#Tigray
የትግራይ ርእሰ መዲና መቐለ አዲስ ከንቲባ እንደተመደበላት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ተናግረዋል።
የመቐለ ከተማ ነዋሪዎችን ፀጥታ እና ደህንነት እንዲጠበቅ እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በጊዜያዊ አስተዳደሩ ብዙ የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን ዶክተር ሙሉ ነጋ አሳውቀዋል።
ፓርቲዎቹ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ እንዲሁም የካቢኔ አባል እየሆኑ እንደሆነ አሳውቀዋል። ከነዚህ ፓርቲዎች መካከል አረና ፣ አሲምባ ፣ ትዴፓ ይገኙበታል።
አሁንም በክልሉ የሃሳብ ብዝሃነት እንዲኖር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ የመጫወቻ ሜዳውን እኩል የማድረግ ኃላፊነቱን ይወጣል ህዝቡ በመረጠው / በፈለገው አካል ይተዳደራል ብለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የትግራይ ርእሰ መዲና መቐለ አዲስ ከንቲባ እንደተመደበላት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ተናግረዋል።
የመቐለ ከተማ ነዋሪዎችን ፀጥታ እና ደህንነት እንዲጠበቅ እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በጊዜያዊ አስተዳደሩ ብዙ የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን ዶክተር ሙሉ ነጋ አሳውቀዋል።
ፓርቲዎቹ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ እንዲሁም የካቢኔ አባል እየሆኑ እንደሆነ አሳውቀዋል። ከነዚህ ፓርቲዎች መካከል አረና ፣ አሲምባ ፣ ትዴፓ ይገኙበታል።
አሁንም በክልሉ የሃሳብ ብዝሃነት እንዲኖር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ የመጫወቻ ሜዳውን እኩል የማድረግ ኃላፊነቱን ይወጣል ህዝቡ በመረጠው / በፈለገው አካል ይተዳደራል ብለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሱዳኑ ጠ/ሚር ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ዛሬ ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተው የነበሩት የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር መሃመድ አብደላ ሃምዶክ እና ልዑካቸው ጉብኝታቸውን በግማሽ ቀን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው ተመለሱ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት በሚል የያዙትን የጉብኝት መርሃ ግብር ለምን በግማሽ ቀን አጠናቀው እንደተመለሱ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ጉብኝቱን በተመለከተ መግለጫ የሰጠው የሃገሪቱ…
የሱዳን ጠ/ሚር አብደላ ሀምዶክ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን በተመለከተ ትናንት ምሽት መግለጫ ሰጡ።
ሀምዶክ ከኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ ጋር ስኬታማ ቆይታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ የጉብኝታቸውን ዓላማ ማሳካታቸውንም ነው የተናገሩት፡፡
ሀምዶክ ፥ “በሚዲያዎች የተንሸራሸሩ አሉታዊ ሀሳቦች ሁሉ አሉባልታዎች ናቸው” ብለዋል በመግለጫቸው፡፡
ከአቀባበል ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ራሳቸው በሚያሽከረክሩት መኪና ተቀብለዋቸው እንዳስተናገዷቸውና በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች መምከራቸውን አንስተዋል፡፡
በትግራይ ክልል ጉዳይ ላይ በሚካሔደው የጅቡቲ ስብሰባ፣ በህዳሴ ግድብ ቀጣይ ድርድር እንዲሁም በኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ነው የገለጹት፡፡
በትግራይ ክልል የተፈጠረውንና አሁን ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በቀጣዩ እሁድ በጅቡቲ ለኢጋድ አባል ሀገራት መሪዎች ሪፖርት እንደሚያቀርቡም ጠ/ሚ ሀምዶክ ተናግረዋል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ “እስካሁን ከነበረኝ ጉብኝት የአሁኑ ይበልጥ የተሳካ ነበር” ያሉት ጠ/ሚ ሀምዶክ “ከዚህ በተቃራኒ የሚባሉ ነገሮች ሀሰት ናቸው” ብለዋል፡፡
‘አየር ማረፊያ እንደደረሰ ተባረረ’ እስከመባል የሀሰት መረጃዎች ተናፍሰዋል” ያሉት ሀምዶክ ይህ የፈጠራ ወሬ እንደሆነ ነው ያብራሩት፡፡
ጉብኝታቸው ለሁለት ቀናት የታሰበ ቢሆንም “ከአየር ማረፊያው ወደ ቤተመንግስት በመጓዝ ላይ እንዳለን፣ በሁለቱም ሀገራት ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር በአጀንዳዎቻችን ላይ ተነጋግረን ሌላው ጉብኝት እንዲቀር #እኔ ባቀረብኩት ሀሳብ ተግባብተን ነው የሁለተኛው ቀን ጉብኝት የቀረው” ብለዋል፡፡
“በመሆኑም በአጀንዳዎቻችን ላይ ስኬታማ ውይይት አድርገን ሌሎች ተጨማሪ የጉብኝት አጀንዳዎችን ሰርዘናል” ነው ያሉት፡፡
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopia
ሀምዶክ ከኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ ጋር ስኬታማ ቆይታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ የጉብኝታቸውን ዓላማ ማሳካታቸውንም ነው የተናገሩት፡፡
ሀምዶክ ፥ “በሚዲያዎች የተንሸራሸሩ አሉታዊ ሀሳቦች ሁሉ አሉባልታዎች ናቸው” ብለዋል በመግለጫቸው፡፡
ከአቀባበል ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ራሳቸው በሚያሽከረክሩት መኪና ተቀብለዋቸው እንዳስተናገዷቸውና በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች መምከራቸውን አንስተዋል፡፡
በትግራይ ክልል ጉዳይ ላይ በሚካሔደው የጅቡቲ ስብሰባ፣ በህዳሴ ግድብ ቀጣይ ድርድር እንዲሁም በኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ነው የገለጹት፡፡
በትግራይ ክልል የተፈጠረውንና አሁን ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በቀጣዩ እሁድ በጅቡቲ ለኢጋድ አባል ሀገራት መሪዎች ሪፖርት እንደሚያቀርቡም ጠ/ሚ ሀምዶክ ተናግረዋል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ “እስካሁን ከነበረኝ ጉብኝት የአሁኑ ይበልጥ የተሳካ ነበር” ያሉት ጠ/ሚ ሀምዶክ “ከዚህ በተቃራኒ የሚባሉ ነገሮች ሀሰት ናቸው” ብለዋል፡፡
‘አየር ማረፊያ እንደደረሰ ተባረረ’ እስከመባል የሀሰት መረጃዎች ተናፍሰዋል” ያሉት ሀምዶክ ይህ የፈጠራ ወሬ እንደሆነ ነው ያብራሩት፡፡
ጉብኝታቸው ለሁለት ቀናት የታሰበ ቢሆንም “ከአየር ማረፊያው ወደ ቤተመንግስት በመጓዝ ላይ እንዳለን፣ በሁለቱም ሀገራት ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር በአጀንዳዎቻችን ላይ ተነጋግረን ሌላው ጉብኝት እንዲቀር #እኔ ባቀረብኩት ሀሳብ ተግባብተን ነው የሁለተኛው ቀን ጉብኝት የቀረው” ብለዋል፡፡
“በመሆኑም በአጀንዳዎቻችን ላይ ስኬታማ ውይይት አድርገን ሌሎች ተጨማሪ የጉብኝት አጀንዳዎችን ሰርዘናል” ነው ያሉት፡፡
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopia
በሆሳዕና በደረሰ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ።
በሆሳዕና ከተማ በአንድ የገበያ አዳራሽ የደረሰው የእሳት ቃጠሎ ከ5 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ንብረት ማውደሙን የከተማው ፖሊስ አስታውቋል።
የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ኤርደዶ አወኖ ዛሬ እንደገለፁት በቀን 05/04/2013 ዓ/ም ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በርካታ የኤሌክትሮኒክስና የአልባሳት የንግድ ድርጅቶች ከነ ሙሉ ንብረታቸው አውድሟል ።
ለሦስት (3) ተከታታይ ሰዓት የቆየው የእሳት ቃጠሎ የአካባቢው ህብረተሰብ ባደረገው እርብርብ ወደ ሌሎች ድርጅቶች ሳይዛመት ማጥፋት የተቻለ ሲሆን ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ላይ መሆኑንም ኮማንደሩ ገልፀዋል።
ምንጭ፦ የሆሳዕና ከተማ ኮሚኒኬሽን ፣ ፎቶ - Tikvah Family Hossana
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በሆሳዕና ከተማ በአንድ የገበያ አዳራሽ የደረሰው የእሳት ቃጠሎ ከ5 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያለው ንብረት ማውደሙን የከተማው ፖሊስ አስታውቋል።
የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ኤርደዶ አወኖ ዛሬ እንደገለፁት በቀን 05/04/2013 ዓ/ም ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በርካታ የኤሌክትሮኒክስና የአልባሳት የንግድ ድርጅቶች ከነ ሙሉ ንብረታቸው አውድሟል ።
ለሦስት (3) ተከታታይ ሰዓት የቆየው የእሳት ቃጠሎ የአካባቢው ህብረተሰብ ባደረገው እርብርብ ወደ ሌሎች ድርጅቶች ሳይዛመት ማጥፋት የተቻለ ሲሆን ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ላይ መሆኑንም ኮማንደሩ ገልፀዋል።
ምንጭ፦ የሆሳዕና ከተማ ኮሚኒኬሽን ፣ ፎቶ - Tikvah Family Hossana
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ርእሰ መዲና መቐለ አዲስ ከንቲባ እንደተመደበላት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ተናግረዋል። የመቐለ ከተማ ነዋሪዎችን ፀጥታ እና ደህንነት እንዲጠበቅ እንደሚሰራ ገልጸዋል። በሌላ በኩል በጊዜያዊ አስተዳደሩ ብዙ የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን ዶክተር ሙሉ ነጋ አሳውቀዋል። ፓርቲዎቹ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ እንዲሁም የካቢኔ አባል እየሆኑ እንደሆነ…
#Mekelle
የትግራይ ርእሰ መዲና መቐለ ጊዜያዊ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ ናቸው።
ጊዜያዊ ከንቲባው የከተማዋ ነዋሪዎችን የልማት እና የጸጥታ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ዛሬ ከኢ.ፕ.ድ. ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
ከንቲባው የከተማ የታክሲ የትራንስፖርት አገልግሎት እና ሌሎች የመስሪያ ቤት አገልግሎቶች በመጀመር ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
በከተማይቱ ውስጥ አብዛኛው አገልግሎት የሚሰጡ የገበያ ቦታዎች መከፈታቸውን እና ህዝቡም ከስጋት እየወጣ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው እየተመለሰ መሆኑን አቶ አታኽልቲ ኃ/ስላሴ አስታውቀዋል።
More : https://telegra.ph/Mekelle-12-15
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የትግራይ ርእሰ መዲና መቐለ ጊዜያዊ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ ናቸው።
ጊዜያዊ ከንቲባው የከተማዋ ነዋሪዎችን የልማት እና የጸጥታ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ዛሬ ከኢ.ፕ.ድ. ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
ከንቲባው የከተማ የታክሲ የትራንስፖርት አገልግሎት እና ሌሎች የመስሪያ ቤት አገልግሎቶች በመጀመር ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
በከተማይቱ ውስጥ አብዛኛው አገልግሎት የሚሰጡ የገበያ ቦታዎች መከፈታቸውን እና ህዝቡም ከስጋት እየወጣ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው እየተመለሰ መሆኑን አቶ አታኽልቲ ኃ/ስላሴ አስታውቀዋል።
More : https://telegra.ph/Mekelle-12-15
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#HumanRightsWatch
በሪያድ ስደተኞች የማቆያ ማዕከል ውስጥ የሚገኙ አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሆኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች አስከፊ በሆነ አያያዝ ውስጥ እንደሚገኙ ሂዩማን ራይትስ ዋች ገለጸ።
ሕጋዊ የሆኑ ሰነዶች ሳይኖራቸው ሥራ ፍለጋ ወደ ሳዑዲ የገቡ እነዚህ ስደተኞች ተይዘው የሚገኙበት ማዕከል የተጨናነቀ ከመሆኑ ባሻገር በጥበቃዎች ማሰቃየት እንዲሁም ድብደባ እንደሚፈጸምባቸውም አመልክቷል።
የማዕከሉ ጥበቃዎች በጎማ በተሸፈነ ብረት በሚፈጸምባቸው ድብደባ ጉዳት እንደሚደርስባቸው የገለጸው ሂማን ራይትስ ዋች፤ በጥቅምት እና ኅዳር ወራት ውስጥ ቢያንስ ሦስት (3) ለሚሆኑ ስደተኞች ሞት ምክንያት መሆኑን በመግለጫው ላይ ጠቅሷል። (BBC)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በሪያድ ስደተኞች የማቆያ ማዕከል ውስጥ የሚገኙ አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሆኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች አስከፊ በሆነ አያያዝ ውስጥ እንደሚገኙ ሂዩማን ራይትስ ዋች ገለጸ።
ሕጋዊ የሆኑ ሰነዶች ሳይኖራቸው ሥራ ፍለጋ ወደ ሳዑዲ የገቡ እነዚህ ስደተኞች ተይዘው የሚገኙበት ማዕከል የተጨናነቀ ከመሆኑ ባሻገር በጥበቃዎች ማሰቃየት እንዲሁም ድብደባ እንደሚፈጸምባቸውም አመልክቷል።
የማዕከሉ ጥበቃዎች በጎማ በተሸፈነ ብረት በሚፈጸምባቸው ድብደባ ጉዳት እንደሚደርስባቸው የገለጸው ሂማን ራይትስ ዋች፤ በጥቅምት እና ኅዳር ወራት ውስጥ ቢያንስ ሦስት (3) ለሚሆኑ ስደተኞች ሞት ምክንያት መሆኑን በመግለጫው ላይ ጠቅሷል። (BBC)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#TigraiTV
የትግራይ ቴሌቪዥን በጊዜያዊ የትግራይ ክልል አስተዳደር እየተመራ በቅርብ ቀን መደበኛ ስርጭቱን እንደሚጀምር ዛሬ አሳውቋል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው ወደአየር መመለሱንም ለመመልከት ችለናል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የትግራይ ቴሌቪዥን በጊዜያዊ የትግራይ ክልል አስተዳደር እየተመራ በቅርብ ቀን መደበኛ ስርጭቱን እንደሚጀምር ዛሬ አሳውቋል።
የቴሌቪዥን ጣቢያው ወደአየር መመለሱንም ለመመልከት ችለናል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ወደ መቐለ እና ባህር ዳር በረራ እንደሚጀመር ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህር ዳር እንዲሁም መቐለ ከተማዎች አቋርጦ የነበረውን የበረራ አገልግሎት እንደገና እንደሚጀምር አሳውቋል።
መንገደኞች በመመዝገብ በረራዎቹን መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህር ዳር እንዲሁም መቐለ ከተማዎች አቋርጦ የነበረውን የበረራ አገልግሎት እንደገና እንደሚጀምር አሳውቋል።
መንገደኞች በመመዝገብ በረራዎቹን መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#COVID19Ethiopia
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 3,867
• በበሽታው የተያዙ - 300
• ህይወታቸው ያለፈ - 4
• ከበሽታው ያገገሙ - 1,082
አጠቃላይ 117,542 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,813 ሰዎች ህይወት አልፏል ፤ 96,307 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
291 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 3,867
• በበሽታው የተያዙ - 300
• ህይወታቸው ያለፈ - 4
• ከበሽታው ያገገሙ - 1,082
አጠቃላይ 117,542 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,813 ሰዎች ህይወት አልፏል ፤ 96,307 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
291 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ወደ መቐለ በረራ ተጀመረ !
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት አቋርጦት የነበረውን በረራ በዛሬው እለት መጀመሩን ኢዜአ አሳውቋል።
ዛሬ ምሽት ከአዲስ አበባ መንገደኞችን የጫነ የመጀመሪያው አውሮፕላን መቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት አርፏል።
መቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት የደረሰው አውሮፕላን ሌሎች መንገደኞችን አሳፍሮ ወደ አዲስ አበባ መመለሱ ተገልጿል።
በቀጣይ አየር መንገዱ በቀን ሁለት ጊዜ የሚያደርገውን በረራ ይቀጥላል ተብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት አቋርጦት የነበረውን በረራ በዛሬው እለት መጀመሩን ኢዜአ አሳውቋል።
ዛሬ ምሽት ከአዲስ አበባ መንገደኞችን የጫነ የመጀመሪያው አውሮፕላን መቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት አርፏል።
መቐለ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት የደረሰው አውሮፕላን ሌሎች መንገደኞችን አሳፍሮ ወደ አዲስ አበባ መመለሱ ተገልጿል።
በቀጣይ አየር መንገዱ በቀን ሁለት ጊዜ የሚያደርገውን በረራ ይቀጥላል ተብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#UPDATE
በሱማሌ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ የሚንስትሪ ፈተና ዛሬ ታህሳስ 7 ቀን 2013 ጀምሯል።
ፈተናውን በሁሴን ጊሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፈተና ጣቢያ በመገኝት ያስጀመሩት የሱማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ መሀመድ ፈታህ እንደገለፁት ፈተናው ከታህሳስ 7-10 የሚቆይ ሲሆን በፈተናው ላይ 41,889 ተማሪዎች መቀመጣቸውን አስታውቀዋል።
657 የፈተና ጣቢያዎች ዝግጁ መደረጋቸውን የገለፁት ሀላፊው ፣ ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ፈተናው እንደሚሰጥ መናገራቸውን ኢቲቪ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በሱማሌ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ የሚንስትሪ ፈተና ዛሬ ታህሳስ 7 ቀን 2013 ጀምሯል።
ፈተናውን በሁሴን ጊሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፈተና ጣቢያ በመገኝት ያስጀመሩት የሱማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ መሀመድ ፈታህ እንደገለፁት ፈተናው ከታህሳስ 7-10 የሚቆይ ሲሆን በፈተናው ላይ 41,889 ተማሪዎች መቀመጣቸውን አስታውቀዋል።
657 የፈተና ጣቢያዎች ዝግጁ መደረጋቸውን የገለፁት ሀላፊው ፣ ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ፈተናው እንደሚሰጥ መናገራቸውን ኢቲቪ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#AddisAbaba
በቀጣይ ሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ #ጃንሜዳ ወደ ቀድሞ አገልግሎቱ እንደሚመለስ የአዲስ አ በባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በቀጣይ ሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ #ጃንሜዳ ወደ ቀድሞ አገልግሎቱ እንደሚመለስ የአዲስ አ በባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Tigray
አቶ አብርሃ ደስታ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ዋና ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።
አቶ አብርሃ ደስታ በመቐለ ዩንቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ክፍለ ትምህርት አስተማሪ ነበሩ።
በሌላ በኩል አቶ ሚሊዮን ኣብርሃ የደቡብ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተደርገው መሾማቸው ተገልጿል።
ምንጭ፦ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
አቶ አብርሃ ደስታ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ዋና ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል።
አቶ አብርሃ ደስታ በመቐለ ዩንቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ክፍለ ትምህርት አስተማሪ ነበሩ።
በሌላ በኩል አቶ ሚሊዮን ኣብርሃ የደቡብ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተደርገው መሾማቸው ተገልጿል።
ምንጭ፦ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia