#CPJ
በግብጽ በቅርቡ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ 6 ጋዜጠኞች ለእስር መዳረጋቸውን ሲፒጄ አስታውቋል፡፡ ጋዜጠኞች የታሰሩት በግብጽ የተለያዩ ከተሞች የአብዱል ፋታህ አል ሲሲን መንግሥት በመቃወም በርካታ ግብጻውያን አደባባይ መውጣታቸውን የሚያሳይ ዘገባ አሰራጭተዋል በሚል ነው፡፡
ሲፒጂ የግብጽ ባለስልጣናት ጋዜጠኛ አላ አብዱልፈታህ ፣ናሰር አብደልሃፌዝ ፣ኢንጊ አብደልወሃብ እና ሌሎች ሶስት ጋዜጠኞች በአስቸኳይ ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡ ግብጽ መገናኛ ብዙሃንን እና ጋዜጠኞችን ከማፈን እና ከማሰር ልትቆጠብ ይገባል ሲልም አሳስቧል ሲፒጄ፡፡ መሐመድ አሊ የተባለ ግለሰብ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ለሚስታቸው እና ለጄኔራሎቻቸው እጅግ ቅንጡ ቪላ ቤቶችን መግዛታቸውን የሚሳይ ቪዲዮ ማሰራጨቱን ተከትሎ ሥልጣናቸውን እንዲለቁ ግብፃውያን እየጠየቁ ነው፡፡
Via አልጀዚራ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በግብጽ በቅርቡ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ 6 ጋዜጠኞች ለእስር መዳረጋቸውን ሲፒጄ አስታውቋል፡፡ ጋዜጠኞች የታሰሩት በግብጽ የተለያዩ ከተሞች የአብዱል ፋታህ አል ሲሲን መንግሥት በመቃወም በርካታ ግብጻውያን አደባባይ መውጣታቸውን የሚያሳይ ዘገባ አሰራጭተዋል በሚል ነው፡፡
ሲፒጂ የግብጽ ባለስልጣናት ጋዜጠኛ አላ አብዱልፈታህ ፣ናሰር አብደልሃፌዝ ፣ኢንጊ አብደልወሃብ እና ሌሎች ሶስት ጋዜጠኞች በአስቸኳይ ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡ ግብጽ መገናኛ ብዙሃንን እና ጋዜጠኞችን ከማፈን እና ከማሰር ልትቆጠብ ይገባል ሲልም አሳስቧል ሲፒጄ፡፡ መሐመድ አሊ የተባለ ግለሰብ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ለሚስታቸው እና ለጄኔራሎቻቸው እጅግ ቅንጡ ቪላ ቤቶችን መግዛታቸውን የሚሳይ ቪዲዮ ማሰራጨቱን ተከትሎ ሥልጣናቸውን እንዲለቁ ግብፃውያን እየጠየቁ ነው፡፡
Via አልጀዚራ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢፌዴሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከዲፕሎማሲ ማህበረሰብ አባላትና ከልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ዙሪያ እየመከረ ነው። በምክክር መድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ፣የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማሪያም እና የተለያዩ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ታድመዋል። ከዚህ ባለፈም የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የልማት አጋር ድርጅቶች ተወካዮች በምክክር መድረኩ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የወልድያ-ቆቦ መንገድ በደለል ምክንያት መዘጋቱ ተገለፀ!
ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ አልቻሉም።
መንገዱ የተዘጋው ከተራራማ ቦታዎች የሚወርድ ደለልን መከላከል የሚያስችል ደጋፊ የግንብ አጥር ባለመኖሩ ነው። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮምቦልቻ መንገድ ዝርጋታ ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ተስፋዬ ‹‹ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች የመንገድ ጠረጋ እየተከናወነ ነው፤ በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት ደግሞ ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንብ ይሠራል›› ብለዋል፡፡
የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንቡ ከደሴ ዋጃ ያለውን መንገድም ተመሳሳይ ችግር እንዳይገጥመው ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ቆቦ መንገድ ከአዲስ አበባ በደሴ-ወልድያ-ቆቦ-መቀሌ የሚገባ ነው፡፡ መንገዱ ክልል ከክልል የሚያገናኝና በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሚተዳደር ነው፡፡
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ አልቻሉም።
መንገዱ የተዘጋው ከተራራማ ቦታዎች የሚወርድ ደለልን መከላከል የሚያስችል ደጋፊ የግንብ አጥር ባለመኖሩ ነው። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮምቦልቻ መንገድ ዝርጋታ ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ተስፋዬ ‹‹ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች የመንገድ ጠረጋ እየተከናወነ ነው፤ በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት ደግሞ ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንብ ይሠራል›› ብለዋል፡፡
የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንቡ ከደሴ ዋጃ ያለውን መንገድም ተመሳሳይ ችግር እንዳይገጥመው ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ቆቦ መንገድ ከአዲስ አበባ በደሴ-ወልድያ-ቆቦ-መቀሌ የሚገባ ነው፡፡ መንገዱ ክልል ከክልል የሚያገናኝና በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሚተዳደር ነው፡፡
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ERA
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አዲስ አበባን ከክልል ከተሞች ጋር የሚያገናኙ አራት ፈጣን መንገዶችን ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገለፀ። ፈጣን መንገዶቹ አዲስ አበባን መዳረሻ በማድረግ ደብረ ማርቆስ፣ ጅማ፣ ነቀምት እና ኮምቦልቻ የሚገነቡ ሲሆን አዲስ አበባ አዳማ ፈጣን መንገድን ጨምሮ በከተማዋ እና በፈጣን መንገዶች መገናኛ ቦታዎች ላይ የማሻሻያ ሥራዎችን የሚጨምር ነው።
Via Addis Maleda
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አዲስ አበባን ከክልል ከተሞች ጋር የሚያገናኙ አራት ፈጣን መንገዶችን ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገለፀ። ፈጣን መንገዶቹ አዲስ አበባን መዳረሻ በማድረግ ደብረ ማርቆስ፣ ጅማ፣ ነቀምት እና ኮምቦልቻ የሚገነቡ ሲሆን አዲስ አበባ አዳማ ፈጣን መንገድን ጨምሮ በከተማዋ እና በፈጣን መንገዶች መገናኛ ቦታዎች ላይ የማሻሻያ ሥራዎችን የሚጨምር ነው።
Via Addis Maleda
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba
የአዲስ አበባ አስተዳደር በከባድ ጭነት ተሸከርካሪዎች በከተማዋ እንዳይንቀሳቀሱ ጥሎት የነበረውን ማሻሻሉን ካፒታል አስነብቧል፡፡ ማንኛውም የጭነት መጠን ያለው የጭነት ተሸከርካሪዎች ቅዳሜ ቅዳሜ በቀን ብቻ እንዲንቀሳቀሱ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ የትራፊክ ፍሰትን ለመቀነስ ሲባል አስተዳደሩ እገዳውን የጣለው በሐምሌ ነበር፡፡
ምንጭ፦ ካፒታል ጋዜጣ/ዋዜማ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ አስተዳደር በከባድ ጭነት ተሸከርካሪዎች በከተማዋ እንዳይንቀሳቀሱ ጥሎት የነበረውን ማሻሻሉን ካፒታል አስነብቧል፡፡ ማንኛውም የጭነት መጠን ያለው የጭነት ተሸከርካሪዎች ቅዳሜ ቅዳሜ በቀን ብቻ እንዲንቀሳቀሱ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ የትራፊክ ፍሰትን ለመቀነስ ሲባል አስተዳደሩ እገዳውን የጣለው በሐምሌ ነበር፡፡
ምንጭ፦ ካፒታል ጋዜጣ/ዋዜማ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢሬቻን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለፀ!
የኢሬቻ በዓልን ከገዳ ስርዓት ማሳያነት ባለፈ ራሱን ችሎ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባሕል ድርጅት ለማስመዝገብ ዝግጅት መጠናቀቁን የኦሮሚያ ክልል ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡
ዩኒስኮ በአሉን ለማስመዝገብ የሚያስቀምጣቸውን መስፈርቶች ለሟሟላት የሚያስችሉ ጥናቶች እየተደረጉ መሆኑም ተነግሯል፡፡ በተለይም ባሕሉን በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የማስተዋወቅ ስራ ትልቁ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ነው ተብሏል፡፡
በ2009 ዓ.ም በበዓሉ አከባበር ወቅት የተፈጠረው ግርግርና የሰዎች ሞት በዓሉን በማስተዋወቅ ጥረት ላይ መጥፎ አሻራ አሳርፎ ስለማለፉ ተጠቁሟል፡፡ በዚህ ዓመት በአዲስ አበባ በሚደረገው የበአሉ አከባበር ላይ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ታዳሚ እንደሚጠበቅ የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ለአሐዱ ቴሌቪዥን ገልጿል፡፡
ምንጭ፦ አሃዱ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢሬቻ በዓልን ከገዳ ስርዓት ማሳያነት ባለፈ ራሱን ችሎ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባሕል ድርጅት ለማስመዝገብ ዝግጅት መጠናቀቁን የኦሮሚያ ክልል ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡
ዩኒስኮ በአሉን ለማስመዝገብ የሚያስቀምጣቸውን መስፈርቶች ለሟሟላት የሚያስችሉ ጥናቶች እየተደረጉ መሆኑም ተነግሯል፡፡ በተለይም ባሕሉን በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የማስተዋወቅ ስራ ትልቁ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ነው ተብሏል፡፡
በ2009 ዓ.ም በበዓሉ አከባበር ወቅት የተፈጠረው ግርግርና የሰዎች ሞት በዓሉን በማስተዋወቅ ጥረት ላይ መጥፎ አሻራ አሳርፎ ስለማለፉ ተጠቁሟል፡፡ በዚህ ዓመት በአዲስ አበባ በሚደረገው የበአሉ አከባበር ላይ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ታዳሚ እንደሚጠበቅ የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ለአሐዱ ቴሌቪዥን ገልጿል፡፡
ምንጭ፦ አሃዱ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert
በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ። በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢህአዴግና የኦዲፒ ሊቀ መንበር እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ የኦዲፒ ምክትል ሊቀ መንበርና የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ፣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀ መንበር አቶ ሌንጮ ለታን ጨምሮ በርካታ በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተሳትፈዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-10-01-3
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ። በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢህአዴግና የኦዲፒ ሊቀ መንበር እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ የኦዲፒ ምክትል ሊቀ መንበርና የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ፣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀ መንበር አቶ ሌንጮ ለታን ጨምሮ በርካታ በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተሳትፈዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-10-01-3
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሲዳማ ዞን ተከስቶ በነበረው ግጭት ሳቢያ በአለታ ወንዶ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማቋቋም የተከናወኑ ስራዎች ተጎበኙ!
ባለፈው በጀት ዓመት በደቡብ ክልሉ በነበረው ግጭት ሳቢያ በሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ከተማ ጉዳት የደረሰባቸው አካላትን መልሶ ለማቋቋም የተሰራውን ስራ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው ጎብኝተዋል፡፡
ከተማዋን ወደ ቀድሞ ሰላሟ መመለስ ቢቻልም ተጎጂዎችን መልሶ የማቋቋም ሂደት በተፈለገው መልክ አልተሰራም ብለዋል፡፡ ተጎጅዎችን ለማቋቋም ከተዋቀረው ኮሚቴ ጋርም መክረዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-10-01-4
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባለፈው በጀት ዓመት በደቡብ ክልሉ በነበረው ግጭት ሳቢያ በሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ከተማ ጉዳት የደረሰባቸው አካላትን መልሶ ለማቋቋም የተሰራውን ስራ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው ጎብኝተዋል፡፡
ከተማዋን ወደ ቀድሞ ሰላሟ መመለስ ቢቻልም ተጎጂዎችን መልሶ የማቋቋም ሂደት በተፈለገው መልክ አልተሰራም ብለዋል፡፡ ተጎጅዎችን ለማቋቋም ከተዋቀረው ኮሚቴ ጋርም መክረዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-10-01-4
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በዛሬው ዕለት የፖሊስ ኃይል በከፈተው ተኩስ አንድ ሰው መገደሉ ተሰምቷል!
ቻይና ዛሬ በኮሙኒስት ፓርቲ ሥር ያለውን ሥርዓትዋን 70ኛ ዓመት ሰፊ ወታደራዊ ትዕይንት አድርጋ ኃይሏን በማሳየት አክብራ ውላለች። በሆንግ ኮንግ ግን በዲሞክራሲ ደጋፊ ሰልፈኞችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት ተነስቷል።
ቻይና የራስ ገዝ አስተዳደር ከተማ ላይ ቁጥጥር ለማጥበቅ የምታደርገውን ጥረት ሆንግ ኮንግ ያሉት ተቃዋሚዎች እየተገዳደሩ ነው። ሆንግ ኮንግ ከተማ ውስጥ ጃንጥላ የያዙ የተቃውሞ ሰልፈኞች ቤት የተሰሩ የቤንዚን ቦምቦች በፖሊሶች ላይ ወርውረዋል። በከተማይቱ ዋና ዋና አካባቢዎች እሳት አጋይተዋል። ፖሊሶቹ በበኩላቸው ዕምባ አስመጪ ጋዝ ተኩሰውባቸዋል፤ የውሀ ግፊትም ተጠቅመዋል። አንድ ሰው ፖሊስ በከፈተው ተኩስ መገደሉ ተዘግቧል።
ምንጭ፦ ቪኦኤ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቻይና ዛሬ በኮሙኒስት ፓርቲ ሥር ያለውን ሥርዓትዋን 70ኛ ዓመት ሰፊ ወታደራዊ ትዕይንት አድርጋ ኃይሏን በማሳየት አክብራ ውላለች። በሆንግ ኮንግ ግን በዲሞክራሲ ደጋፊ ሰልፈኞችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት ተነስቷል።
ቻይና የራስ ገዝ አስተዳደር ከተማ ላይ ቁጥጥር ለማጥበቅ የምታደርገውን ጥረት ሆንግ ኮንግ ያሉት ተቃዋሚዎች እየተገዳደሩ ነው። ሆንግ ኮንግ ከተማ ውስጥ ጃንጥላ የያዙ የተቃውሞ ሰልፈኞች ቤት የተሰሩ የቤንዚን ቦምቦች በፖሊሶች ላይ ወርውረዋል። በከተማይቱ ዋና ዋና አካባቢዎች እሳት አጋይተዋል። ፖሊሶቹ በበኩላቸው ዕምባ አስመጪ ጋዝ ተኩሰውባቸዋል፤ የውሀ ግፊትም ተጠቅመዋል። አንድ ሰው ፖሊስ በከፈተው ተኩስ መገደሉ ተዘግቧል።
ምንጭ፦ ቪኦኤ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba
በዛሬው ዕለት ቀን 9:20 ላይ ኤግዚቢሽን ማእከል ጀርባ በደረሰ የእሳት አደጋ የ78 ሰዎች መኖርያ የሆኑ 14 ቤቶች መውደሙ ተሰምቷል። ግምቱ 7 ሚልየን ብር የሆነ ንብረትም ተቃጥሏል። ተጎጂዎች ጊዜያዊ መጠለያ ውስጥ እንደሚገኙም ታውቋል።
•አመሻሹን ደግሞ አ/አ አንዋር መስጅድ ዙርያ እሳት ተነስቶ የነበረ ሲሆን አሁን በቁጥጥር ስር መዋሉ ለማወቅ ተችሏል።
Via Abdurahim Ahmed & Tesfaye Getent
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት ቀን 9:20 ላይ ኤግዚቢሽን ማእከል ጀርባ በደረሰ የእሳት አደጋ የ78 ሰዎች መኖርያ የሆኑ 14 ቤቶች መውደሙ ተሰምቷል። ግምቱ 7 ሚልየን ብር የሆነ ንብረትም ተቃጥሏል። ተጎጂዎች ጊዜያዊ መጠለያ ውስጥ እንደሚገኙም ታውቋል።
•አመሻሹን ደግሞ አ/አ አንዋር መስጅድ ዙርያ እሳት ተነስቶ የነበረ ሲሆን አሁን በቁጥጥር ስር መዋሉ ለማወቅ ተችሏል።
Via Abdurahim Ahmed & Tesfaye Getent
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የእገዳ ውሳኔ አልተላለፈም...
የኢትዮጵያ የማራቶን ውድድር ሯጮች ላይ ምንም አይነት የእገዳ ውሳኔ እንዳልተላለፈ ከአትሌቶቹ ጋር ካታር የሚገኙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክትር ዱቤ ጂሎ ለቢቢሲ ተናገሩ።
በካታር ዶሃ እየተካሄደ ባለው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ በማራቶን ውድድር ላይ የተሳተፉት አትሌቶች ለቀጣዮቹ ሦስት ወራት እረፍት አድርገው እንዲያገግሙ እንጂ እገዳ አለመሆኑን ገልጸዋል።
ውሳኔው ከ42 ኪሎሜትሮች በላይ በሚሮጥበት ከባድ በሚባለው የማራቶን ውድድር ላይ የሚሳተፉ ሯጮችን ጤንነትና ደህንነት ለመጠበቅ የሚወሰድ ተቀባይነት ያለው እረፍት ነው ብለዋል ዱቤ ጅሎ።
አትሌቶች የሦስት ወራት #የማገገሚያ ጊዜ እንዲያገኙ ማድረግ በዓለም አቀፍ የውድድር ሕግና ደንብ ውስጥ ተቀባይነት ያለውና በሌሎችም ሃገራት የሚሰራበት እንደሆነ አመልክተዋል።
Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የማራቶን ውድድር ሯጮች ላይ ምንም አይነት የእገዳ ውሳኔ እንዳልተላለፈ ከአትሌቶቹ ጋር ካታር የሚገኙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክትር ዱቤ ጂሎ ለቢቢሲ ተናገሩ።
በካታር ዶሃ እየተካሄደ ባለው 17ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ በማራቶን ውድድር ላይ የተሳተፉት አትሌቶች ለቀጣዮቹ ሦስት ወራት እረፍት አድርገው እንዲያገግሙ እንጂ እገዳ አለመሆኑን ገልጸዋል።
ውሳኔው ከ42 ኪሎሜትሮች በላይ በሚሮጥበት ከባድ በሚባለው የማራቶን ውድድር ላይ የሚሳተፉ ሯጮችን ጤንነትና ደህንነት ለመጠበቅ የሚወሰድ ተቀባይነት ያለው እረፍት ነው ብለዋል ዱቤ ጅሎ።
አትሌቶች የሦስት ወራት #የማገገሚያ ጊዜ እንዲያገኙ ማድረግ በዓለም አቀፍ የውድድር ሕግና ደንብ ውስጥ ተቀባይነት ያለውና በሌሎችም ሃገራት የሚሰራበት እንደሆነ አመልክተዋል።
Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጭልጋ
"ችግሩ የተፈጠረው ቅማንት ኮሚቴውን መያዝ መቻል አለብን፤ ወንጀለኛ ነው ብሎ ነው እያሰማራ ያለው ይሄን ፋኖ፤ ወደ 8 -9 ሰው ሞቶብናል፤ 7-8 ሰው ቁስለኛ አለ።...ፋኖ የሚባለው እራሱን የቻለ ልብስ ነው ያለው። ፋኖ ነው የሚለው..." የቅማንት ማህበረሰብ አባል
.
.
"ፋኖ የሚባል ጦር የለም! እውነታው ይሄ ነው" የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ
.
.
"በክልሉ ውስጥ በህዝቦች መካከል ግጭት እንዲነሳ ለማድረግ አጀንዳ ይዞ የሚሰራ ኃይል አለ። ይሄ ኃይል አሁን ፅንፈኛ የቅማንት ኮሚቴ አባላት ክልሉን ማተራመስ እንዲችሉ ማስታጠቅ ነው አንደኛው፤ ባለፉት አመታት እኔም ወደዚህ ቢሮ ከመምጣቴ በፊት ጄነራል አሳምነው በነበረ ጊዜም ከዚያም በፊት ሌሎች ቢሮ ኃላፊዎች በነበሩ ጊዜ ግጭት ነበር። ስለዚህ እዚህ ቢሮ ያለ ሰው በሙሉ ለቅማንት ፅንፈኛ ኮሚቴ ጠላት ነው። ጄነራል አሳምነው ነበር ጠላት ነው፤ ከዚያ በፊት አቶ ደሴ አሰሜ ነበር ጠላት ነው፤ ከዚያ በፊት አቶ እዘዝ ዋሴ ነበር ጠላት ነው፤ አሁን ደግሞ እኔ መጣሁ ጠላት ነኝ፤ ስለዚህ አጀንዳ መቅርፅ ነው። እዚህ ቢሮ ላይ የምንመደብ ሰዎች ህግና ስርዓት ለማስከበር በምናደርገው እንቅስቃሴ ስም ማጥፋት ነው፤ ስም ማብጠልጠል ነው።" የአማራ ክልል ሰላምና ግንባታ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘው ተሻገር
Via #VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ችግሩ የተፈጠረው ቅማንት ኮሚቴውን መያዝ መቻል አለብን፤ ወንጀለኛ ነው ብሎ ነው እያሰማራ ያለው ይሄን ፋኖ፤ ወደ 8 -9 ሰው ሞቶብናል፤ 7-8 ሰው ቁስለኛ አለ።...ፋኖ የሚባለው እራሱን የቻለ ልብስ ነው ያለው። ፋኖ ነው የሚለው..." የቅማንት ማህበረሰብ አባል
.
.
"ፋኖ የሚባል ጦር የለም! እውነታው ይሄ ነው" የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ
.
.
"በክልሉ ውስጥ በህዝቦች መካከል ግጭት እንዲነሳ ለማድረግ አጀንዳ ይዞ የሚሰራ ኃይል አለ። ይሄ ኃይል አሁን ፅንፈኛ የቅማንት ኮሚቴ አባላት ክልሉን ማተራመስ እንዲችሉ ማስታጠቅ ነው አንደኛው፤ ባለፉት አመታት እኔም ወደዚህ ቢሮ ከመምጣቴ በፊት ጄነራል አሳምነው በነበረ ጊዜም ከዚያም በፊት ሌሎች ቢሮ ኃላፊዎች በነበሩ ጊዜ ግጭት ነበር። ስለዚህ እዚህ ቢሮ ያለ ሰው በሙሉ ለቅማንት ፅንፈኛ ኮሚቴ ጠላት ነው። ጄነራል አሳምነው ነበር ጠላት ነው፤ ከዚያ በፊት አቶ ደሴ አሰሜ ነበር ጠላት ነው፤ ከዚያ በፊት አቶ እዘዝ ዋሴ ነበር ጠላት ነው፤ አሁን ደግሞ እኔ መጣሁ ጠላት ነኝ፤ ስለዚህ አጀንዳ መቅርፅ ነው። እዚህ ቢሮ ላይ የምንመደብ ሰዎች ህግና ስርዓት ለማስከበር በምናደርገው እንቅስቃሴ ስም ማጥፋት ነው፤ ስም ማብጠልጠል ነው።" የአማራ ክልል ሰላምና ግንባታ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ አቶ አገኘው ተሻገር
Via #VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዙር 5ኛ አመት የሥራ ዘመን የፊታችን ሰኞ መስከረም 26 በይፋ ይከፈታል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakePage ይህ ከ260,000 በላይ ተከታይ ያለውና በገጣሚ ሜሮን ጌትነት ስም ታየተከፈተ የፌስቡክ ገፅ ሀሰተኛ ነው። እጅግ በሚገርም ሁኔታ በገፁ የሚሰራጩት መልእክቶችን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ላይክ እና ሼር ያደርጉታል። ፖስት የሚደረጉት ፎቶዎችም ከኢንስታግራም ገጿን የሚወሰዱ ናቸው።
Meron Getnet❌
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Meron Getnet❌
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሜሮን ትክክለኛ የፌስቡክ አካውንቷ⬆️
ከወራት በፊት ታዋቂዋ ገጣሚ እና ተዋናይት ሜሮን ጌትነት በትክክለኛው የኢንስታግራም ገጿ እሷ የምትጠቀምበት የፌስቡክ አካውንቷ Meron Ghetnet የሚል ላይክ ፔጅ ያልሆነ እንደሆነ ገልፃ ነበር። ለመጨረሻ ጊዜ #ሼር ያደረገችው September 24 2019 ነው።
Meron Ghetnet ላይክ ፔጅ አይደለም!
•Meron Getnet❌
•Meron Ghetnet✅
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወራት በፊት ታዋቂዋ ገጣሚ እና ተዋናይት ሜሮን ጌትነት በትክክለኛው የኢንስታግራም ገጿ እሷ የምትጠቀምበት የፌስቡክ አካውንቷ Meron Ghetnet የሚል ላይክ ፔጅ ያልሆነ እንደሆነ ገልፃ ነበር። ለመጨረሻ ጊዜ #ሼር ያደረገችው September 24 2019 ነው።
Meron Ghetnet ላይክ ፔጅ አይደለም!
•Meron Getnet❌
•Meron Ghetnet✅
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አቅም በተሻለ አግባብ ለማሳደግ መንግስት በዓለም አቀፍ የአጋርነት ትስስር ፈጠራ ዙሪያ በትኩረት እንደሚሰራ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አስታወቁ።
"በሳይንስ እና በከፍተኛ ትምህርት" ዙሪያ ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ለሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅት ተዎካዮች፥ አጋር የልማት ድርጅቶች እና የውጭ ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ "የአጋርነት እና የትስስር" መፍጠሪያ መድረክ በሸራተን አዲስ ሆቴል ተካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ፥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አቅም በተሻለ አግባብ ለማሳደግ መንግሥት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህ ረገድ መንግስት ዓለም አቀፍ የአጋርነት ትስስር ፈጠራ ዙሪያ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አቅም ለማሻሻል ከአጋር አካላት እና ወዳጅ ሃገራት በትብብር እና በቅንጅት መስራት ወቅታዊ መሆኑን በአፅንኦት አብራርተዋል።
መንግሥት የጀመረውን ሃገራዊ የለውጥ ጉዞ ትርጉም ባለው ደረጃ በከፍተኛ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ለማስደገፍ አጋር አካላትን እና ወዳጅ ሃገራትን ድጋፋቸው እንዲጠናከር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ ጠይቀዋል ሲል የዘገበው የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ነው።
ምንጭ፦የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት/EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በሳይንስ እና በከፍተኛ ትምህርት" ዙሪያ ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ለሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅት ተዎካዮች፥ አጋር የልማት ድርጅቶች እና የውጭ ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ "የአጋርነት እና የትስስር" መፍጠሪያ መድረክ በሸራተን አዲስ ሆቴል ተካሄዷል።
በመድረኩ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ፥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አቅም በተሻለ አግባብ ለማሳደግ መንግሥት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህ ረገድ መንግስት ዓለም አቀፍ የአጋርነት ትስስር ፈጠራ ዙሪያ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አቅም ለማሻሻል ከአጋር አካላት እና ወዳጅ ሃገራት በትብብር እና በቅንጅት መስራት ወቅታዊ መሆኑን በአፅንኦት አብራርተዋል።
መንግሥት የጀመረውን ሃገራዊ የለውጥ ጉዞ ትርጉም ባለው ደረጃ በከፍተኛ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ለማስደገፍ አጋር አካላትን እና ወዳጅ ሃገራትን ድጋፋቸው እንዲጠናከር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ ጠይቀዋል ሲል የዘገበው የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ነው።
ምንጭ፦የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት/EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Photoshop የ2012 የዩኒቨርሲቲ ምደባን በሚመለከት በርካታ ሀሰተኛ መረጃዎች እየተሰረጩ ይገኛሉ። በተለይ የTIKVAH-ETHን ስም በመጠቀም የውሸት መረጃዎች እየተሰራጩ ስለሆነ ጥንቃቄ ይደረግ።
ከምደባ ጋር በተያያዘ አዲስ ጉዳይ ሲኖር እናሳውቃለን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከምደባ ጋር በተያያዘ አዲስ ጉዳይ ሲኖር እናሳውቃለን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ተመልከቱ⬆️
የኛም የኢትዮጵያውያን ነገር እንደዚህ እንዳይሆን ከመለያየት ይልቅ መቀራረብ፤ ከመጠላላት ይልቅ መዋደድ፤ ወንድምን እንደ ጠላት ከማየት ይልቅ ቀርቦ መነጋገር፤ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን፤ ለጦርነት ከመዘጋጀት ይልቅ ለሰላም ዘብ መቆም በዚህች ሀገር ማንስፈን አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። የኛ መበላላትን በጉጉት የሚጠብቁ የውጭ ኃይሎች አሉና እርስ በእርስ መተባበራችን እጅግ በጣም ወሳኝ ነው!!
ያለ ሀገር ሁሉም ከንቱ ነው!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኛም የኢትዮጵያውያን ነገር እንደዚህ እንዳይሆን ከመለያየት ይልቅ መቀራረብ፤ ከመጠላላት ይልቅ መዋደድ፤ ወንድምን እንደ ጠላት ከማየት ይልቅ ቀርቦ መነጋገር፤ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን፤ ለጦርነት ከመዘጋጀት ይልቅ ለሰላም ዘብ መቆም በዚህች ሀገር ማንስፈን አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። የኛ መበላላትን በጉጉት የሚጠብቁ የውጭ ኃይሎች አሉና እርስ በእርስ መተባበራችን እጅግ በጣም ወሳኝ ነው!!
ያለ ሀገር ሁሉም ከንቱ ነው!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
AudioLab
ልዩ መረጃ ከኤልያስ ጋር
በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
በTIKVAH-ETH ስም እየተሰራጨ ስለነበረው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒፎርም ጉዳይ ሀሰት ስለመሆኑ በAPው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
በTIKVAH-ETH ስም እየተሰራጨ ስለነበረው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒፎርም ጉዳይ ሀሰት ስለመሆኑ በAPው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የወልድያ-ቆቦ መንገድ በደለል ምክንያት መዘጋቱ ተገለፀ! ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ አልቻሉም። መንገዱ የተዘጋው ከተራራማ ቦታዎች የሚወርድ ደለልን መከላከል የሚያስችል ደጋፊ የግንብ አጥር ባለመኖሩ ነው። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮምቦልቻ መንገድ ዝርጋታ ዳይሬክተር…
#update ትናንት በደለል ምክንያት ተዘግቶ የነበረው የወልድያ ቆቦ መንገድ ለጊዜው ደለሉ ተጠርጎ ከትናንት ማታ ጀምሮ ተሽከርካሪዎች እየተላለፉ ነው፤ ነገር ግን ችግሩ በዘላቂነት ካልተፈታ ዛሬም ከበድ ያለ ዝናብ ከጣለ መዘጋቱ አይቀሬ እንደሆነ #አብመድ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia