TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#NobelPeacePrize

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የዓለም የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን በማስመልከት የሰላም ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ የእውቅና መድረክ የፊታችን እሁድ በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል፡፡

በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች፣ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በሚሊኒየም አዳራሽ የሚከናወነው ይህ የደስታ መግለጫ ዝግጅት እሁድ ጥቅምት 9፣2012 ዓ.ም ከቀኑ 11 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት እንደሚዘልቅ የሰላም ሚኒስቴር መግለጫ አስታውቋል።

Via #WaltaTV
@tsehabwolde @tikvahethiopia
#Ameen

አቢሲኒያ ባንክ ‘አሚን’ የተሰኘ እና የሸሪዓ ህግጋትን የተከተለ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጥ ቅርንጫፍ ዛሬ አስመርቋል። በሰሜን ሆቴል አካባቢ የተከፈተው አሚን ባንክ ከወለድ ነፃ አገልግሎትን ለሚሹ ደንበኞቹ አገልግሎት በመስጠት ተጠቃሚ የሚደርግ መሆኑን የአቢሲኒያ ባንክ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዳይሬክተር አብዱልቃድር ሬድዋን ገልጸዋል፡፡

#waltatv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia