TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.4K photos
1.58K videos
216 files
4.33K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
"#የማያዳግም እርምጃ ተወስዷል‼️"

ምዕራብ ኦሮሚያ እና ኦሮሚያን ከበኒ ሻንጉል ጉሙዝ መስተዳድር ጋር በሚያዋስኑ ድንበሮች ባለፉት ተከታታይ ወራት በርካታ ሰዉ በገደሉ እና ባፈናቀሉ ታጣቂዎች ላይ «የማያዳግም» ያለዉን እርምጃ መዉሰዱን ባካባቢዉ የሠፈረዉ ጦር አስታወቀ።

በቅርቡ «ኮማንድ ፖስት» በሚል መጠሪያ ወደ አካባቢዉ የዘመተዉ ጦር ዛሬ ባሰራጨዉ መግለጫ እንዳለዉ ቁጥራቸዉን ያልጠቀሰዉ የታጠቁ «ፀረ ሠላም» ኃይላት እጅ ሰጥተዋል፣ እጅ ባልሰጡት ላይ ደግሞ የኃይል እርምጃ ወስዶ «አበረታች» ያለዉን ዉጤት አስመዝግቧል።

ሰዉ የገደሉ፤ ሕዝብ ያንገላቱ፣ የዘረፉ፣ ያፈናቀሉና መንገድ የዘጉ ኃይላትን #መያዙንም አስታዉቋል።

በመግለጫዉ መሠረት ጦሩ፣ ከያዛቸዉ ኃይላት ላይ በርካታ የጦር መሳሪያ እና በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ #ማርኳልም

ሠላምን ያዉካሉ በተባሉት ኃላት ላይ ጠንካራ እርምጃ በመወሰዱ #ተዘግተዉ የነበሩ መንገዶች፣የንግድ መደብሮች፣ የጤና እና የሌሎች አገልግሎት መስጪያ ተቋማት #መከፈታቸዉን መግለጫዉ ጠቅሶ፣ ዝርዝሩን ወደፊት ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታዉቋል።

የኦሮሚያ የጤና እና የትምሕርት ቢሮዎች በአብዛኛዉ የምዕራብ ኦሮሚያ የጤና እና የትምሕርት አገልግሎት መቋረጡን ትናንት አስታዉቀዉ ነበር።

ምዕራብ ኦሮሚያ፣ ኦሮሚያን ከበኒ ሻንጉል ጉሙዝ ጋር በሚያዋስኑ የድንበር ግዛቶች ካለፈዉ መስከረም ጀምሮ በተባባሰዉ ግጭት በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች መገደላቸዉ፣ በመቶሺሕ የሚቆጠሩ መፈናቀላቸዉ እና በርካታ ሐብትና ንብረት ወድሙ ወይም መዘረፉ በተደጋጋሚ ሲዘገብ ነበር።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ
@tsegabwolde @tikvahethiopia