#update ዛሬ #InnovationEducationInAfrica በቦትስዋና፣ ጋቦሮኒ ተከፍቷል፡፡ በዚህ ኤክስፖ ላይ የመቐለ ዩኒቨርሲቲው መምህር ኢንጂነር #ፊሊሞን_ግደይ /EIT/ ከተመረጡት 40 ፈጣሪዎች መካከል አንዱ በመሆን ተካፋይ ሆኗል።
የመምህር ፊሊሞ ፈጠራ AHADU MOBILE GSM የተሰኘ ሲሆን የትምህርት ቤት አስተዳደር ስርዓት ላይ ትኩረት ያደርገ ነው። ሲስተሙ መምህራን በሞባይላቸው ተጠቅመው ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸውን ላይ ስለመገኘታቸው ለመቆጣጠርና መምህራን በስራ ገበታቸው ላይ እንደተገኙ ለመቆጣጠር፤ መምህራን ለወላጆች ስለተማሪዎቻቸው የትምህርት ሁኔታ ሪፖርት ለማድረግና ወላጆችም በልጆቻቸው የትምህርት ሁኔታ ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሚረዳ ነው።
በኤክስፖው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፅዮን ተክሉ በመምህሩ የፈጠራ ስራ መደሰታቸውን ገልፀው የሀገራችንን ስራዎች አጠንክረን ልናስተዋውቅ ይገባል ብለዋል። ለመምህር ፊሊሞንም እንኳን ደስ አለህ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመምህር ፊሊሞ ፈጠራ AHADU MOBILE GSM የተሰኘ ሲሆን የትምህርት ቤት አስተዳደር ስርዓት ላይ ትኩረት ያደርገ ነው። ሲስተሙ መምህራን በሞባይላቸው ተጠቅመው ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸውን ላይ ስለመገኘታቸው ለመቆጣጠርና መምህራን በስራ ገበታቸው ላይ እንደተገኙ ለመቆጣጠር፤ መምህራን ለወላጆች ስለተማሪዎቻቸው የትምህርት ሁኔታ ሪፖርት ለማድረግና ወላጆችም በልጆቻቸው የትምህርት ሁኔታ ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሚረዳ ነው።
በኤክስፖው መክፈቻ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፅዮን ተክሉ በመምህሩ የፈጠራ ስራ መደሰታቸውን ገልፀው የሀገራችንን ስራዎች አጠንክረን ልናስተዋውቅ ይገባል ብለዋል። ለመምህር ፊሊሞንም እንኳን ደስ አለህ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia