TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update የፓሪሱ ጥቃት⬇️

ፈረንሳይ በመዲናዋ በሰኔ ወር የፈነዳውን ቦምብ #ያቀነባበረው የኢራን የደህንነት
መስሪያ ቤት መሆኑን አረጋግጫለው አለች፡፡

በወቅቱ በፓሪስ ጎዳና ላይ ከኢራን የተሰደዱ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ሰላማዊ ሰልፍ ላይ እንደነበሩ ተነግሯል፡፡

ይህንንም ተከትሎ ፈረንሳይ የሁለት #ኢራናውያንን እና ከሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ጋር የተያያዙ የባንክ አካውንቶችን አግዳለች፡፡

ከፍንዳታው ጋር በተያያዘም ረዥም ጊዜ የፈጀ ምርመራ ካካሄደች በኋላ ነው ይፋ ማድረጓን ያስታወቀችው፡፡

የኢራን የደህንነት መስሪያ ቤት ኃላፊ የሆኑት ሰይድ ሐሺም #በቀጥታ ትዕዛዙን እንደሰጡ ተገልጿል፡፡

የደህንነት መስሪያ ቤቱ ቃልአቀባይ ፓሪስ የደረሰችበትን ምርመራ ተቀባይነት የለውም ያሉ ሲሆን በጀርመን ተያዙ ተያዙ የተባሉ ዲፕሎማታቸውንም እንዲለቁ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በተጨማሪም ጥቃቱ የተፈጸመው የሁለቱ ሀገራትን የረዥም ጊዜ ወዳጅነት በማይፈልጉ ሴረኞች የተቀነባበረ ነው ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ሲጂቲኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia