TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.3K photos
1.58K videos
216 files
4.33K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#ዓድዋ

እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ !

" ዓድዋ ዛሬ ናት ዓድዋ ትናንት
መቼ ተነሱና የወዳደቁት
ምስጋና ለእነርሱ ለዓድዋ ጀግኖች
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ
አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ
ተናገሪ
የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ

መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !!

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል። የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97…
#ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።


አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር

አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር

አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር

የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር

አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር

#ነዳጅ #ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ_ታምርት_ኤክስፖ2017

#ትፈለጋላችሁ

ጥራት እና ተወዳዳሪ ምርት ካሎት ይፈለጋሉ !
ለየት ያለ እና ጥራት ያለዉ ምርት ያላችሁ ትፈለጋላችሁ!

ማንኛዉም ልዩ፤ ጥራትና ተወዳዳሪ ምርት ያላቸው አምራቾችና ኢንዱስትሪዎች በ #ኢትዮጵያ_ታምርት ኤክስፖ 2017 ላይ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከሚያዝያ 25 እስከ 29/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል።

በዚህ ኤክስፖ መሳተፍ የምትፈልጉ በሙሉ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በመምጣት መመዝገብ ይችላሉ።

📞 ለበለጠ መረጃ በ 0906555552 ወይም 0988080808 ይደውሉ

#ኢትዮጵያታምርት   #ኢንዱስትሪሚኒስቴር
በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አዘጋጅነት በሚዘጋጀው የኢትዮጵያ ታምርት ሩጫ እና ኤክስፖ ተጋብዘዋል

📱 ሩጫው መቼ ነው ?

የኢትዮጵያ ታምርት  የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ መነሻውን መስቀል አደባባይ አድርጎ መስቀል አደባባይ የሚጠናቀቅ ሲሆን #ሚያዚያ_19 /2017 ዓ.ም ይከናወናል።

በዚህ ሩጫ ውድድር ፦
1ኛ ለሚወጡ 300,000 ሺህ ብር
2ኛ ለሚወጡ 200,000 ሺህ ብር
3ኛ ለሚወጡ 100,000 ሺህ ብር ሽልማት ተዘጋጅቷል።

በሁለቱም ፆታ እስከ 10ኛ የሚወጡ አሸናፊዎችም #በሽልማት ይንበሸበሻሉ!

🎽 ቲሸርቱን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኙታል
📞 ለበለጠ መረጃ 0975070707

⚙️ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ መቼ ነው ?

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከሚያዝያ 25 እስከ 29/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል።

ማንኛዉም ልዩ፤ ጥራትና ተወዳዳሪ ምርት ያላቸው አምራቾችና ኢንዱስትሪዎች በ #ኢትዮጵያ_ታምርት ኤክስፖ 2017 ላይ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል።

📞 ለበለጠ መረጃ በ 0906555552 ወይም 0988080808 ይደውሉ

#ኢትዮጵያታምርት   #ኢንዱስትሪሚኒስቴር
TIKVAH-ETHIOPIA
እንኳን ለ84ኛው የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች የድል በዓል (የድል ቀን) አደረሳችሁ ! ክብር ለጀግኖች አርበኞቻችን ይሁን🙏 @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ🇪🇹

ዛሬ 84ኛው ዓመት የኢትዮጵያውያን አርበኞች የድል በዓል እየተከበረ ይገኛል።

የአርበኞች የድል በዓል ለምን ይከበራል ?


ጣሊያን የዓድዋን ድል ለመበቀል በሚል በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቤኒቶ ሙሶሎኒ አማካኝነት፥ ከ1928 እስከ 1933 ዓ.ም ድረስ ኢትዮጵያን ወራ ነበር።

በወቅቱ የነበሩት ኢትዮጵያውያንም ወራሪውን ሀይል ለአምስት ዓመታት በጽናት ታግለው 1933 ዓ.ም ድል ነስተውታል።

የወቅቱ አርበኞቻችን ለሀገራቸው ነጻነት የከፈሉትን መስዋዕትነት እና ያስገኙትን ድል ለማሰብ ነው በየአመቱ ሚያዚያ 27 የኢትዮጵያ አርበኞች የድል በዓል የሚከበረው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
እንኳን አደረሳችሁ !

ፎቶ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ

@tikvahethiopia
#ATTENTION🚨

ከዛሬ ግንቦት 6 / 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት የኩፍኝ ክትባት ይሰጣል።

ወላጆች ልጆቻችሁን አስከትቡ።

ኩፍኝ ምንድነው ?

የኩፍኝ በሽታ የኩፍኝ ቫይረስ በሚባል ረቂቅ ተህዋስ የሚከሰትና በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው የሚዛመት የበሽታ ዓይነት ነው፡፡ የኩፍኝ በሽታ ለብዙ ህጻናት ህመም፣ የአካል ጉዳትና ሞት ምክንያት ከሆኑት በሽታዎች አንዱ ነው፡፡

የበሽታው መተላለፊያ መንገዶች ምንድናቸው ?

➡️ ኩፍኝ በሽታ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው የኩፍኝ በሽታ ከተያዘው ሰው አፍንጫና ጉሮሮ በሚወጡ ፈሳሽና ጠብታዎች ንክኪና በትንፋሽ አማካኝነት ነው፡፡

➡️ የኩፍኝ በሽታ አምጭ ተህዋስ ወይም ቫይረስ በኩፍኝ ከተያዘዉ ሰዉ በከፍተኛ ሁኔታ የመሰራጨት አቅም የሚኖረው የበሽታው ምልክቶች መታየት በሚጀምርበት ወቅት ነው፡፡

➡️ አንድ በኩፍኝ የተያዘ ሰው በአብዛኛው ጊዜ ቫይረሱ ወደ ሰውነቱ ከገባ በኋላ የሽፍታ ምልክቶች በሰውነቱ ከመውጣቱ ከ4 ቀናት በፊት እንዲሁም ሽፍታዎቹ ከወጡ በኋላ እስከ 4 ቀን ድረስ ባለው ጊዜ በሽታውን ወደ ሌሎች ሰዎች በከፍተኛ ሁኔታ ያስተላልፋል፡፡

➡️ ህጻናት በሚሰባሰቡበት ቦታ ማለትም በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ተቋማት እና በሌሎችም ቦታዎች በሽታው በቀላሉ ሊዛመት ይችላል፡፡

የበሽታው ዋና ዋና ምልክቶች ምንድናቸው ?

- ከፍተኛ ትኩሳት፣
- ከራስ ፀጉር ጀምሮ ወደ ሌሎች የሰውነት፣ ክፍሎች የሚዛመት ሽፍታ፣
- የአይን መደፍረስ ወይም መቅላት፣
- ከአፍንጫ የሚወጣ ፈሳሽ መብዛት፣
- የአይን እንባ ማዘል፣
- ሳል እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡

ስላ ኩፍኝ መከላከያ ክትባት ፦ የኩፍኝ መከላከያ ክትባት ህፃናት ከተወለዱ በ9 እና በ15 ወር ዕድሜያቸው በመደበኛው የክትባት አገልግሎት ይሰጣል፡፡

በተጨማሪም የኩፍኝ ክትባት የህፃናትን በሽታ የመከላከል አቅም ለማዳበር በተለያዩ ጊዜያት በዘመቻ ይሰጣል፡፡

የኩፍኝ በሽታን በዘላቂነት መከላከል የሚቻለው ህፃናትን በመደበኛ የክትባት መርሐግብር እና በዘመቻ መልክ የሚሰጠውን የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባትን ማስከተብ ሲቻል ነው፡፡

ልጅዎትን ያስከትቡ !!
#ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ? የብሔራዊ ባንክ መመሪያ በትክክል ምን ይላል ?

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ ባለፈው አመት 2016 ሐምሌ ወር ላይ የውጭ ምንዛሬ ግብይት በነፃ ገበያ እንዲመራ ከወሰነ በኋላ፣ አብሮ ይፋ በተደረገው መመሪያ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ አንዳንድ ማሻሻዎችን ማድረጉን አስታውቋል፡፡

በመመሪያው ላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት መሰረት በማድረግም፣ ከህብረተሰቡ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ወይ ? የሚል ጥያቄ ይነሳል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ይህን በሚመለከት የባንክ ባለሙያዎች ማብራሪያ ጠይቋል፡፡

በዚህ ጉዳይ ዙርያ ማብራሪያቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የብሔራዊ ባንክ ባለሙያ ምን አሉ ?

" ኢትዮጵያ ውስጥ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውጪ፣ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት አይፈቀድም፡፡ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በውጭ ምንዛሪ ወይም ዶላር መገበያየት አይችልም፡፡

ግብይትን በዶላር የሚፈፅሙ ሰዎች፣ የተፈቀደላቸው ብቻ ናቸው፡፡ እነዚህም ዶላር ይዘው ከውጭ የሚመጡ ቱሪስቶች፣ ዲያስፖራዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ከውጭ ሲመጡ እስከ 10 ሺህ ዶላር ይዘው እንዲገቡ ስለሚፈቀድላቸው፣ በጉምሩክ አስመዝግበው ባስገቡት ዶላር መገበያየት ይችላሉ፡፡  "

አገልግሎት ሰጭዎችስ በዶላር ማስከፈል ይችላሉ ?

" እነዚህ ሰዎች በዶላር መገበያየት የሚችሉት፣ አገልግሎታቸውን በውጭ ምንዛሪ እንዲሸጡ ከተፈቀደላቸው ተቋማት ብቻ ነው፡፡

ለምሳሌ ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጭዎች፣ ማለትም ሆቴሎችና አስጎብኝዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለሰጡት አገልግሎተት በዶላር ክፍያ መቀበል እንዲችሉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ያላቸው ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዊ ሆኖ፣ በዶላር ግብይት መፈፀም አይችልም፣ ከተፈቀደላቸው ተቋማትም ቢሆን፡፡

እኔ ኢትዮጵያዊ ሆኜ በዶላር እንዲያስከፍል ወደ ተፈቀደለት ሆቴል ሄጄ በዶላር መጠቀም አልችልም፡፡ ዲያስፖራ ከሆነንክ ግን፣ የሆነ ሆቴል ሔደህ ለተሰጠህ አገልግሎት በዶላር መክፈል ትችላለህ፡፡ ሆቴል ደግሞ ለሰጠው አገልግሎት በዶላር የማስከፈል ፈቃድ ያለው መሆን ይጠበቅበታል፡፡ ከፋዩም፣ አስከፋዩም (ተጠቃሚውና አገልግሎት ሰጪው) በዶላር ለመገበያየት የተፈቀደላቸው ወይም እውቅና የተሰጣቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡

ከአንድ የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ ዶላር ማስተላለፍ ይቻላል ?

" የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፍን (ትራንስፈርን) በተመለከተ፣ ከአንድ የዶላር ሒሳብ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለ ሌላ የዶላር ሒሳብ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፍ አይቻልም፡፡ ለምን ዓላማ ነው የሚተላለፈው ? የሚለው ይታያል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ዕቃ ገዝተህ በዶላር ልክፈል ብትል፣ አንተም በዶላር የመክፈል መብት የለህም፣ ሻጩም በዶላር ክፍያ የመቀበል ፈቃድ የለውም፣ ስለዚህ አይቻልም፡፡

ነገር ግን የዶላር አካውንት ኖሮህ፣ ከውጪ ሀገር እቃ ብትገዛ፣ ለእሱ በዶላር የመክፈል መብት አለህ፡፡ በቀጥታ ለእቃ ሻጩ ነው ዶላሩ የሚተለላለፈው፡፡ ውጭ ሀገር እቃ ወደገዛህበት መደብር ትራንስፈር ይደረጋል/ይተላለፋል፡፡ መረጃ አቅርበህ፣ ባንኩ ያንን መረጃ አይቶ አሳማኝ ሆኖ ካገኘው ይህንን ያደርግልሀል፡፡ ከራስህ ዶላር መፅሐፉን ለሸጠልህ ነጋዴ በቀጥታ ማስተላለፍ ይቻላል፡፡ ዋናው ነገር ለምን አላማ ነው የምታስተላልፈው የሚለው ነው፡፡ "

ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼ ሊጀመር ይችላል ?

" በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼም አይጀመርም፡፡ በየትም ሀገር በውጭ ምንዛሪ ግብይት አይደረግም፡፡ እንደዛ ከሆነ፣ የሚነግርህ ትርጉም የሀገርህን ብር አታምነውም ማለት ነው፡፡ ኢኮኖሚዋ ችግር ላይ የወደቀባት ዚምባብዌ እንኳን ያንን አላደረገችም፡፡

የውጭ ምንዛሪ ፍሰትን ለመጨመር፣ ኤክስፖርትን ለማበረታታት፣ የምታደርጋቸው ማስተካከያዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ከዛ ውጪ፣ ዜጎችህን በዶላር ተገበያዩ ልትል አትችልም፡፡

ለምሳሌ፣ ሪልስቴቶች ወይም አለምአቀፍ ት/ቤቶች የዋጋ እና የክፍያ ተመንን በዶላር ሲያወጡ ይታያል፡፡ ይህ ችግር የለውም፡፡ ክፍያው ሲፈፀም ግን በኢትዮጵያ ብር ነው የምትከፍለው፡፡ "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጣይ ፦
- ለውጭ ጉዞ ዶላር/የውጭ ምንዛሪ እንዴት ነው የሚሰጠው ?
- የባንኮች ቪዛ ካርዶች እንዴት ነው የምንጠቀምባቸው ?
- የባንኮች ቪዛ ካርዶች በሀገር ውስጥ የምንጠቀምበት ዕድል አለ ?
- የዶላር አካውንት/የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ቅድመ ሁኔታ አለ ? በሚሉ ጥያቄዎች ላይ የባለሙያ ማብራሪያ ያቀርባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ መገበያየት ይቻላል ? የብሔራዊ ባንክ መመሪያ በትክክል ምን ይላል ? የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ ባለፈው አመት 2016 ሐምሌ ወር ላይ የውጭ ምንዛሬ ግብይት በነፃ ገበያ እንዲመራ ከወሰነ በኋላ፣ አብሮ ይፋ በተደረገው መመሪያ በውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ አንዳንድ ማሻሻዎችን ማድረጉን አስታውቋል፡፡ በመመሪያው ላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት መሰረት በማድረግም፣ ከህብረተሰቡ…
#ኢትዮጵያ

" የዶላር ባንክ ሒሳብ ለመክፈት የዶላር ምንጭህ መታወቅ አለበት፡፡ ከዚሁ በጥቁር ገበያ እየለቃቀምክ ማስገባት አትችልም፡፡ ይህ ህገወጥ ነው " - የባንክ ባለሙያ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከብሔራዊ ባንክ ባለሙያ ጋር ፦
- ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሬ መገበያያት ይቻላል ወይ ?
- አገልግሎት ሰጪዎች በዶላር ማስከፈል ይችላሉ ?
- ከአንድ የባንክ ሒሳብ ወደሌላ የባንክ ሒሳብ ዶላር ማስተላለፍ ይቻላል ?
- ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ግብይት መቼ ሊጀመር ይችላል ?

የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ማብራሪያ ማቅረቡ ይታወሳል።

ለዛሬ ደሞ ከኚሁ ባለሙያ እንዲሁም ከአንድ ሌላ የባንክ ባለሙያ ጋር የተለያዩ ማብራሪያ የሚፈልጉ ጥያቄዎችን በማንሳት ያዘጋጀውን ማብራሪያ ያቀርባል።

ለውጭ ጉዞ ዶላር/የውጭ ምንዛሪ እንዴት ነው የሚሰጠው ?

" ለጉዞ ከሆነ ከራስህ ዶላር አካውንት ወይም ዶላር አካውንትም ባይኖርህ ከባንኮች ወይም ከተፈቀደላቸው የውጭ ምንዛሪ ሱቆች በግዢ እስከ 10 ሺህ ዶላር ይዘህ መውጣት ትችላለህ፡፡ ለዚህ ግን ማሳየት ያሉብህ ማስረጃዎች ይኖራሉ፣ የጉዞ ሰነዶች ማለት ነው፣ ለምሳሌ ቪዛ እና የአየር ቲኬት የመሳሰሉት፡፡ "

የባንኮች ቪዛ ካርዶች እንዴት ነው የምንጠቀምባቸው ?

" የንግድ ባንኮች ቪዛ/ማስተር ካርዶች ሁለት አላማ አላቸው፡፡

አንደኛው፣ ዳያስፖራዎች ከካርዳቸው በቀጥታ ወደ ሀገር ቤት በቀላሉ ዶላር እንዲልኩ ያስችላቸዋል፡፡ አሜሪካ ያለው ዳያስፖራ የአሜሪካ ባንክ ካርድ ይኖረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ተቀባይ ደግሞ የንግድ ባንክ ማስተር ካርድ ይኖረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለው ተቀባይ በካርዱ በቀላሉ ዶላር ሊያስተላልፍለት ይችላል፡፡ ተቀባዩ ደግሞ ከውጭ ዶላር ሊላክልኝ ስለሆነ የዶላር አካውንት ክፈቱልኝ ይላል፡፡ ከዛም ላኪው ከካርዱ በቀጥታ ወደ ተቀባዩ አካውንት ዶላር ያስተላልፍለታል፡፡

ሁለተኛው ጠቀሜታ፣ ከዚህ ወደ ውጭ ስትወጣ እስከ 10 ሺህ ዶላር መውሰድ ትችላለህ፡፡ ይህን በካሽ ከሚሰጡህ ይልቅ በካርድ ቢሰጡህ ይሻላል የሚል ነው፡፡ ስለዚህ ከባንክ ወደ ውጭ ይዘህ ለመውጣት የተፈቀደልህ ዶላር ማስተር ካርዱ ላይ ይጫናል ማለት ነው፡፡ ከዛም ካርዱን ይዘህ በመውጣት እንደ ኤቲኤም ትጠቀምበታለህ፡፡ "

ማስተር ካርዱን በውጭ ሀገራት ብቻ ነው የምንጠቀምበት ?

ስለዚህ ጉዳይ ያብራሩልን ማንነቴ አይጠቀስ ያሉን ሁለተኛ የባንክ ባለሙያ ፥ ቪዛ ካርዱ የሚጠቅመው ዶላር ይዞ ለመውጣት እና እዛው እንደ ኤቲኤም ለመጠቀም ነው ብለዋል፡፡

ካርዱ ላይ የሚጫነው ዶላር/የውጭ ምንዛሪ በባንክ የተፈቀደ ብቻ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ካርዱን ስላወጣህና አካውንትህ ውስጥ ዶላር ስላለህ ብቻ ካርዱ ላይ አይጫንም፡፡ አሳማኝ በሆነ ምክንያት የውጭ ጉዞ መኖሩ ከተረጋገጠ በኋላ ይዘህ እንድትወጣ የተፈቀደልህን ዶላር ካርዱ ላይ ይጭኑልሃል፡፡

ከውጭ ሀገር ከተመልስክ በኋላ፣ ካርድህ ውስጥ የተጫነውን ዶላር ካልጨረስከው ያልተጠቀምክበት ዶላር ካርዱ ውስጥ ካለ እዚህ ሀገር ካለ ኤቲኤም ማሽን ልታወጣው ትችላለህ፡፡ ግን ኤቲኤም ማሽኑ ዘርዝሮ ነው በብር የሚሰጥህ በዶላር አይሰጥህም፡፡

ለሀገር ውስጥ ግብይት ልትጠቀምበት አትችልም፡፡ ምክንያትም ቪዛ ካርድ የሚጠይቅ ግብይት የለም እዚህ ሀገር፡፡ ነገር ግን ካርድህ ውስጥ ያለውን ዶላር (ያልተጠቀምክበትን) ለውጭ ግብይት ልትጠቀምበት ትችላለህ፡፡ የካርድ ቁጥርህን በመናገር የፈለከውን ክፍያ ትፈፅምበታለህ፡፡ ለምሳሌ የቪዛ ክፍያ የሚጠይቁ ኤምባሲዎች አሉ ' በዶላር ክፈል ' ይሉሀል፡፡ ቪዛ ካርድ ካለህ (ቀድሞ ዶላር የተጫነበት) የካርድ ቁጥሩን ትነግራቸውና ከዛ መቀነስ ይችላሉ፡፡  "

የባንኮች ቪዛ ካርዶች በሀገር ውስጥ የምንጠቀምበት ዕድል አለ ?

" ቪዛ ካርዶቹ ብርም ሊጫንባቸው ይችላል፡፡ ንግድ ባንኮች ካርዶቹን ከዶላር በተጨማሪ ብርም ከጫኑባቸው እዚህ እንደ ኤቲኤም ልትጠቀምባቸው ትችላለህ፡፡ እንደዛ የሚያደርጉ ባንኮች አሉ፡፡

ለምሳሌ ፦ አንዳንድ ባንኮች በቪዛ ካርዳችሁ መጥታችሁ በፖስ ማሽን ተጠቀሙ የሚል ማስታወቂያ ሲያስነግሩ እንሰማለን፡፡ ይህ ማለት ቪዛ ካርዳቸው ከዶላር በተጨማሪ ብርም ተጭኖበታል ማለት ነው፡፡ ሁለቱንም አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል ቪዛ ካርዱ፡፡

ፖስ ማሽኑ እና ኤቲኤም ማሽኑ ቪዛ ካርዶችን ያነብባል፡፡ ይህ ግን እንደ ባንኩ ምርጫ ይወሰናል፡፡ ሁለቱንም እንዲያገለግል (ዱዋል ማለት ነው ብርም ዶላርም እንዲጫንበት) ሊያደርግ ይችላል ወይም ለውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ብቻ እንዲሆን ሊያደርግ ይችላል።

ቪዛ ካርዱ ዱዋል (ለሁለቱም የሚያገለግል) ካልሆነ ግን አንዴ ከተጠቀምክበት በኋላ ከጥቅም ውጪ ነው የሚሆነው፡፡ ሁሌም ወደ ውጭ አትመላለስም፡፡ "

የዶላር አካውንት/የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ቅድመ ሁኔታ አለ ?

" የዶላር ባንክ ሒሳብ ለመክፈት፣ የዶላር ምንጭህ መታወቅ አለበት፡፡ ከዚሁ በጥቁር ገበያ እየለቃቀምክ ማስገባት አትችልም፡፡ ይህ ህገወጥ ነው፡፡ ከውጭ የሚገባልህ የደመወዝ ወይም የስጦታ አለያም የክፍያ ዶላር እንዳለህ ማስረዳትና ለዚያ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅብሀል፡፡

በካሽ ይዘህ ስትሔድ ደግሞ ከውጭ ያስገባኸው ዶላር ስለመሆኑ፣ በጉምሩክ በህጋዊነት የገባ መሆኑን የሚያሳይ ሰነድ ማቅረብ አለብህ፡፡ ምክንያቱም ከውጭ ስትገባ አስመዝግበህ ነው እስከ 10 ሺህ ዶላር ድረስ ይዘህ የምትገባው፡፡ ስለሆነም የዶላር የባንክ ሒሳብ/ዶላር አካውንት ለመክፈት ቅድመ ሁኔታው፣ የዶላር ምንጭህን ማሳወቅ ነው፡፡ "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኢትዮጵያ #ረቂቅአዋጅ

የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መሬትን በሊዝ በባለቤትነት መያዝ የሚያስችላቸው የአዋጅ ረቂቅ ነገ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል።

የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት " ባለቤት ' ወይም  " ባለይዞታ " የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣው ይህ " የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበት " ወይም " ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል መሬት የሚያገኙበትን " ህጋዊ አሰራር ለመዘርጋት ነው።

ረቂቅ አዋጁ ምን ይላል ?

- ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው ግለሰቦች በኢትዮጵያ መሬትን፣ የመኖሪያ ቤትን ወይም ተያያዥ ግንባታዎችን በባለቤትነት ለመያዝ፤ ቢያንስ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ሊመድቡ እንደሚገባ ይደነግጋል።

- በውጭ ዜጋ " በሊዝ ባለይዞታነት " ወይም " ባለቤትነት " የሚያዝ መሬት ወይም የመኖሪያ ቤት፤ " የማይንቀሳቀስ ንብረት " ተደርጎ ይወሰዳል። " ሊዝ "  ማለት " አግባብነት ባለው ህግ መሰረት በጊዜ በተገደበ ውል ለመኖሪያ ቤት ግንባታ ዓላማ የሚውል የከተማ ወይም የገጠር መሬት የሚገኝበት የመሬት ይዞታ ስሪት " ነው።

- ማንኛውም የውጭ ዜጋ በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ሊሆን የሚችለው በአዋጁ የተዘረዘሩ ቅደመ ሁኔታዎችን ሲያሟላ ነው።

እነዚህም ፦
° የውጭ ዜጋው ስም፣ ዜግነት እና ሌሎችን ማንነትን የሚገልጹ ህጋዊ ሰነዶችን ማቅረብ አለበት።
° የውጭ ዜጋው የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለመብት ለመሆን የሚያስፈልግ አነስተኛ የገንዘብ መጠን ለማሟላት የሚያስችል በቂ አቅም ያለው መሆን አለበት።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ለመሆን፤ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም።
° የውጭ ዜጋው የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆን ይገባዋል።

እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟላ አንድ የውጭ ዜጋ ከከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የሚሰጥ ፈቃድ ሊያገኝ ይገባዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ " የፈቃድ ይሰጠኝ " ማመልከቻ ላቀረበ የውጭ ዜጋ፤ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ በ15 ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት ይጠበቅበታል።

- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከውጭ ዜጎች የሚጠበቀውን የአነስተኛ ገንዘብ መጠን ከፍ ወይም ዝቅ የሚያደርግ የእያንዳንዱን የሊዝ ቦታ ወይም ቤት ስፋት እንዲሁም የሊዝ ይዞታዎችን ወይም ቤቶችን አጠቃላይ ቁጥር የሚወስን መመሪያ የማውጣት ስልጣን በአዋጅ ረቂቁ ተሰጥቶታል። መመሪያውን የሚያወጣው፤ የቤቶች ገበያ ወቅታዊ ሁኔታን፣ የከተሞች የማይንቀሳቀስ ንብረት አማካይ ዋጋን፣ የውጭ ዜጎች በቤቶች ገበያ ያላቸውን የተሳትፎ መጠን እና የአዋጁን ዓላማ ለማሳካት የሚረዱ ሌሎች ምክንያቶችን መሰረት በማድረግ ነው።

- የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ፤ የተወሰኑ ሀገራት ዜጎችን ወይም ዜግነት የሌላቸው የውጭ ሀገር ሰዎችን በኢትዮጵያ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ እንዳይሆኑ #ሊከልክል ይችላል።

- ለውጭ ዜጎች የተገደቡ ልዩ ቦታዎች እና የድንበር አካባቢዎችም እንዲሁ በሚያወጣ መመሪያ ይወሰናሉ።

- በውጭ ዜጎች ላይ የተጣሉ ሌሎች ገደቦችም አሉ።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ለመሆን ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋም ወይም ምንጭ ገንዘብ መበደር ወይም ካፒታል ማሰባሰብ አይችልም።
° የውጭ ዜጎች ይህን ጉዳይ ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ የሊዝ፣ የቤት ግዢ፣ የግንባታ ፈቃድ ወይም ተያያዥ የመንግስታዊ አገልግሎት ክፍያዎችን መክፈል ያለባቸው በኢትዮጵያ ተቀባይነት ባለው የውጭ ምንዛሬ ብቻ ነው።
° ማንኛውም የውጭ ዜጋ በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ ለዜጎች በሚሰሩ የጋራ መኖሪያ ህንጻዎች ውስጥ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት መሆን አይችልም። ይህ ገደብ በግል እና በመንግስት አጋርነት ወይም በተመሳሳይ የቤቶች ልማት ማዕቀፍ በፌደራል ወይም በክልል መንግስታት የሚገነቡ መኖሪያ ቤቶችን አያካትትም። ለውጭ ዜጎች የተቀመጠው ገደብ በእነዚህ አካላት አማካኝነት ለትርፍ ዓላማ ተገንብተው ለሽያጭ የሚቀርቡ ቤቶች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ የነበረው የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት የግል ዘርፍን ጨምሮ ሌሎች አካላት እንዲሳተፉ የሚያስችለው ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መተላለፉን የሚኒስትሮች ምክር ቤት አስታወቀ።

በሀገሪቱ ባለፉት ዓመታት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ መቆየቱን ያስታወሰው ምክር ቤቱ፣ ከዘርፉ እያደገ ከመጣው ፍላጎት አንፃር መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ የግል ዘርፉን፣ የሕብረት ሥራ ማሕበራትንና የሙያ ማሕበራትን ማሳተፍ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝቧል።

ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምጽ ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 45ኛ መደበኛ ስብሰባው በበርካታ ጉዳዮች ላይ ከተወያየ በኋላ ውሳኔ ያሳለፈው ምክርቤቱ የስርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን በተጨማሪነት ለፓርላማው እንዲተላለፍ መወሰኑ ካፒታል ለመረዳት ተችሏል። #CAPITAL

@tikvahethiopia