"የኢትዮጵያ መንግስት ምን እንደሚጠብቅ አልገባንም!" አቶ ጋአስ አህመድ
በትላንትናው ዕለት ከጅቡቲ የመጡ ወታደሮች "ኦብኖ" በሚባል አካባቢ ጥቃት ፈፅመው የ16 ሰዎችን ህይወት ማጥፋታቸውን የአፋር የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ሊቀመንበር አቶ ጋአስ አህመድ ለTIKVAH-ETH በላኩት የድምፅ መልዕክት ገልፀዋል። አቶ ጋአስ እንደሚሉት ወታደሮቹ የመጡት ከጅቡቲ ነው፤ ከባድ መሳሪያም የታጠቁ ነበሩ፤ ስልጠናም የወሰዱ ናቸው። እነዚህ ወታደሮች የሲቪል ልብስ በመልበስ ነው ጥቃት የፈፀሙት ያሉት አቶ ጋአስ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ምን እንደሚጠብቅ አልገባንም ሲሉ ተናግረዋል። መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ካልቻለ የዜጎችን ህይወት መታደግ አይቻልም፤ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት ጥቃት የራሱን ቤተሰብ እና ንብረት በራሱ አቅም እየተከላከለ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። በጅቡቲ መንግስት የሚታገዙ ወታደሮችና ታጣቂዎች በጣም ብዙ ህይወት እያጠፉና ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ፤ ይህ ጉዳይ እጅግ በጣም አሳዝኝ ነው መንግስት አስፈላጊውን ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ሲሉ አቶ ጋአስ አህመድ አሳስበዋል።
----------
በጉዳዩ ላይ ምላሽ መስጠት የምትፈልጉና ተጨማሪ መረጃ ያላችሁ የመንግስት አካላት በ @tsegabwolde ወይም በ @tsegabtikvah ላይ የድምፅ መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ!
TIKVAH ETH FAMILY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በትላንትናው ዕለት ከጅቡቲ የመጡ ወታደሮች "ኦብኖ" በሚባል አካባቢ ጥቃት ፈፅመው የ16 ሰዎችን ህይወት ማጥፋታቸውን የአፋር የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ሊቀመንበር አቶ ጋአስ አህመድ ለTIKVAH-ETH በላኩት የድምፅ መልዕክት ገልፀዋል። አቶ ጋአስ እንደሚሉት ወታደሮቹ የመጡት ከጅቡቲ ነው፤ ከባድ መሳሪያም የታጠቁ ነበሩ፤ ስልጠናም የወሰዱ ናቸው። እነዚህ ወታደሮች የሲቪል ልብስ በመልበስ ነው ጥቃት የፈፀሙት ያሉት አቶ ጋአስ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ምን እንደሚጠብቅ አልገባንም ሲሉ ተናግረዋል። መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ካልቻለ የዜጎችን ህይወት መታደግ አይቻልም፤ የአፋር ህዝብ ከሚደርስበት ጥቃት የራሱን ቤተሰብ እና ንብረት በራሱ አቅም እየተከላከለ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል። በጅቡቲ መንግስት የሚታገዙ ወታደሮችና ታጣቂዎች በጣም ብዙ ህይወት እያጠፉና ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ፤ ይህ ጉዳይ እጅግ በጣም አሳዝኝ ነው መንግስት አስፈላጊውን ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ሲሉ አቶ ጋአስ አህመድ አሳስበዋል።
----------
በጉዳዩ ላይ ምላሽ መስጠት የምትፈልጉና ተጨማሪ መረጃ ያላችሁ የመንግስት አካላት በ @tsegabwolde ወይም በ @tsegabtikvah ላይ የድምፅ መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ!
TIKVAH ETH FAMILY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ላለፉት 2 ቀናት ዝግ ሆኖ የቆየው አዲስ አበባ ከተማን ከባህርዳር ከተማ የሚያገናኘው መንገድ ዛሬ ተከፍቷል።
#ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ እንኳን ደስ አላችሁ! ለማለት ይወዳል። የህክምና ኮሌጁ የ3ኛው የጣና ሽልማትን በጤና መረጃ ዘርፍ አሸንፏል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2012
የኢሬቻ በዓል ቡራዩ በሚገኘው መልካ አቴቴ እየተከበረ ይገኛል፡፡ በመልካ አቴቴ የኢሬቻ በዓል ላይ የጋሞ አባቶችና ሌሎች የጋሞ ብሔረሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡
Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢሬቻ በዓል ቡራዩ በሚገኘው መልካ አቴቴ እየተከበረ ይገኛል፡፡ በመልካ አቴቴ የኢሬቻ በዓል ላይ የጋሞ አባቶችና ሌሎች የጋሞ ብሔረሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡
Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አልማ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምሥራቅ በለሳ ወረዳ በአማራ አቀፍ ልማት ማኅበር (አልማ) ድጋፍ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል።
https://telegra.ph/ETH-10-13-2
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምሥራቅ በለሳ ወረዳ በአማራ አቀፍ ልማት ማኅበር (አልማ) ድጋፍ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል።
https://telegra.ph/ETH-10-13-2
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba
ትናንት ማምሻውን በአዲስ አበባ ከተማ ፍልውሃ አካባቢ 2 የፌደራል ፖሊስ አባላት ህይወታቸው ማለፉን የፌደራል ፖሊስ ኮምንኬሽን ለሸገር ተናግሯል። 4 አባላት መቁሰላቸውንም ተሰምቷል። ምክንያቱም ምን እንደሆነ የተጠየቃት የስራ ሀላፊ የአንድ አባል ቀልድ መሳይ ብሽሽቅ እንደሆነ ተናግረዋል። በተጀመረውም ብሽሽቅ አንደኛው አባል 2 ጓደኞቹን በእጁ በያዘው መሳሪያ ተኩሶ መግደሉን የፌደራል ፖሊስ ለሸገር ራድዮ ተናግረዋል። ህይወት ያጠፋው አባልም እንደቆሰለ እና ጉዳዩ በምርመራ እንደሆነ ታውቋል። ሸገር የፌደራል ፖሊስ አባላቱ ፍልውሀ አካባቢ ምን ያደርጉ እንደነበር ጠይቋል። የኮሚንኬሽን ዳይሬክተሩ አቶ ጄላን አባሎቹ በአካባቢው የሚኖሩበት ቦታ አለ በጥበቃም የተሰየሙ ነበሩ የሚል መልስ ሰጥተዋል።
Via ሸገር ኤፍ ኤም ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትናንት ማምሻውን በአዲስ አበባ ከተማ ፍልውሃ አካባቢ 2 የፌደራል ፖሊስ አባላት ህይወታቸው ማለፉን የፌደራል ፖሊስ ኮምንኬሽን ለሸገር ተናግሯል። 4 አባላት መቁሰላቸውንም ተሰምቷል። ምክንያቱም ምን እንደሆነ የተጠየቃት የስራ ሀላፊ የአንድ አባል ቀልድ መሳይ ብሽሽቅ እንደሆነ ተናግረዋል። በተጀመረውም ብሽሽቅ አንደኛው አባል 2 ጓደኞቹን በእጁ በያዘው መሳሪያ ተኩሶ መግደሉን የፌደራል ፖሊስ ለሸገር ራድዮ ተናግረዋል። ህይወት ያጠፋው አባልም እንደቆሰለ እና ጉዳዩ በምርመራ እንደሆነ ታውቋል። ሸገር የፌደራል ፖሊስ አባላቱ ፍልውሀ አካባቢ ምን ያደርጉ እንደነበር ጠይቋል። የኮሚንኬሽን ዳይሬክተሩ አቶ ጄላን አባሎቹ በአካባቢው የሚኖሩበት ቦታ አለ በጥበቃም የተሰየሙ ነበሩ የሚል መልስ ሰጥተዋል።
Via ሸገር ኤፍ ኤም ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆናቸውን ተከትሎ በተለያዩ ከተሞች የደስታ መግለጫ ሰልፎች ተደርገዋል፦ ዱከም፣ ገላን፣ ሻሸመኔ፣ አምቦ፣ ወሊሶ፣ ሱሉልታ፣ ባሌ ሮቤ፣ ጅማ፣ መቱ፣ በደሌ፣ ባቱ፣አዳማ፣ ጅማ ዞን /ጌራ/፣ ድሬዳዋ፣ ቢሾፍታ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ ሀረር፣ጭሮ፣አሶሳ/ቤኒሻንጉል ጉምዝ/ ደንገሃቡር/ሱማሌ ክልል/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆናቸውን ተከትሎ በተለያዩ ከተሞች የደስታ መግለጫ ሰልፎች ተደርገዋል፦ ዱከም፣ ገላን፣ ሻሸመኔ፣ አምቦ፣ ወሊሶ፣ ሱሉልታ፣ ባሌ ሮቤ፣ ጅማ፣ መቱ፣ በደሌ፣ ባቱ፣አዳማ፣ ጅማ ዞን /ጌራ/፣ ድሬዳዋ፣ ቢሾፍታ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ ሀረር፣ጭሮ፣አሶሳ/ቤኒሻንጉል ጉምዝ/ ደንገሃቡር/ሱማሌ ክልል/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቢሾፍቱ በልምምድ ላይ የነበረ አንድ የኢትዮጵያ የጦር አውሮፕላን ተከስክሶ የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል። አውሮፕላኑ ዛሬ ጠዋት ቢሾፍቱ ከሚገኘው የአየር ሃይል ካምፕ በመነሳት በልምምድ ላይ እያለ በምስራቅ ሸዋ ዞን አደአ ወረዳ ኡኬ ደንካካ በተሰኘ ቦታ መከስከሱን የምስራቅ ሸዋ ዞን ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አበራ ያሚ ለዶቸ ቨለ አረጋግጠዋል። በአደጋው የሁለት አብራሪዎች ህይወት ማለፉንም አቶ…
#RIP
ሻለቃ ሰበሪ ቶፊቅ🕯ሻምበል ኃየሎም ተስፋይ!
