TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
'እጅግ እየተባባሰ የመጣው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ'

ትላንት ብቻ በመላው ዓለም ላይ 8,802 ሰዎች በኮቪድ-19 ህይወታቸው አልፏል።

በተመሳሳይ በ24 ሰዓት ውስጥ 575,845 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ በአጠቃላይ 54, 480 , 640 በበሽታው መያዛቸው ሲረጋግጥ ፤ 1, 320, 616 ህይወታቸው አልፏል።

#እራሳችሁን_ጠብቁ!

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#እራሳችሁን_ጠብቁ !

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት አሁንም የጤና ስጋት ሆኖ ቀጥሏል አሉ።

ዶ/ር ሊያ ይህን ያሉት በኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ ዓለም አቀፉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዛሬ ሲከበር ነው።

አጠቃላይ ህዝቡ፣ ሁሉም ተቋማትና የሚመለከታቸው አካላት ስርጭቱን ለመግታት በትብብር አንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

አሁን ላይ ኮቪድ-19 ስርጭት የተስፋፋበት ወቅት በመሆኑ ድርብ ስራና ሃላፊነትን ይጠይቃል ብለዋል።     
በአዲስ አበባ ከተማ፣ በጋምቤላ ክልል እና ከተሜነት በተስፋፋባቸው ሌሎች አካባቢዎች የኤች አይቪ ቫይረስ ስርጭት እየጨመረ መምጣቱን ገልፀዋል።

በግንባታ ቦታዎች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተመሳሳይ የስርጭት መስፋፋት መኖሩን ጠቁመዋል።

ዶክተር ሊያ ፥ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች የህክምና ክትትል ማድረግ እና መድሃኒት በአግባቡ መውሰድ እንዳለባቸው መክረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ቫይረሱ በደማቸው የተገኘባቸው ግለሰቦችን እና በቫይረሱ ምክንያት ወላጆቻውን ያጡ ህጻናት እና አረጋዊያንን በመንከባከበ የህብረተሰቡ ትብብር መጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል - ENA

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia