TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
"ወንጀል ውርስ አይደለም በጋብቻ መተሳሰራቸው ብቻ እንዴት በሽብር ያስጠይቃቸዋል?" የወ/ሮ ደስታ (የብ/ጀ አሳምነው ጽጌ ባለቤት) ጠበቃ ዛሬ የተናገሩት!
.
.
"ፃፈ የተባለው #opinion ነው እሱ ደግሞ ወንጀል ሊሆን አይችልም የኤልያስን አስተሳሰብ ፖሊስ ጠላው ማለት ወንጀል ነው ማለት አይደለም" የኤልያስ ገብሩ ጠበቃ!
.
.
ዛሬ በችሎት በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩት እነ ኤልያስ ገብሩ የቀረቡ ሲሆን ፖሊስ የሰራቸውን የምርመራ ስራዎች ለዳኛው ገልፆ ለቀሪ ምርመራዎች ተጨማሪ 28 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል። ወ/ሮ ደስታን በተመለከተ በባንክ ገንዘብ ማግኘቱን፣ በእናታቸው ስም የተገዛ መኪና መገኘቱን፣ የጦር መሳርያ በቤታቸው መገኘቱን ገልፅዋል። ወንጀል ውርስ አይደለም ያሉት ጠበቃቸው ተጠርጣሪዋ 18 አመት ውጪ ሰርተው ነው የመጡት ንብረት ማፍራት እንዴት ሽብርን ያቋቁማል የጦር መሳርያውም ባለቤታቸው የመንግስት ባለስልጣን በመሆናቸው ቤታቸው የተቀመጠ ነው ብለዋል።

Via Samrawit
@tsegabwolde @tikvahethiopia