#BISHOFTU
በአደጋው በደረደበት ወቅት ኢንስትራክተር አብራሪ ሻለቃ ሰብሪ ቶፊቅ ከተዋጊ ጄቱ ተስፈንጥሮ የወጣ ቢሆንም፣ ፓራሹቱ ሊዘረጋለት ባለመቻሉ ሕይወቱ እንዳለፈ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። ሌላው በአደጋው ሕይወቱን ያጣው ሠልጣኝ አብራሪ ሻምበል ኃየሎም ተስፋይ ነው፡፡
ሻለቃ ሰብሪ በ1999 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት በከፍተኛ ማዕረግ እንደተመረቀና አየር ኃይሉን ከአሥር ዓመት በላይ እንዳገለገለ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ድሬዳዋ ተወልዶ ያደገው ሻለቃ ሰብሪ በጂማ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ተማሪ የነበረ ቢሆንም፣ ለበረራ በነበረው ፍቅር የምሕንድስና ትምህርቱን አቋርጦ ወደ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት እንደገባ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ በትምህርቱም በከፍተኛ ውጤት ያስመዘግብ እንደነበር ገልጸው፣ ሲመረቅ ከክፍሉ በአንደኛ ደረጃ እንዳጠናቀቀ ተናግረዋል፡፡ ሻለቃ ሰብሪ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነበር፡፡
ሱኮይ 27 ተዋጊ አውሮፕላኖች የተገዙት በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ነበር!
Via Reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሻለቃ ሰበሪ ቶፊቅ🕯ሻምበል ኃየሎም ተስፋይ!
#BISHOFTU
በአደጋው በደረደበት ወቅት ኢንስትራክተር አብራሪ ሻለቃ ሰብሪ ቶፊቅ ከተዋጊ ጄቱ ተስፈንጥሮ የወጣ ቢሆንም፣ ፓራሹቱ ሊዘረጋለት ባለመቻሉ ሕይወቱ እንዳለፈ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። ሌላው በአደጋው ሕይወቱን ያጣው ሠልጣኝ አብራሪ ሻምበል ኃየሎም ተስፋይ ነው፡፡
ሻለቃ ሰብሪ በ1999 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት በከፍተኛ ማዕረግ እንደተመረቀና አየር ኃይሉን ከአሥር ዓመት በላይ እንዳገለገለ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ድሬዳዋ ተወልዶ ያደገው ሻለቃ ሰብሪ በጂማ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ተማሪ የነበረ ቢሆንም፣ ለበረራ በነበረው ፍቅር የምሕንድስና ትምህርቱን አቋርጦ ወደ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት እንደገባ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ በትምህርቱም በከፍተኛ ውጤት ያስመዘግብ እንደነበር ገልጸው፣ ሲመረቅ ከክፍሉ በአንደኛ ደረጃ እንዳጠናቀቀ ተናግረዋል፡፡ ሻለቃ ሰብሪ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነበር፡፡
ሱኮይ 27 ተዋጊ አውሮፕላኖች የተገዙት በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ነበር!
Via Reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#PMOEthiopia
ዛሬ ማለዳ የካቢኔ አባላት በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ተገኝተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት በማግኘታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል። ለአመራሩ እንዲሁም ለተገኘው ስኬት ያላቸውን አድናቆት ለመግለጽ የወርቅ ሀብል ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያበረከቱ ሲሆን "እውነት ፍቅር ያሸንፋል" የሚል ጽሑፍ ተቀርጾበታል።
#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ ማለዳ የካቢኔ አባላት በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ተገኝተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት በማግኘታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል። ለአመራሩ እንዲሁም ለተገኘው ስኬት ያላቸውን አድናቆት ለመግለጽ የወርቅ ሀብል ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያበረከቱ ሲሆን "እውነት ፍቅር ያሸንፋል" የሚል ጽሑፍ ተቀርጾበታል።
#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኬንያዊቷ ለ16 ዓመታት ተይዞ የነበረውን የሴቶች ማራቶን ሪከርድ ሰበረች!
ዛሬ በተካሄደው ቺካጎ ማራቶን ኬንያዊቷ ብርጊድ ኮስጊ በ 2003 ፓውላ ራድ ክሊፍ ያስመዘገበችውን የሴቶች የማራቶን ሪከርድ 2:14:04 በመግባት ከ 16 ዓመታት በውኋላ ሪከርዱን መስበር ችላለች።
@tikvahethsport @GoitomH @kidusyoftahe
ዛሬ በተካሄደው ቺካጎ ማራቶን ኬንያዊቷ ብርጊድ ኮስጊ በ 2003 ፓውላ ራድ ክሊፍ ያስመዘገበችውን የሴቶች የማራቶን ሪከርድ 2:14:04 በመግባት ከ 16 ዓመታት በውኋላ ሪከርዱን መስበር ችላለች።
@tikvahethsport @GoitomH @kidusyoftahe
#GAMBELA
ከጋምቤላ ከተማ 38 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር ዛሬ በቁጥጥር ሥር ዋሉ። የክልሉ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አቶው አኮት እንደገለጹት መሣሪያዎቹ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት በክልሉ ጸጥታ ኃይል፣ ፌዴራል ፖሊስና መከላከያ ሠራዊት ለሦስት ቀናት ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት ነው።
የጦር መሣሪያዎቹና ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት ከአንድ ግለሰብ ቤት ኮድ 3 ሠሌዳ ቁጥር ቁጥር አዲስ አበባ 55966 በሆነ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር ነው። በክልሉ እየተስፋፋ ያለውን ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያዎች ዝውውር ለመግታት የክልሉና የፌዴራል ጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው በመሥራት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ኡቲያንግ ኡቻን እንተናገሩት ክልሉ ድንበር ያለው ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያዎች ዝውውር መበራከቱን ተናግረዋል። ችግርን ለመካለካል በሚደረገው ጥረት ሕዝቡና ጸጥታ አካላት ለሚያደርጉት ጥረት አመስግነው፣ በቀጣይም ቁጥጥሩ ይጠናከራል ብለዋል።
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከጋምቤላ ከተማ 38 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር ዛሬ በቁጥጥር ሥር ዋሉ። የክልሉ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አቶው አኮት እንደገለጹት መሣሪያዎቹ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት በክልሉ ጸጥታ ኃይል፣ ፌዴራል ፖሊስና መከላከያ ሠራዊት ለሦስት ቀናት ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት ነው።
የጦር መሣሪያዎቹና ተጠርጣሪዎቹ የተያዙት ከአንድ ግለሰብ ቤት ኮድ 3 ሠሌዳ ቁጥር ቁጥር አዲስ አበባ 55966 በሆነ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር ነው። በክልሉ እየተስፋፋ ያለውን ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያዎች ዝውውር ለመግታት የክልሉና የፌዴራል ጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው በመሥራት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ኡቲያንግ ኡቻን እንተናገሩት ክልሉ ድንበር ያለው ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያዎች ዝውውር መበራከቱን ተናግረዋል። ችግርን ለመካለካል በሚደረገው ጥረት ሕዝቡና ጸጥታ አካላት ለሚያደርጉት ጥረት አመስግነው፣ በቀጣይም ቁጥጥሩ ይጠናከራል ብለዋል።
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በዩጋንዳ አቻው ተሸነፈ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ከዩጋንዳ አቻው ጋር በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 ተሸንፏል። በመጀመሪያው አጋማሽ በተቆጠረበት አንድ ግብ ነው የኢትዮጵያ የወንዶች የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የተሸነፈው።
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ከዩጋንዳ አቻው ጋር በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 ተሸንፏል። በመጀመሪያው አጋማሽ በተቆጠረበት አንድ ግብ ነው የኢትዮጵያ የወንዶች የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የተሸነፈው።
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE ከጅግጅጋ እስከ ሀረሙከሌ መገንጠያ 104 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የግንባታ ስራ ጥቅምት 02/ 2012 ዓ.ም በይፋ ተጀመረ፡፡ የመንገዱ ግንባታ በብር 1,551,507,344.53 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ አምሳ አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ አርባ አራት) የሚፈጅ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነዉ። ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮረፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation (CCECC) ጨረታዉን አሸንፎ ወደ ስራ የገባዉ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራዉን የሚያከናዉን ኤስ.ጂ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ.የተ.የግ.ማ. (S G Consulting Engineers PLC) ነዉ፡፡
Via ERA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via ERA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#SRIYA
ቱርክ በሰሜን ሶሪያ እየፈፀመች በሚገኘው ጥቃት ምክንያት በመቶዎች የሚቆጠሩ ከአይ ኤስ አባላት ጋር ግንኙነት ያላቸው ሰዎች ከካምፕ ማምለጣቸውን የኩርድ አመራሮች ገለፁ፡፡ የአይ ኤስ አባላት የቅርብ ሰዎች የሆኑ እስረኞች ቱርክ ጥቃት እየፈፀመችበት በሚገኘው አከባቢ የሚገኘውን ኢን ኢሳ የስደተኞች መጠለያ መግቢያ ጥቃት እንደፈፀሙበት ተነግሯል፡፡ መረጃዎችን የሚከታተሉ ተቋማ 100 የሚሆኑ የአይ ኤስ አባላት የቅርብ ሰዎች ማምለጣቸውን የሚገልፁ ቢሆንም የኩርድ ሃላፊዎች ግን ከ800 በላይ የሚሆኑ የውጭ ዜግነት ያላቸውና ከአይ ኤስ አባላት የቅርብ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች አምልጠዋል ነው የሚሉት፡፡
Via BBC/FBC/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቱርክ በሰሜን ሶሪያ እየፈፀመች በሚገኘው ጥቃት ምክንያት በመቶዎች የሚቆጠሩ ከአይ ኤስ አባላት ጋር ግንኙነት ያላቸው ሰዎች ከካምፕ ማምለጣቸውን የኩርድ አመራሮች ገለፁ፡፡ የአይ ኤስ አባላት የቅርብ ሰዎች የሆኑ እስረኞች ቱርክ ጥቃት እየፈፀመችበት በሚገኘው አከባቢ የሚገኘውን ኢን ኢሳ የስደተኞች መጠለያ መግቢያ ጥቃት እንደፈፀሙበት ተነግሯል፡፡ መረጃዎችን የሚከታተሉ ተቋማ 100 የሚሆኑ የአይ ኤስ አባላት የቅርብ ሰዎች ማምለጣቸውን የሚገልፁ ቢሆንም የኩርድ ሃላፊዎች ግን ከ800 በላይ የሚሆኑ የውጭ ዜግነት ያላቸውና ከአይ ኤስ አባላት የቅርብ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች አምልጠዋል ነው የሚሉት፡፡
Via BBC/FBC/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba
ዛሬ በአዲስ አበባ ሊደረግ ታስቦ ከነበረ ሰልፍ ጋር በተያያዘ በትላንትናው ዕለት የታሰሩ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች መለቀቃቸው ለመስማት ተችሏል።
በተጨማሪ ደግሞ ቢቢሲ የሰራውን ዘገባ ይህንን በመጫን ማንበብ ትችላላችሁ👇
https://telegra.ph/ETH-10-13-3
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ በአዲስ አበባ ሊደረግ ታስቦ ከነበረ ሰልፍ ጋር በተያያዘ በትላንትናው ዕለት የታሰሩ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች መለቀቃቸው ለመስማት ተችሏል።
በተጨማሪ ደግሞ ቢቢሲ የሰራውን ዘገባ ይህንን በመጫን ማንበብ ትችላላችሁ👇
https://telegra.ph/ETH-10-13-3
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EGYPT #ETHIOPIA
የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታኅ አል-ሲሲ በታላቁ የኅዳሴ ግድብ ላይ የሚደረገውን ድርድር እንደገና ለማስጀመር ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በቅርቡ እንደሚገናኙ አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ በዛሬው ዕለት በአገራቸው ቴሌቭዥን ባደረጉት ንግግር ከጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ ጋር በሩሲያ እንደሚገናኙ አስታውቀዋል።
አል-ሲሲ ከጠቅላይ ምኒስትሩ ጋር የሚገናኙበትን ትክክለኛ ቀን ባይገልጹም ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ ጥቅምት 12 ቀን በሶቺ ከተማ የሚካሔደውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ በተባባሪ ሊቀ-መንበርነት ይመራሉ። ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን በታላቁ የኅዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አስተዳደር ላይ ያደረጓቸው ድርድሮች ያለ ውጤት ተበትነዋል።
ባለፈው መስከረም በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ የድርድሩ ፈቅ አለማለት ለቀጣናው መረጋጋት ሥጋት ሆኗል ያሉት ፕሬዝዳንት አል-ሲሲ ከፍትኃዊ እና ሚዛናዊ ስምምነት ለመድረስ ዓለም አቀፍ አሸማጋዮች ጣልቃ እንዲገቡ ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ በበኩሏ «የሶስተኛ ወገን ጣልቃ-ገብነት ኢትዮጵያ እና ሱዳን የማይቀበሉት እና ተገቢ ያልሆነ» በማለት ውድቅ አድርጋለች።
Via DW
PHOTO: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታኅ አል-ሲሲ በታላቁ የኅዳሴ ግድብ ላይ የሚደረገውን ድርድር እንደገና ለማስጀመር ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በቅርቡ እንደሚገናኙ አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ በዛሬው ዕለት በአገራቸው ቴሌቭዥን ባደረጉት ንግግር ከጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ ጋር በሩሲያ እንደሚገናኙ አስታውቀዋል።
አል-ሲሲ ከጠቅላይ ምኒስትሩ ጋር የሚገናኙበትን ትክክለኛ ቀን ባይገልጹም ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ ጥቅምት 12 ቀን በሶቺ ከተማ የሚካሔደውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ በተባባሪ ሊቀ-መንበርነት ይመራሉ። ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን በታላቁ የኅዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አስተዳደር ላይ ያደረጓቸው ድርድሮች ያለ ውጤት ተበትነዋል።
ባለፈው መስከረም በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ የድርድሩ ፈቅ አለማለት ለቀጣናው መረጋጋት ሥጋት ሆኗል ያሉት ፕሬዝዳንት አል-ሲሲ ከፍትኃዊ እና ሚዛናዊ ስምምነት ለመድረስ ዓለም አቀፍ አሸማጋዮች ጣልቃ እንዲገቡ ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ በበኩሏ «የሶስተኛ ወገን ጣልቃ-ገብነት ኢትዮጵያ እና ሱዳን የማይቀበሉት እና ተገቢ ያልሆነ» በማለት ውድቅ አድርጋለች።
Via DW
PHOTO: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#attention
የአፋር TIKVAH-ETH ቤተሰቦቻችን፦
በትናንትናው እለት የጁቡቲ ሠርጎ ገብ ታጣቂዎች በአፋር ክልል የአፋምቦ ወረዳ ነዋሪዎች በተኙበት ጨለማን ተገን በማድረግ ጥቃት አድርሰዋል። በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው በርካታ ህፃናት በዱቡቲ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል። ዛሬ ጥዋት የአፋር አርብቶ አደሮች መልሶ በማጥቃት በከፈቱት ተኩስ ከታጣቂዎቹ በርካታ የፈረንሳይ ጦር መሳሪያ መማረክ እንደቻሉ ስለሁኔታው የሚከታተሉ የአፋር አክቲቪስቶች ገልፀዋል። በጥቃቱ ከሞቱ ታጣቂዎች በርካታ የሠነድ ማስረጃዎችን ማግኘት እንደቻሉም ተነግሯል። በአፋር የሚገኙ TIKVAH-ETH ቤተሰቦቻችን አሁን የአፋርን ህዝብ እየገደለ እና እያጠቃ የሚገኘው ከጎረቤት አገራት የሚገቡ ሠርጎ ገቦች ናቸው፤ አሁንም ድምፃችን ይሰማ ብለዋል።
TIKVAH ETH FAMILY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአፋር TIKVAH-ETH ቤተሰቦቻችን፦
በትናንትናው እለት የጁቡቲ ሠርጎ ገብ ታጣቂዎች በአፋር ክልል የአፋምቦ ወረዳ ነዋሪዎች በተኙበት ጨለማን ተገን በማድረግ ጥቃት አድርሰዋል። በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው በርካታ ህፃናት በዱቡቲ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል። ዛሬ ጥዋት የአፋር አርብቶ አደሮች መልሶ በማጥቃት በከፈቱት ተኩስ ከታጣቂዎቹ በርካታ የፈረንሳይ ጦር መሳሪያ መማረክ እንደቻሉ ስለሁኔታው የሚከታተሉ የአፋር አክቲቪስቶች ገልፀዋል። በጥቃቱ ከሞቱ ታጣቂዎች በርካታ የሠነድ ማስረጃዎችን ማግኘት እንደቻሉም ተነግሯል። በአፋር የሚገኙ TIKVAH-ETH ቤተሰቦቻችን አሁን የአፋርን ህዝብ እየገደለ እና እያጠቃ የሚገኘው ከጎረቤት አገራት የሚገቡ ሠርጎ ገቦች ናቸው፤ አሁንም ድምፃችን ይሰማ ብለዋል።
TIKVAH ETH FAMILY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ቱኒዚያኖች አዲስ ፕሬዝዳንት ለመምረጥ ድምፅ እየሰጡ ነው ፤በመጨረሻው ዙር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ወደ ፖለቲካው አዲስ የገቡ ተፎካካሪዎች ናቸውም ተብሏል፡፡ የንግድ ሰው የሆኑት ካቢል ካሩይ እና በጡረታ የተገለሉት የቀለም ሰው ካኢስ ሰይድ ለፕሬዝዳንትነት እየተወዳደሩ መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል፡፡
Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#WolaitaSodo
ግጭቶችንና አለመግባባቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የድርሻቸውን እንደሚያበረክቱ በወላይታ ዞን የሶዶ ከተማ ነዋሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ በከተማው በሁለት ወጣቶች መካከል በግል ጸብ መነሻነት የተከሰተው አለመግባባት እንዳይስፋፋ በእርቅ መፈታቱን የዞኑ ወጣቶች ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡
በእርቅ ስነ-ስርዓቱ ላይ የሀገር ሽማግሌዎች በሰጡት አስተያየት ስሜታዊነት ግለሰብን ብቻ ሳይሆን ቤተሰብን፣ አከባቢንና ሀገርን ለጉዳት እንደሚዳርግ ገልጸዋል፡፡ ነገሮችን በሰከነ መንፈስና በመቻቻል ማየት ፍርሀት ሳይሆን አርቆ አስተዋይነት መሆኑን አመላክተው አለመግባባትን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ባህል እንዲሰርጽ ተግተን መስራት አለብን ብለዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-10-13-4
📹16 MB
Via Wolaita Zone Youth League
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ግጭቶችንና አለመግባባቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የድርሻቸውን እንደሚያበረክቱ በወላይታ ዞን የሶዶ ከተማ ነዋሪ ወጣቶች ገለጹ፡፡ በከተማው በሁለት ወጣቶች መካከል በግል ጸብ መነሻነት የተከሰተው አለመግባባት እንዳይስፋፋ በእርቅ መፈታቱን የዞኑ ወጣቶች ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡
በእርቅ ስነ-ስርዓቱ ላይ የሀገር ሽማግሌዎች በሰጡት አስተያየት ስሜታዊነት ግለሰብን ብቻ ሳይሆን ቤተሰብን፣ አከባቢንና ሀገርን ለጉዳት እንደሚዳርግ ገልጸዋል፡፡ ነገሮችን በሰከነ መንፈስና በመቻቻል ማየት ፍርሀት ሳይሆን አርቆ አስተዋይነት መሆኑን አመላክተው አለመግባባትን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ባህል እንዲሰርጽ ተግተን መስራት አለብን ብለዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-10-13-4
📹16 MB
Via Wolaita Zone Youth League
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#JIGJIGA
”ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተበረከተው ሽልማት #ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰጠ ትልቅ ክብር ነው” ሲሉ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ ዑመር ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ሽልማት በማግኘታቸው ”የእንኳን ደስ አልዎ!” ሰልፍ በጅግጅጋ ስታዲዬም ዛሬ ተካሂዷል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት “ሰዎች 50 ዓመታት ስልጣን ላይ ቆይተው የማያገኙትን ዓለም አቀፍ ሽልማት ክብር ጠቅላይ ሚኒስትራችን በማግኘታቸው እጅግ ተደስቻለሁ” ብለዋል።
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
”ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተበረከተው ሽልማት #ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰጠ ትልቅ ክብር ነው” ሲሉ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ ዑመር ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ሽልማት በማግኘታቸው ”የእንኳን ደስ አልዎ!” ሰልፍ በጅግጅጋ ስታዲዬም ዛሬ ተካሂዷል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት “ሰዎች 50 ዓመታት ስልጣን ላይ ቆይተው የማያገኙትን ዓለም አቀፍ ሽልማት ክብር ጠቅላይ ሚኒስትራችን በማግኘታቸው እጅግ ተደስቻለሁ” ብለዋል።
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UnityPark
መደበኛ የክፍያ ጉብኝት ከነገ ሰኞ ይጀምራል!
ከነገ ሰኞ ማለትም ከጥቅምት 3 2012 ጅምሮ ማንኛውም ዜጋ 200 ብር እንዲሁም በቪአይፒ (VIP) 1 ሺህ ብር በመክፈል ቤተ መንግስቱን መጎብኘት ይችላል።
የአንድነት ፓርክን ለመጎብኘት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መገኘት ሲኖርበት በተጨማሪም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅድመሁኔታዎች ካላሟሉ ፓርኩን መጎብኘት አይችሉም።
ጎብኚዎች ይዘው መምጣት የሌለባቸው ነገሮች፦
- ስለት
- ተቀጣጣይ ቁሶች
- የጦር መሳሪያዎች
- ምግብ መጠጦች እና ጣፋጭ ነገሮች
- ማስቲካ
- የመዋቢያ ቁሶች
- የግል ካሜራዎች
- ስልኮች ታብሌቶች እና ማንቸውንም የምስልና ድምጽ መቅረጫ መሳሪያዎችን
- ሲጋራ እና አደንዛዥ ዕጾች
በፓርኩ ውስጥ ማድረግ የተከለከሉ ተግባራትና ባህሪያት፦
- መጮህና መረበሽ
- ከአስጎብኚ ውጪና ከተመደቡበት የጉብኝት ቡድን ውጪ መንቀሳቀስ
- በታሪካዊ ህንጻዎቹ ላይ መደገፍ
- ቅርሶችንና እንስሳትን መነካካት
- እንስሳትን ከተፈቀደው ቦታ ውጪ መቅረብ
- እንስሳትን መመገብ
- እንስሳትን ማስቆጣት (ጠጠር መወርወር፣ በአካላዊ እንቅስቃሴ ማስፈራራት፣ አላስፈላጊ ድምጽ ማውጣት)
- ከተቀመጡ የቆሻሻ ማስወገጃ እቃ ውጪ ቆሻሻ መጣል
- ሲጋራና ሌሎች አደንዛዥ እጾችን መጠቀም
- የቤት እንስሳትን ይዞ መምጣት
- መንገድ ከተበጀለት ዉጪ መራመድ እና አጥሮችን ከልክ በላይ መጠጋትም ሆነ መደገፍ
- ማንኛዉንም በፓርኩ የሚገኝ የኤሌትሮኒክስ ቁስ ያለፍቃድ መንካት
#አንድነት_ፓርክ
#UnityPark
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መደበኛ የክፍያ ጉብኝት ከነገ ሰኞ ይጀምራል!
ከነገ ሰኞ ማለትም ከጥቅምት 3 2012 ጅምሮ ማንኛውም ዜጋ 200 ብር እንዲሁም በቪአይፒ (VIP) 1 ሺህ ብር በመክፈል ቤተ መንግስቱን መጎብኘት ይችላል።
የአንድነት ፓርክን ለመጎብኘት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ይዞ መገኘት ሲኖርበት በተጨማሪም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅድመሁኔታዎች ካላሟሉ ፓርኩን መጎብኘት አይችሉም።
ጎብኚዎች ይዘው መምጣት የሌለባቸው ነገሮች፦
- ስለት
- ተቀጣጣይ ቁሶች
- የጦር መሳሪያዎች
- ምግብ መጠጦች እና ጣፋጭ ነገሮች
- ማስቲካ
- የመዋቢያ ቁሶች
- የግል ካሜራዎች
- ስልኮች ታብሌቶች እና ማንቸውንም የምስልና ድምጽ መቅረጫ መሳሪያዎችን
- ሲጋራ እና አደንዛዥ ዕጾች
በፓርኩ ውስጥ ማድረግ የተከለከሉ ተግባራትና ባህሪያት፦
- መጮህና መረበሽ
- ከአስጎብኚ ውጪና ከተመደቡበት የጉብኝት ቡድን ውጪ መንቀሳቀስ
- በታሪካዊ ህንጻዎቹ ላይ መደገፍ
- ቅርሶችንና እንስሳትን መነካካት
- እንስሳትን ከተፈቀደው ቦታ ውጪ መቅረብ
- እንስሳትን መመገብ
- እንስሳትን ማስቆጣት (ጠጠር መወርወር፣ በአካላዊ እንቅስቃሴ ማስፈራራት፣ አላስፈላጊ ድምጽ ማውጣት)
- ከተቀመጡ የቆሻሻ ማስወገጃ እቃ ውጪ ቆሻሻ መጣል
- ሲጋራና ሌሎች አደንዛዥ እጾችን መጠቀም
- የቤት እንስሳትን ይዞ መምጣት
- መንገድ ከተበጀለት ዉጪ መራመድ እና አጥሮችን ከልክ በላይ መጠጋትም ሆነ መደገፍ
- ማንኛዉንም በፓርኩ የሚገኝ የኤሌትሮኒክስ ቁስ ያለፍቃድ መንካት
#አንድነት_ፓርክ
#UnityPark
@tsegabwolde @tikvahethiopia