አሽከርካሪዎች አይያዙ የሚል አመለካከት የለውም ማህበሩ። ግን አሰራሩ ሙሉ ለሙሉ ለሹፌሮች ብቻ እየተደረገ ባሽከርካሪዎች የመስራት ፍላጎት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያስከተለ ነው።
ሹፌሮች ረጅም መንገድ በሚጓዙበት ወቅት ለሚጓጓዙበት የሚሆን ሪዘርቭ ነዳጅ በታንከራቸው ይጭናሉ፤ ግን ከተሳቢ ታንከር ወደ ፊተኛው መኪና ሽፍት ሲያረጉ‘ነዳጅ እየቀሸብክ ነው; ተብሎ የሚያዙበት አጋጣሚ እየተፈጠረ ነው። ይሄ ትክክል አይደለም።
ከጅቡቲ ሞያሌ የሚሄድ አሽከርካሪ ሪዘርብ ነዳጅ ካልያዘ መንደር ላይ ሊያጣ ይችላል። ባሁኑ ወቅታዊ ሁኔታ ነዳጅ በየቦታው አይገኝም። ስለዚህ ሹፌርን ሆን ተብሎ ለመበደል ምክንያት እየተፈለገ ነው ” ብለዋል።
ሌላኛው የማኀበሩ አመራር ምን አሉ ?
“ አንድ አሽከርካሪ ነዳጅ ከጅቡቲ አድስ አበባ ከጫነ በአራት ቀን መድረስ አለበት ተብሏል። ካልደረሰ 480 ሺሕ ብር፣ ተደብቆ የተገኘ እስከ 500 ሺሕ ብር የሚያስቀጣ መሆኑን ወስነዋል። ከ300 ሺሕ እሰከ 500 ሺሕ ነው ቅጣቱ። ግን ሪዘርቭ ነዳጅ እንዳይያዝም ከልክለዋል።
አንድ አሽከርካሪ በዋና ታከሩ የያዘው ነዳጅ አያደርሰውም እየተጓዘ ነዳጅ ካቋረጠው ወረፋ ይዞ እንደማንኛውም ደረቅ ጭነት የጫነ ተሽከርካሪ ተሰልፎ ነው የሚቀዳው፤ ከወረፋ መካከል አውጥተው ‘ተደብቆ የተገኘ ሹፌር ይዘናል’ ተብሎ ለሚዲያ ፍጆታ ይቀርባል።
የነዳጅ ጫኚ መኪና የሚቀዳበት የተለየ ማደያ የለም። ይሄ በሌለበት በዛ ቀን አልደረስከም ተብሎ መያዝ፣ ካገኙት ማደያ እንኳ ሪዘርቭ ይዘው ሲሄዱ ሪዘርቩን ሲያገላብጥ ‘እየቀሸበ ነው’ ተብሎ መጠየቁ አሽከርካሪውን ስራ ወደ ማቆም እያደረሰ ነው።
በጣም አስቸጋሪ ደረጃ እየደረስን ነው። ባሽከርካሪ ጉዳይ የሚወጣ ህግ ካለ ቀድመን በመሳተፍ የህጉ የግብአት አካል መሆን አለብን።
ነዳጂና ኢነርጂ ባለስልጣንን ጠይቀን፤ ‘አናስገባም’ አሉን በፅሑፍ አምጡ ተባልን በእጅ ፅሑፍ ሀሳባችንን ገለጽን፤ ነገር ግን ‘ሌላ አካል ስላነጋገርን አናነጋግርም’ የሚል መልስ ሰጡን፤ ሕጋዊ ደብዳቤም ፅፈን አስገባን አሁንም የተሰጠን የፅሑፍም ሆነ የቃል መልስ የለም።
ለንግድና ቀጠናዊ ትስስርም ደብዳቤ አስገባን። ፕሮግራም ተይዞልን ህጉ በነጋሪት ጋዜጣ ከመታወጁ በፊት ንግግር እናድርግ ብለን ሄደን ጠየቅን፤ ግን የሚያነጋግረን አጣን። ሕጉ በነጋሪት ጋዜጣ ታወጀ ወደ ተግባር ገባ።
ሹፌር እንደማንኛውም ሙያ እኩል ነው እንዲባልና የሙያውን ዋጋ እንዲሰጠው ነው የምንሰራው። በተደራጀን ቁጥር ወደ መገፋት እየመጣን ነው። ማህበሩ ባይኖር በአንድ ቀን ስራ ሊቆም ይችላል። ሀሳባችነን ስናቀርብ ተደማጭነት ካጣን ምን እናደርጋለን።
ኮማድ ፖስት ባለበት ከጅቡቲ ነዳጅ የሚጭኑ ሹፌሮች በአራት ቀናት አዲስ አበባ ሊደርሱ አይችሉም። ሰዓቱን እንኳ ለመሸፈን ሪዘርቭ ነዳጅ እንዳይዙ ከተከለከለ በምን ሊደርሱ ይችላሉ? ሁለቱ የሚጋጭ ነው።
‘ሪዘርቭ ነዳጅ አትያዝ’ ከተባለ አሽከርካሪው ሞያሌ ድረስ በምን ሊቀሳቀስ ይችላል? ካለበት ቦታ እንኳ ነዳጅ ቀድቶ ሪዘርቭ ይዞ እንዳይደርስ እንዳይቀዳ ማዕቀብ ተጣለ። ካልደረስክም ትቀጣለህ ተባለ ህጉ አልተገናዘበም።
አንድ ቻግኒ ተመድቦ የነበረ አሽከርካሪ ከጅቡቲ ቻግኒ 6 ቀን አልፏል ተብሎ ተቀጥቷል። በነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ፊርማ እነዚህ ሰዎች እንዲቀጡ፤ ተሽከርካሪው ካለው ካምፓኒ 480 ሺሕ ብር እንዲቆረጥ ተደረገ።
በወጣው ነጋሪት ጋዜጣው መሠረት፥ ተደብቆ የተገኘ ሹፌር ይቀጣል ይባላል። ተሽከርካሪኮ ከመንገድ ውጪ አይሄድም ማደያ፣ ኬላ ላይ ሰልፍ ይዟል፤ ወይም በጸጥታው ምክንያት ከዚህ ሰዓት በኋላ አይኬድም በመባሉ ከተማላይ ቁሟል ማለት ነው።
ግን ተደብቆ የተገኘ አሽከርካሪ ከ300 ሺሕ እስከ 500 ሺሕ ብርና የሦስት አመት የእስራት ቅጣት ነጋሪት ጋዜጣ የተቀመጠ ዐዋጅ አለ። ይሄ አግባብ አይደለም ” ነው ያሉት።
(ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንለት ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምላሽ እንደሰጠ ይቀርባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
አሽከርካሪዎችን በተመለከተ የሚወጡ ህጎች አሳታፊነት የጎደላቸውና አሽከርካሪዎች ሥራ እንዲያቆሙ የሚያደርጉ በመሆናቸው ሊጤኑ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር አሳሰበ።
ግብዓት የሚያጓጓዙ ሹፌሮች በጸጥታ ችግር መንገድ ላይ በሚጉላሉበት፣ የሚጓጓዙበት ሪዘርቭ ነዳጅ እንዳይጭኑ በሚከለከሉበት ሁኔታ በአራትና አምስት ቀናት ከጂቡቲ ወደ መሀል ሀገር ካልደረሱ እስከ 500 ሺሕ ብር የተጣለባቸውን ቅጣት ማኀበሩ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ተቃውሟል።
ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አለ?
የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ዘውዱ፥ “ ህግ ሲወጣ አሳትፉን ብለን ለነዳጅና ኢነርጅ ባለስልጣን በተደጋጋሚ ደብዳቤ አስገብተን ሊያነጋግሩን ፈቃደኞች አይደሉም።
ህግ ሲወጣ ማህበሩ መሳተፍ አለበት። የሚጎዱና ተደራራቢ ህጎችን በማውጣት አሽከርካሪዎች ከስራ እንዲፈናቀሉ እንጅ ህግ እንዲከበር አያደርግም። ያሽከርካሪን ችግር ሳያዳምጡ ህግ ማውጣቱን ማህበሩ አይቀበለውም።
ወንጀለኛ ከሆኑ አሽከርካሪዎች አይያዙ የሚል አመለካከት የለውም ማህበሩ። ግን አሰራሩ ሙሉ ለሙሉ ለሹፌሮች ብቻ እየተደረገ ባሽከርካሪዎች የመስራት ፍላጎት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያስከተለ ነው።
ሹፌሮች ረጅም መንገድ በሚጓዙበት ወቅት ለሚጓጓዙበት የሚሆን ሪዘርቭ ነዳጅ በታንከራቸው ይጭናሉ፤ ግን ከተሳቢ ታንከር ወደ ፊተኛው መኪና ሽፍት ሲያረጉ‘ነዳጅ እየቀሸብክ ነው; ተብሎ የሚያዙበት አጋጣሚ እየተፈጠረ ነው። ይሄ ትክክል አይደለም።
ከጅቡቲ ሞያሌ የሚሄድ አሽከርካሪ ሪዘርብ ነዳጅ ካልያዘ መንደር ላይ ሊያጣ ይችላል። ባሁኑ ወቅታዊ ሁኔታ ነዳጅ በየቦታው አይገኝም። ስለዚህ ሹፌርን ሆን ተብሎ ለመበደል ምክንያት እየተፈለገ ነው ” ብለዋል።
ሌላኛው የማኀበሩ አመራር ምን አሉ ?
“ አንድ አሽከርካሪ ነዳጅ ከጅቡቲ አድስ አበባ ከጫነ በአራት ቀን መድረስ አለበት ተብሏል። ካልደረሰ 480 ሺሕ ብር፣ ተደብቆ የተገኘ እስከ 500 ሺሕ ብር የሚያስቀጣ መሆኑን ወስነዋል። ከ300 ሺሕ እሰከ 500 ሺሕ ነው ቅጣቱ። ግን ሪዘርቭ ነዳጅ እንዳይያዝም ከልክለዋል።
አንድ አሽከርካሪ በዋና ታከሩ የያዘው ነዳጅ አያደርሰውም እየተጓዘ ነዳጅ ካቋረጠው ወረፋ ይዞ እንደማንኛውም ደረቅ ጭነት የጫነ ተሽከርካሪ ተሰልፎ ነው የሚቀዳው፤ ከወረፋ መካከል አውጥተው ‘ተደብቆ የተገኘ ሹፌር ይዘናል’ ተብሎ ለሚዲያ ፍጆታ ይቀርባል።
የነዳጅ ጫኚ መኪና የሚቀዳበት የተለየ ማደያ የለም። ይሄ በሌለበት በዛ ቀን አልደረስከም ተብሎ መያዝ፣ ካገኙት ማደያ እንኳ ሪዘርቭ ይዘው ሲሄዱ ሪዘርቩን ሲያገላብጥ ‘እየቀሸበ ነው’ ተብሎ መጠየቁ አሽከርካሪውን ስራ ወደ ማቆም እያደረሰ ነው።
በጣም አስቸጋሪ ደረጃ እየደረስን ነው። ባሽከርካሪ ጉዳይ የሚወጣ ህግ ካለ ቀድመን በመሳተፍ የህጉ የግብአት አካል መሆን አለብን።
ነዳጂና ኢነርጂ ባለስልጣንን ጠይቀን፤ ‘አናስገባም’ አሉን በፅሑፍ አምጡ ተባልን በእጅ ፅሑፍ ሀሳባችንን ገለጽን፤ ነገር ግን ‘ሌላ አካል ስላነጋገርን አናነጋግርም’ የሚል መልስ ሰጡን፤ ሕጋዊ ደብዳቤም ፅፈን አስገባን አሁንም የተሰጠን የፅሑፍም ሆነ የቃል መልስ የለም።
ለንግድና ቀጠናዊ ትስስርም ደብዳቤ አስገባን። ፕሮግራም ተይዞልን ህጉ በነጋሪት ጋዜጣ ከመታወጁ በፊት ንግግር እናድርግ ብለን ሄደን ጠየቅን፤ ግን የሚያነጋግረን አጣን። ሕጉ በነጋሪት ጋዜጣ ታወጀ ወደ ተግባር ገባ።
ሹፌር እንደማንኛውም ሙያ እኩል ነው እንዲባልና የሙያውን ዋጋ እንዲሰጠው ነው የምንሰራው። በተደራጀን ቁጥር ወደ መገፋት እየመጣን ነው። ማህበሩ ባይኖር በአንድ ቀን ስራ ሊቆም ይችላል። ሀሳባችነን ስናቀርብ ተደማጭነት ካጣን ምን እናደርጋለን።
ኮማድ ፖስት ባለበት ከጅቡቲ ነዳጅ የሚጭኑ ሹፌሮች በአራት ቀናት አዲስ አበባ ሊደርሱ አይችሉም። ሰዓቱን እንኳ ለመሸፈን ሪዘርቭ ነዳጅ እንዳይዙ ከተከለከለ በምን ሊደርሱ ይችላሉ? ሁለቱ የሚጋጭ ነው።
‘ሪዘርቭ ነዳጅ አትያዝ’ ከተባለ አሽከርካሪው ሞያሌ ድረስ በምን ሊቀሳቀስ ይችላል? ካለበት ቦታ እንኳ ነዳጅ ቀድቶ ሪዘርቭ ይዞ እንዳይደርስ እንዳይቀዳ ማዕቀብ ተጣለ። ካልደረስክም ትቀጣለህ ተባለ ህጉ አልተገናዘበም።
አንድ ቻግኒ ተመድቦ የነበረ አሽከርካሪ ከጅቡቲ ቻግኒ 6 ቀን አልፏል ተብሎ ተቀጥቷል። በነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ፊርማ እነዚህ ሰዎች እንዲቀጡ፤ ተሽከርካሪው ካለው ካምፓኒ 480 ሺሕ ብር እንዲቆረጥ ተደረገ።
በወጣው ነጋሪት ጋዜጣው መሠረት፥ ተደብቆ የተገኘ ሹፌር ይቀጣል ይባላል። ተሽከርካሪኮ ከመንገድ ውጪ አይሄድም ማደያ፣ ኬላ ላይ ሰልፍ ይዟል፤ ወይም በጸጥታው ምክንያት ከዚህ ሰዓት በኋላ አይኬድም በመባሉ ከተማላይ ቁሟል ማለት ነው።
ግን ተደብቆ የተገኘ አሽከርካሪ ከ300 ሺሕ እስከ 500 ሺሕ ብርና የሦስት አመት የእስራት ቅጣት ነጋሪት ጋዜጣ የተቀመጠ ዐዋጅ አለ። ይሄ አግባብ አይደለም ” ነው ያሉት።
(ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንለት ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምላሽ እንደሰጠ ይቀርባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ የአሜሪካ ታሪፍ መጨመር፣ በኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ ተፅዕኖ ይፈጥራል ” - አቶ ክቡር ገና
➡️ “ እርምጃው፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳትም ስለሚያስከትል፣ ሌሎች የገበያ መዳረሻዎችን ማፈላለግ ይገባል ! ”
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ሰሞኑን ባደረጉት አዲስ የቀረጥ ጭማሪ እርምጃ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ40 በላይ የአፍሪካ ሀገራትን አካቷል፡፡
እርምጃው ኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ በምታስገባቸው ምርቶች ላይ የ10 በመቶ ቀረጥ እንዲጣልባቸው አድርጓል፡፡
ይህ አዲሱ የፕረዝደንት ትራምፕ እርምጃ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እና ወደ አሜሪካ ገበያ በሚገቡ የኢትዮጵያ ምርቶች ላይ ምን ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው ባለሙያ፣ “ ተፅዕኖ መፍጠሩ አይቀሬ ነው ” ብለዋል፡፡
የቀረጥ ወይም ታሪፍ ጭማሪው፣ ወደ አሜሪካ ገበያ የሚላኩ ሸቀጦች ዋጋቸውን ያንረዋል፣ ይህ ደግሞ በሸማቹ ማኅበረሰብ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ሲሉ ተናረዋል፣ የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ክቡር ገና፡፡
በኢኮኖሚ፣ በንግድና ኢንቨስትመንት ጉዳዮች ትንታኔ በመስጠት የሚታወቁት አንጋፋው ባለሙያ አቶ ክቡር ገና በሰጡት ማብራሪያ፣ ኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ከምትልካቸው ምርቶች ቡና እና ጨርቃጨርቅ ትልቁን ድርሻ እንደሚይዙ ገልፀው፣ አሁን እነዚህ ምርቶች አሜሪካ በሚደርሱበት ጊዜ ዋጋቸው ይጨምራል ብለዋል፡፡
የሸቀጦቹ ዋጋ ሲጨምር፣ ገዢዎቹ ይቀንሳሉ፣ ያ ደግሞ ሀገር ውስጥ ያሉ አምራቾች ምርታቸው ሊቀንስ እና በአቅምም ሊያንገዳግዳቸው ይችላል ሲሉም አክለዋል፡፡
አቶ ክቡር ገና በዝርዝር ምን አሉ ?
“ እርምጃው የኤክስፖርት ኢኮኖሚውን ይጎዳዋል፡፡ ቀደም ሲል አባል የነበርንበት የአጎዋ ዕድል (የአፍሪካ ምርቶች ከቀረጥ ነፃ ወደ አሜሪካ ገበያ የሚገቡበት አሰራር) ተጠቃሚዎች ነበርን፡፡ ያ ዕድል ተቋርጦዋል፡፡
የኢትዮጵያ ምርቶች ቀረጥ ተክፍሎባቸው ነበር ወደ አሜሪካ ገበያ ሲገቡ የነበሩት፡፡ አሁን የተጨመረው የ 10 በመቶ ታሪፍ ቀደም ብሎ በነበረው ላይ ነው፡፡ ይህ የኢትዮጵያ ላኪዎችን ያዳክማል፡፡ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል፡፡
በአብዛኛው አንዲህ ዓይነት ለውጥ በሚመጣበት ጊዜ፣ የውጭ ምንዛሪ ግብይት (የገንዘብ መዘርዘሪያ መጠን) ላይ የሆነ ተፅዕኖ ያስከትላል፡፡ እርምጃው ብርን ሊያጠነክረው ይችላል፣ አለያም የበለጠ ሊያዳክመው ይችላል፣ እሱን ቀጥለን የምናየው ይሆናል፣ ግን ተፅዕኖው አይቀሬ ነው፡፡ ”
የትኞቹ ሸቀጦች የበለጠ ይጎዳሉ ?
“ በትክክል ምንድነው የሚፈጠረው የሚለው በትግበራው ወቅት ነው የሚታየው፡፡ ለምሳሌ እዛ ያሉት ኢምፖርተሮች (ከእኛ ላኪዎች ሸቀጦችን የሚረከቡ የአሜሪካ ነጋዴዎች)፣ አሁን በዚህ የታሪፍ መጨመር ምክንያት የሸቀጥ ዋጋ ጨምሮባቸዋል፡፡
አሁን እነሱ ምን ይወስናሉ፣ ጭማሪውን ራሳቸው ሸፍነው ትርፋቸውን ቀንሰው እቃውን ለሸማች ያቀርባሉ ወይስ ጭማሪውን በቀጥታ ለተጠቃሚው ያስተላልፋሉ የሚለው ገና የሚታይ ይሆናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ እርምጃው የትኞቹን ሸቀጦች የበለጠ ይጎዳል የሚለውም እንደዚሁ ቀጥሎ የሚታይ ነው፡፡
ለምሳሌ በአሜሪካ ገበያ ብዙም ተወዳዳሪ የሌለው የኢትዮጵያ ሸቀጥ ብዙም ተፅዕኖ ላይደርስበት ይችላል፣ ምክንያቱም ሸማቹ አማራጭ ስለሌለው ዋጋውም ቢጨምርበት እቃውን ይገዛዋል፡፡
የሆነ ሆኖ ግን ታሪፉ የምርት ዋጋ እንዲጨምር ያደርጋል፣ ያ ደግሞ በሸማቾች ዘንድ የመግዛት ፍላጎት ይቀንሳል፣ ከዛም የምርት መጠን ይዳከማል፣ ገዢ ከሌለ የኢትዮጵያ አምራቾች ሊያመርቱ አይችሉም፡፡ ”
መፍትሔው ምንድነው የሚሆነው ?
“ መፍትሔው ያንን የሚተካ ሌላ ገበያ መፈለግ ነው፡፡ ከአሜሪካ ወጥቶ የሌሎችን ሀገራት ገበያ ማፈላለግ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ተፅዕኖው ከመበርታቱ በፊት ሌሎች የንግድ መዳረሻዎችን ማፈላለግ ይገባል፡፡
ታሪፉ የተጣለው በሁሉም ሀገራት ላይ ስለሆነ፣ የትኛው ሀገር የበለጠ ይቋቋመዋል የሚለው ገና በትግበራ ወቅት የሚታይ ይሆናል፡፡ የታሪፍ ለውጥ መምጣት የፖሊሲ ለውጥ ለማድረግም ይረዳል፡፡
ወደ ሌሎች ዘርፎች እንድነገባ ሊያስገድድ ይችላል፡፡ ለምሳሌ የቱሪዝም ዘርፉን ማጠናከርና ማስፋፋት ይገባ ይሆናል፡፡ በተጣለው ታሪፍ ምክንያት የሚታጣውን ገቢ ለማካካስ ማለት ነው፡፡
በቅድሚያ ግን የእርምጃውን ተፅዕኖ በደንብ ማጥናትና የመውጫ መንገዶችን ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ተፅዕኖው ምን ሊሆን እንደሚችል ማየት ይኖርብናል፡፡ ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
➡️ “ እርምጃው፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳትም ስለሚያስከትል፣ ሌሎች የገበያ መዳረሻዎችን ማፈላለግ ይገባል ! ”
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ሰሞኑን ባደረጉት አዲስ የቀረጥ ጭማሪ እርምጃ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ40 በላይ የአፍሪካ ሀገራትን አካቷል፡፡
እርምጃው ኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ በምታስገባቸው ምርቶች ላይ የ10 በመቶ ቀረጥ እንዲጣልባቸው አድርጓል፡፡
ይህ አዲሱ የፕረዝደንት ትራምፕ እርምጃ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እና ወደ አሜሪካ ገበያ በሚገቡ የኢትዮጵያ ምርቶች ላይ ምን ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው ባለሙያ፣ “ ተፅዕኖ መፍጠሩ አይቀሬ ነው ” ብለዋል፡፡
የቀረጥ ወይም ታሪፍ ጭማሪው፣ ወደ አሜሪካ ገበያ የሚላኩ ሸቀጦች ዋጋቸውን ያንረዋል፣ ይህ ደግሞ በሸማቹ ማኅበረሰብ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ሲሉ ተናረዋል፣ የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ክቡር ገና፡፡
በኢኮኖሚ፣ በንግድና ኢንቨስትመንት ጉዳዮች ትንታኔ በመስጠት የሚታወቁት አንጋፋው ባለሙያ አቶ ክቡር ገና በሰጡት ማብራሪያ፣ ኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ከምትልካቸው ምርቶች ቡና እና ጨርቃጨርቅ ትልቁን ድርሻ እንደሚይዙ ገልፀው፣ አሁን እነዚህ ምርቶች አሜሪካ በሚደርሱበት ጊዜ ዋጋቸው ይጨምራል ብለዋል፡፡
የሸቀጦቹ ዋጋ ሲጨምር፣ ገዢዎቹ ይቀንሳሉ፣ ያ ደግሞ ሀገር ውስጥ ያሉ አምራቾች ምርታቸው ሊቀንስ እና በአቅምም ሊያንገዳግዳቸው ይችላል ሲሉም አክለዋል፡፡
አቶ ክቡር ገና በዝርዝር ምን አሉ ?
“ እርምጃው የኤክስፖርት ኢኮኖሚውን ይጎዳዋል፡፡ ቀደም ሲል አባል የነበርንበት የአጎዋ ዕድል (የአፍሪካ ምርቶች ከቀረጥ ነፃ ወደ አሜሪካ ገበያ የሚገቡበት አሰራር) ተጠቃሚዎች ነበርን፡፡ ያ ዕድል ተቋርጦዋል፡፡
የኢትዮጵያ ምርቶች ቀረጥ ተክፍሎባቸው ነበር ወደ አሜሪካ ገበያ ሲገቡ የነበሩት፡፡ አሁን የተጨመረው የ 10 በመቶ ታሪፍ ቀደም ብሎ በነበረው ላይ ነው፡፡ ይህ የኢትዮጵያ ላኪዎችን ያዳክማል፡፡ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል፡፡
በአብዛኛው አንዲህ ዓይነት ለውጥ በሚመጣበት ጊዜ፣ የውጭ ምንዛሪ ግብይት (የገንዘብ መዘርዘሪያ መጠን) ላይ የሆነ ተፅዕኖ ያስከትላል፡፡ እርምጃው ብርን ሊያጠነክረው ይችላል፣ አለያም የበለጠ ሊያዳክመው ይችላል፣ እሱን ቀጥለን የምናየው ይሆናል፣ ግን ተፅዕኖው አይቀሬ ነው፡፡ ”
የትኞቹ ሸቀጦች የበለጠ ይጎዳሉ ?
“ በትክክል ምንድነው የሚፈጠረው የሚለው በትግበራው ወቅት ነው የሚታየው፡፡ ለምሳሌ እዛ ያሉት ኢምፖርተሮች (ከእኛ ላኪዎች ሸቀጦችን የሚረከቡ የአሜሪካ ነጋዴዎች)፣ አሁን በዚህ የታሪፍ መጨመር ምክንያት የሸቀጥ ዋጋ ጨምሮባቸዋል፡፡
አሁን እነሱ ምን ይወስናሉ፣ ጭማሪውን ራሳቸው ሸፍነው ትርፋቸውን ቀንሰው እቃውን ለሸማች ያቀርባሉ ወይስ ጭማሪውን በቀጥታ ለተጠቃሚው ያስተላልፋሉ የሚለው ገና የሚታይ ይሆናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ እርምጃው የትኞቹን ሸቀጦች የበለጠ ይጎዳል የሚለውም እንደዚሁ ቀጥሎ የሚታይ ነው፡፡
ለምሳሌ በአሜሪካ ገበያ ብዙም ተወዳዳሪ የሌለው የኢትዮጵያ ሸቀጥ ብዙም ተፅዕኖ ላይደርስበት ይችላል፣ ምክንያቱም ሸማቹ አማራጭ ስለሌለው ዋጋውም ቢጨምርበት እቃውን ይገዛዋል፡፡
የሆነ ሆኖ ግን ታሪፉ የምርት ዋጋ እንዲጨምር ያደርጋል፣ ያ ደግሞ በሸማቾች ዘንድ የመግዛት ፍላጎት ይቀንሳል፣ ከዛም የምርት መጠን ይዳከማል፣ ገዢ ከሌለ የኢትዮጵያ አምራቾች ሊያመርቱ አይችሉም፡፡ ”
መፍትሔው ምንድነው የሚሆነው ?
“ መፍትሔው ያንን የሚተካ ሌላ ገበያ መፈለግ ነው፡፡ ከአሜሪካ ወጥቶ የሌሎችን ሀገራት ገበያ ማፈላለግ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ተፅዕኖው ከመበርታቱ በፊት ሌሎች የንግድ መዳረሻዎችን ማፈላለግ ይገባል፡፡
ታሪፉ የተጣለው በሁሉም ሀገራት ላይ ስለሆነ፣ የትኛው ሀገር የበለጠ ይቋቋመዋል የሚለው ገና በትግበራ ወቅት የሚታይ ይሆናል፡፡ የታሪፍ ለውጥ መምጣት የፖሊሲ ለውጥ ለማድረግም ይረዳል፡፡
ወደ ሌሎች ዘርፎች እንድነገባ ሊያስገድድ ይችላል፡፡ ለምሳሌ የቱሪዝም ዘርፉን ማጠናከርና ማስፋፋት ይገባ ይሆናል፡፡ በተጣለው ታሪፍ ምክንያት የሚታጣውን ገቢ ለማካካስ ማለት ነው፡፡
በቅድሚያ ግን የእርምጃውን ተፅዕኖ በደንብ ማጥናትና የመውጫ መንገዶችን ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ተፅዕኖው ምን ሊሆን እንደሚችል ማየት ይኖርብናል፡፡ ”
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
“ እናቶች የሚያለቅሱበት፣ የወላጆች ልጅ አልባ መሆን ሊቆም ይገባል” - ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም
➡️ “ ወንድም ወንድሙን ለምን ይገድላል? ለምን ያሳድዳል? ብለን የምንጠይቅበት መድረክ ነው” - ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስታዲዬም ዛሬ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
በዚህም የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች፣ የሃማይኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ተሳታፊዎች፣ የባህል ማዕከል፣ የክልሉ ማርሽ ባንድ የተገኙ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩም የኃማይኖት አባቶች ባደረጉት ጸሎት ተጀምሯል።
በዚህም ከአምስት ባድርሻ አካላት የተወከሉ ከ6000 በላይ ወኪሎች ይሳተፋሉ፣ በተለያዩ ወረዳዎች ማኀበረሰቡን የወከሉ 4500 ወኪሎች በመጀመሪያዎቹ አራት ቀናት በአገራዊ አጀንዳ ውይይት ያደርጋሉ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ምን አሉ?
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም፣ “ኢትዮጵያ በመደማማት ያተረፈችው ነገር የለም። የጦርነት አዙሪት፣ እርስ በእርስ ለማስቆም ያስችላል በሚል ምክክሩ ተጀምሯል” ብለዋል።
“እርስ በእርስ መጨራረስን በቃ ልንል ይገባል። እናቶች የሚያለቅሱበት፣ የወላጆች ልጅ አልባ መሆን ሊቆም ይገባል” ያሉት ኮሚሽነሩ፣ “ለምንድን ነው የምንገዳደለው?” ሲሉ ጠይቀዋል።
ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ አማርኛን ያስተማረ የአማራ ህዝብ መሆኑን ጠቅሰው፣ “የቤሰብ ፀብ ቢፈጠር ዝም ብለን ማዬት አለብን?” ሲሉ ጠይቀዋል።
ዐድዋን የመጀመሪያ፣ ዓባይ ግድብን ሁለተኛ ድል ጠቅሰው ሀገራዊ ምክክሩን “3ኛው ዓድዋ” ሲሉ የጠሩት ዮናስ (ዶ/ር)፣ ምክክሩ፣ ህዝብን ከህዝብ ለማግባባት፣ በተከፉ ቁጥር ትጥቅ አንግበው ጫካ የሚወጡ አካላት በመወያዬት እንዲያምኑ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
ምክትል ዋና ኮሚሽነር ወ/ሮ ሂሩት ገ/ስላሴ፣ “ያለፉት ዘመናት አልፈው ተርፈው በትጥቅ ትግል ተይዘዋል” ብለው፣ የትጥቅ ትግል ጊዜያዊ እንደሆን እንጂ ዘላቂ መፍትሄና ሰላም እንደማያመጣ አስገንዝበዋል።
ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር)፣ “ወንድም ወንድሙን ለምን ይገድላል? ለምን ያሳድዳል? ብለን የምንጠይቅበት መድረክ ነው። ለዝመት፣ እንደፍራለን አሁን ደግሞ ለማዳመጥ የምንደፍርበት ወቅት ነው ብዬ አስባለሁ” ብለዋል።
ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)፣ አለመግባባቶች እንደሚስተዋሉ ገልጸው፣ ለዚህም አማራ ክልልም አንዱ መሆኑን ገልጸው፣ በሚሊዮን የሚቅጠሩ ህፃናት ከትምህርት ቤት በር መድረስ እንዳልቻሉ፣ በርካታ ወጣቶች ወደ ጫካ ለመግባት ለመግባት መገደዳቸውን ገልጸዋል።
ለዚህም ምክክር እንደሚያስልግ፣ ታጣቂዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ ጥሪ ሲያደርጉ እንደቆዩ ገልጸው፣ ለታጣቂዎች አሁንም በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ እናቶች የሚያለቅሱበት፣ የወላጆች ልጅ አልባ መሆን ሊቆም ይገባል” - ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም
➡️ “ ወንድም ወንድሙን ለምን ይገድላል? ለምን ያሳድዳል? ብለን የምንጠይቅበት መድረክ ነው” - ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስታዲዬም ዛሬ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
በዚህም የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች፣ የሃማይኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ተሳታፊዎች፣ የባህል ማዕከል፣ የክልሉ ማርሽ ባንድ የተገኙ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩም የኃማይኖት አባቶች ባደረጉት ጸሎት ተጀምሯል።
በዚህም ከአምስት ባድርሻ አካላት የተወከሉ ከ6000 በላይ ወኪሎች ይሳተፋሉ፣ በተለያዩ ወረዳዎች ማኀበረሰቡን የወከሉ 4500 ወኪሎች በመጀመሪያዎቹ አራት ቀናት በአገራዊ አጀንዳ ውይይት ያደርጋሉ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ምን አሉ?
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም፣ “ኢትዮጵያ በመደማማት ያተረፈችው ነገር የለም። የጦርነት አዙሪት፣ እርስ በእርስ ለማስቆም ያስችላል በሚል ምክክሩ ተጀምሯል” ብለዋል።
“እርስ በእርስ መጨራረስን በቃ ልንል ይገባል። እናቶች የሚያለቅሱበት፣ የወላጆች ልጅ አልባ መሆን ሊቆም ይገባል” ያሉት ኮሚሽነሩ፣ “ለምንድን ነው የምንገዳደለው?” ሲሉ ጠይቀዋል።
ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ አማርኛን ያስተማረ የአማራ ህዝብ መሆኑን ጠቅሰው፣ “የቤሰብ ፀብ ቢፈጠር ዝም ብለን ማዬት አለብን?” ሲሉ ጠይቀዋል።
ዐድዋን የመጀመሪያ፣ ዓባይ ግድብን ሁለተኛ ድል ጠቅሰው ሀገራዊ ምክክሩን “3ኛው ዓድዋ” ሲሉ የጠሩት ዮናስ (ዶ/ር)፣ ምክክሩ፣ ህዝብን ከህዝብ ለማግባባት፣ በተከፉ ቁጥር ትጥቅ አንግበው ጫካ የሚወጡ አካላት በመወያዬት እንዲያምኑ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
ምክትል ዋና ኮሚሽነር ወ/ሮ ሂሩት ገ/ስላሴ፣ “ያለፉት ዘመናት አልፈው ተርፈው በትጥቅ ትግል ተይዘዋል” ብለው፣ የትጥቅ ትግል ጊዜያዊ እንደሆን እንጂ ዘላቂ መፍትሄና ሰላም እንደማያመጣ አስገንዝበዋል።
ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር)፣ “ወንድም ወንድሙን ለምን ይገድላል? ለምን ያሳድዳል? ብለን የምንጠይቅበት መድረክ ነው። ለዝመት፣ እንደፍራለን አሁን ደግሞ ለማዳመጥ የምንደፍርበት ወቅት ነው ብዬ አስባለሁ” ብለዋል።
ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)፣ አለመግባባቶች እንደሚስተዋሉ ገልጸው፣ ለዚህም አማራ ክልልም አንዱ መሆኑን ገልጸው፣ በሚሊዮን የሚቅጠሩ ህፃናት ከትምህርት ቤት በር መድረስ እንዳልቻሉ፣ በርካታ ወጣቶች ወደ ጫካ ለመግባት ለመግባት መገደዳቸውን ገልጸዋል።
ለዚህም ምክክር እንደሚያስልግ፣ ታጣቂዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ ጥሪ ሲያደርጉ እንደቆዩ ገልጸው፣ ለታጣቂዎች አሁንም በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ለትምህርትና ለህክምና ቅድሚያ ሰጥቻለሁ " - ባንኩ
አዋሽ ባንክ ባንክ ባለፉት 3 ወራት ከ498 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለደንበኞቹ ማቅረቡን አስታውቋል።
ባንኩ ይህንን የውጭ ምንዛሬ ያቀረበው ለ2200 ለሚሆኑ የባንኩ ደንበኞች መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
በዚሁ ጊዜ ለተለያዩ የሀገር ውስጥ ባንኮች ከ100 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ዕገዛ ማድረጉን የገለጸ ሲሆን ይህም ባንኮች የዶላር እጥረት ሲገጥማቸው በኢንተር ባንክ ያደረገላቸውን የዶላር ሽያጭ መጠን የሚያሳይ ነው።
በሦስት ወር ጊዜ ውስጥም ባንኩ ፦
- ለዘይት ከ50 ሚሊዮን ዶላር በላይ ፣
- ለነዳጅ 79 ሚሊዮን ዶላር፣
- ለስኳር 20 ሚሊዮን ዶላር፣
- ለሩዝ 11 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መስጠቱን አስታውቋል።
" ባንኩ ለትምህርት እና ለህክምና ቅድሚያ ሰጥቻለሁ " ማለቱን ተከትሎ ለምን ያህል ዜጎች አገልግሎቱን እንደሰጡ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የባንኩ የብራንዲንግ እና ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር ሰለሞን ጀቤሳ " በከፍተኛ መጠን " ሲሉ ትክክለኛ መጠኑን ከመግለፅ ተቆጥበዋል።
" ለትምህርት ለህክምና የሚጠየቁት አነስ አነስ ያሉ ወጪዎች ናቸው። በቁጥር በጣም ብዙ ሰዎች ይሆናሉ ...[ዋናው] ለእነዚህ ጥያቄዎች ትኩረት መስጠታችን ነው " ያሉት ዳይሬክተሩ ከትምህርት እና ከጤና ጋር ጥያቄ ለቀረበባቸው አብዛኞቹ ፍላጎቶች ግን ምላሽ መስጠታቸውን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
አዋሽ ባንክ ባንክ ባለፉት 3 ወራት ከ498 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለደንበኞቹ ማቅረቡን አስታውቋል።
ባንኩ ይህንን የውጭ ምንዛሬ ያቀረበው ለ2200 ለሚሆኑ የባንኩ ደንበኞች መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
በዚሁ ጊዜ ለተለያዩ የሀገር ውስጥ ባንኮች ከ100 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ዕገዛ ማድረጉን የገለጸ ሲሆን ይህም ባንኮች የዶላር እጥረት ሲገጥማቸው በኢንተር ባንክ ያደረገላቸውን የዶላር ሽያጭ መጠን የሚያሳይ ነው።
በሦስት ወር ጊዜ ውስጥም ባንኩ ፦
- ለዘይት ከ50 ሚሊዮን ዶላር በላይ ፣
- ለነዳጅ 79 ሚሊዮን ዶላር፣
- ለስኳር 20 ሚሊዮን ዶላር፣
- ለሩዝ 11 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መስጠቱን አስታውቋል።
" ባንኩ ለትምህርት እና ለህክምና ቅድሚያ ሰጥቻለሁ " ማለቱን ተከትሎ ለምን ያህል ዜጎች አገልግሎቱን እንደሰጡ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የባንኩ የብራንዲንግ እና ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር ሰለሞን ጀቤሳ " በከፍተኛ መጠን " ሲሉ ትክክለኛ መጠኑን ከመግለፅ ተቆጥበዋል።
" ለትምህርት ለህክምና የሚጠየቁት አነስ አነስ ያሉ ወጪዎች ናቸው። በቁጥር በጣም ብዙ ሰዎች ይሆናሉ ...[ዋናው] ለእነዚህ ጥያቄዎች ትኩረት መስጠታችን ነው " ያሉት ዳይሬክተሩ ከትምህርት እና ከጤና ጋር ጥያቄ ለቀረበባቸው አብዛኞቹ ፍላጎቶች ግን ምላሽ መስጠታቸውን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ለሹፌሩ እና ረዳቱ ደጋግመን እየደወልን ነው እስካሁን ማግኘት አልቻልንም " -ፈለገ ግዮን ባስ 🚨" መኪናው መስታወቱ እና የፊት ለፊት ጎማው በጥይት ተመቷል " -የዓይን እማኝ ሹፌር በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ወደ ማርቆስ ተሳፋሪዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ " ፈለገ ግዮን " የሚል ስያሜ ያለው ባስ በኦሮሚያ ክልል ከፍቼ እና ጎሀፂዮን መሃከል ባለው መንገድ ላይ አሊደሮ በተባለ ስፍራ ሙሉ ተሳፋሪዎቹ…
“ የሟች ቤተሰቦች አስክሬን ለማምጣት ሄደዋል ” - የአንዱ ሟች ቤተሰብ
ትላንት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን፣ “ጎሃ ፅዮን” እና “ቱሉ ሚልኪ” መካከል ታጣቂዎች አንድ ሙሉ ተሽከርካሪ ተሳፋሪዎችን መገታቸው ከዛም ውስጥ የተገደሉ መኖራቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
አንድ የሟች የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ አንድ የልጆች አባት እንደተገደሉ፣ ነገ የቀብር ሥርዓታቸው ይፈጸማል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸው፣ “ የሟች ቤተሰብ አስከሬን ለማምጣት ሄደዋል ” ብለዋል።
ሌላኛው የሌላ ሟች ጓደኛ በበኩላቸው፣ ሹፌሩን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ተሳፋሪዎች ሳይገደሉ እንዳልቀሩ፣ የሟቾቹን አስክሬን ወደ ትውልድ ቦታቸው ለማምጣት የሟች ቤተሰቦች ዛሬ ወደ እገታ ቦታው እንደሄዱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የሟቾች ወላጆች የሟቾቹን አስክሬን ገና ሊቀበሉ በመሆኑ፣ ሀዘናቸውም ስለበረታ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት የሚያስችል መረጋጋት ላይ አለመሆናቸው ተመልክቷል።
የሹፌሮችን ውሎ የሚከታተለው ጣና የአሽከርካሪዎች ማኀበር በበኩሉ፣ በታጣቂዎች ታገቱ ከተባሉት ተሳፋሪዎች መካከል በርካቶች በጥይት ተመትተው መገደላቸውን ከስፍራው መረጃ እንደደረሰው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ከተገዱሉት ተሳፋሪዎች ባሻገር ታፍነው የተወሰዱ እንዳሉም ያመለከተ ሲሆን፣ እገታው የተጸመው ትላንት (ቅዳሜ መጋቢት 27 ቀን 2027 ዓ/ም) መሆኑን ተናግሯል።
ስለእገታው ከመንግስት እስካሁን በግልጽ የተባለ ነገር ባይኖርም፣ በእገታው ቦታ የፌደራል ፓሊስ ደርሶ እንደነበር በማኀበራዊ ሚዲያ ሲሰራጭ ተስተውሏል።
ስለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቅናቸው በኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጀይላን አብዲ፣ ስራ ላይ እንደሆኑ በመግለጻቸው ለጊዜው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም። ምላሽ ከሰጡን የምናቀርብ ይሆናል።
የትላንቱ እገታ በተፈጸመበት አካባቢ ከ19 ቀናት በፊት ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ማርቆስ በርካታ ተሳፋሪዎች ይዞ ሲጓዝ የነበረ " ፈለገ ግዮን " ባስ ታጣቂዎች አስቁመውት ሙሉ ተሳፋሪዎች መታገታቸውን የአይን እማኝ ሹፌሮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀው ነበር።
ከእገታው በኃላ የታጋች ቤተሰቦች በሚሊዮን ብር እየተጠየቁ ነው።
https://yangx.top/tikvahethiopia/95170?single
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ትላንት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን፣ “ጎሃ ፅዮን” እና “ቱሉ ሚልኪ” መካከል ታጣቂዎች አንድ ሙሉ ተሽከርካሪ ተሳፋሪዎችን መገታቸው ከዛም ውስጥ የተገደሉ መኖራቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
አንድ የሟች የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ አንድ የልጆች አባት እንደተገደሉ፣ ነገ የቀብር ሥርዓታቸው ይፈጸማል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸው፣ “ የሟች ቤተሰብ አስከሬን ለማምጣት ሄደዋል ” ብለዋል።
ሌላኛው የሌላ ሟች ጓደኛ በበኩላቸው፣ ሹፌሩን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ተሳፋሪዎች ሳይገደሉ እንዳልቀሩ፣ የሟቾቹን አስክሬን ወደ ትውልድ ቦታቸው ለማምጣት የሟች ቤተሰቦች ዛሬ ወደ እገታ ቦታው እንደሄዱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የሟቾች ወላጆች የሟቾቹን አስክሬን ገና ሊቀበሉ በመሆኑ፣ ሀዘናቸውም ስለበረታ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት የሚያስችል መረጋጋት ላይ አለመሆናቸው ተመልክቷል።
የሹፌሮችን ውሎ የሚከታተለው ጣና የአሽከርካሪዎች ማኀበር በበኩሉ፣ በታጣቂዎች ታገቱ ከተባሉት ተሳፋሪዎች መካከል በርካቶች በጥይት ተመትተው መገደላቸውን ከስፍራው መረጃ እንደደረሰው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ከተገዱሉት ተሳፋሪዎች ባሻገር ታፍነው የተወሰዱ እንዳሉም ያመለከተ ሲሆን፣ እገታው የተጸመው ትላንት (ቅዳሜ መጋቢት 27 ቀን 2027 ዓ/ም) መሆኑን ተናግሯል።
ስለእገታው ከመንግስት እስካሁን በግልጽ የተባለ ነገር ባይኖርም፣ በእገታው ቦታ የፌደራል ፓሊስ ደርሶ እንደነበር በማኀበራዊ ሚዲያ ሲሰራጭ ተስተውሏል።
ስለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቅናቸው በኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጀይላን አብዲ፣ ስራ ላይ እንደሆኑ በመግለጻቸው ለጊዜው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም። ምላሽ ከሰጡን የምናቀርብ ይሆናል።
የትላንቱ እገታ በተፈጸመበት አካባቢ ከ19 ቀናት በፊት ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ማርቆስ በርካታ ተሳፋሪዎች ይዞ ሲጓዝ የነበረ " ፈለገ ግዮን " ባስ ታጣቂዎች አስቁመውት ሙሉ ተሳፋሪዎች መታገታቸውን የአይን እማኝ ሹፌሮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀው ነበር።
ከእገታው በኃላ የታጋች ቤተሰቦች በሚሊዮን ብር እየተጠየቁ ነው።
https://yangx.top/tikvahethiopia/95170?single
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia