TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
የኮሌራ በሽታ ተቀሰቀሰ!

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን በምትገኘው የሻሸመኔ ወረዳ የኮሌራ በሽታ መቀስቀሱ ተሰማ። አንድ የወረዳው ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት የስራ ሃላፊ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ እንደገለፁት ወረርሽኙ ከባለፈው ስምንት መጀመሪያ አንስቶ የታየውና የተቀሰቀሰው በወረዳው ቶጋ፣ ቢሊቻ ፣ ጩሉሌ እና ቄሬሳ በተባሉ የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ ነው።

በአሁኑ ወቅት በበሽታው የተጠቁ ስድስት ሰዎች ወደ ጤና ተቋማት ተወስደው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የወረዳው የጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መሀመድ ገመዴ ተናግረዋል።

አስከአሁን በወረርሽኙ ከተጠቁት ስድስት ሰዎች በስተቀር የሞት አደጋ #አለመድረሱን የፅህፈት ቤቱ ሃላፊ ገልጸዋል። ፅህፈት ቤቱ የበሽታው ስርጭት እንዳይስፋፋ ለማድረግ በአካባቢው በሚሰራጩ የራዲዮ ጣቢያዎች አማካኝነት ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ የጥንቃቄ መልዕክቶችን እያስተላለፈ ይገኛል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia