TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ሰበር ዜና-አብዴፓ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና ከአፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲዊ ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አመራር ጋር ባለፈዉ ሳምንት የጀመሩትን ዉይይት ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጥለዋል፡፡

በዚህ ዉይይት በአገር አቀፍ ደረጃ በመካሄድ ላይ ያለውን ለውጥ በክልል ደረጃ እንዴት መካሄድ እንዳለበት ትኩረቱን ተደርጎበታል፡፡ በውይይቱ መጨረሻ ለውጡን የበለጠ ለማሳካት እንዲቻል ነባር የፓርቲ አመራሮች በአዲስ አመራሮች #እንዲተኩ ተወስንዋል።

ከዚህም በተጨማሪ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ በበለጠ #በማጠናከር ህዝቡ የልማት ተጠቃሚነቱን የበለጠ ለማረጋገጥ እንዲቻል ሁሉም አመራር በጋር ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በሌላም በኩል የክልሉን ወጣቶችን ይበልጥ በማሳተፍ የህዝቡን የልማትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ አመራሮቹ ቃል ገብተዋል፡፡

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia