TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#ባለ_2_መኝታ🔝

የመከላከያ ሰራዊት አባል ለሆናችሁ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች በሙሉ፦

የመከ/ሰራዊት ፋውንዴሽን #የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች እጣ የወጣላቸው እና የቤት እድለኞች ቼክሊስት!

#TIKVAH_ETHIOPIA

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባለ_3_መኝታ🔝

የመከላከያ ሰራዊት አባል ለሆናችሁ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች በሙሉ፦

የመከ/ሰራዊት ፋውንዴሽን #የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች እጣ የወጣላቸው እና የቤት እድለኞች ቼክሊስት!

#TIKVAH_ETHIOPIA

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባለ_4_መኝታ🔝

የመከላከያ ሰራዊት አባል ለሆናችሁ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች በሙሉ፦

የመከ/ሰራዊት ፋውንዴሽን #የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች እጣ የወጣላቸው እና የቤት እድለኞች ቼክሊስት!

#TIKVAH_ETHIOPIA

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Breaking_News Loading...
#ሰበር_ዜና በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ በሚገኙ #ሁሉም ዞኖች፣ ከተማ አስተዳደሮች እና ልዩ ወረዳዎች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ #ታውጇል#ETHIOPIA

#State_of_emergency

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደቡብ ክልል ከዛሬ ጀምሮ በኮማንድ ፖስት እንዲመራ ተወስኗል። #state_of_emergency #ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Breaking

"...በክልሉ ባሉ ሁሉም ዞኖች፤ ሀዋሳ ከተማ አስተዳደርና ልዩ ወረዳዎች በፌደራል የፀጥታ ኃይል ቁጥጥር ስር ሆኖ በጊዚያዊ ኮማንድ ፖስት እንዲመራ የክልሉ መንግስት በጠየቀው መሰረት የፌደራል ፀጥታ ምክር ቤት ከሐምሌ 15/2011 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ወስኗል።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ንግድን ለማሳለጥ ከተቋቋመው ኮሚቴ አባላት ጋር እየተወያዩ ነው።
በውይይታቸውም ባለፉት ጥቂት ወራት በሀገሪቱ የተከናወኑ የቢዝነስ እንቅስቃሴዎችን በመገምገም ላይ መሆናቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

በተጨማሪም የሀገሪቱን የቢዝነስ ዘርፍ እንቅስቃሴ ለማሳደግ እየተከናወኑ ባሉ የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜ ግቦች ላይ ሊካሄዱ በሚገባቸው ማሻሻያዎች ዙሪያ እየመከሩ ይገኛሉ።

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሚያ እና የአፋር ክልል መንግስታት ለአማራ ክልል መንግስት አጋርነታቸውን ገለጹ፡፡ የክልል መንግስታት ርዕሰ መስተዳድሮች ትላንት ባህር ዳር በነበረው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በዓለ ሲመት ላይ ታድመዋል፡፡

የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ባስተላለፉት የአጋርነት መልዕክት ‹‹ኢትዮጵያውያን የሚያዋጣን ለጋራ አንድነታችንና ለልማታችን በጋራ መትጋት ነው፤ ፈተናወች የጋራ ቤትን የሚያፈርሱ ከሆነ ማንም አይጠቀምበትም፤ የጋራ ቤት የሆነችውን ኢትዮጵያ በአንድነት ልማቷን እና ሰላሟን አስጠብቆ ለማሻገር መትጋት ይገባል›› ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ አንድነትና ቀጣይነት የማረጋገጥ ትልቅ ኃላፊነት መወጣት ተገቢ መሆኑንም አቶ ሽመልስ አሳስበዋል፡፡

የጥፋት መንገድ እንዳይደገም፣ ኢትዮጵያን ለዘመናት በአዙሪት ውስጥ ያኖራት በውይይትና በዴሞክራሲያዊ መንግድ ችግሮችን የመፍታት ችግር እንዲያበቃ ሁሉም በጋራ መታገል እንደሚገባውም ነው ያሳሰቡት፡፡ የኦሮሚያ ክልል ሕዝብ እና መንግስትም ከአማራ ክልል መንግስት ጎን እንደሚቆሙ አረጋግጠዋል፡፡

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/BDR-07-23-2
#update አሜሪካ ስደተኞችን ፍርድ ቤት ሳታቀርብ ወደመጡበት ሀገር ልትመልስ ነው፡፡ የአሜሪካ መንግሥት ያለፍርድ ቤት ውሳኔ ስደተኞችን ወደ መጡበት አገር መመለስ የሚያስችል መመሪያ አወጣ፡፡

በአዲሱ ደንብ መሰረት ማንኛውም ማስረጃ የሌለው ስደተኛና በተከታታይ ለሁለት ዓመት አሜሪካ ውስጥ እንደነበር ማረጋገጥ ያልቻለ ግለሰብ ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ይደረጋል። ፖሊሲው ዛሬ ይፋ ተደርጎ በሁሉም የአሜሪካ ግዛቶች በአፋጣኝ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል ተብሏል።

አሜሪካን ሲቪል ሊበርቲስ ዩኒየን የተባለ የመብት ተሟጋች ቡድን ፖሊሲውን በመቃወም ፍርድ ቤት ወስዶ ለመሟገት ማሰቡን ተናግሯል። የአሜሪካ የስደተኞች ፖሊሲ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጥብቅ እየሆነ መምጣቱ ይታወቃል፡፡

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ደጋማው ክፍል በተነሳው የእሳት ቃጠሎ የደረሰውን ውድመት ለማካካስ ከ38 ሺህ በላይ ሀገር በቀል ችግኞች መተከላቸውን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አበባው አዛናው እንደገለፁት የችግኝ ተከላው በተያዘው ዓመት መጋቢትና ሚያዚያ ወር በፓርኩ ውስጥ በተነሳው የእሳት አደጋ የደረሰውን ጉዳት መልሶ ለመተካት ነው፡፡

ችግኞቹ የተተከሉትም ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ ሁለት ሺህ የሚደርሱ ወጣቶችና የዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አባላትን በማሳተፍ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡

በፓርኩ ውስጥ በህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተተከሉ ያሉ ችግኞች በፍጥነት የሚያድጉና ለአካባቢው ስነ-ምህዳር ተስማሚ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ከ60 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን እስካሁን በተካሄደ እንቅስቃሴ አብዛኛውን ማሳካት እንደተቻለ ተመልክቷል፡፡

ምንጭ፡-ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኮምቦልቻ

"እኛ የኢትዮጵያ መንገዶችን ባለስልጣን የኮምቦልቻ መንገድ አውታርና ደህንነት ማኔጅመንት ሰራተኞች በዶ/ር አብይ የተጀመረውን የችግኝ ተከላ ፕሮጀክት ጀምረናል።" ሀይሉወሰን በቀለ ከኮምቦልቻ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert አቶ አህመድ ቡህ #የድሬዳዋ_ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሆነው ተሾሙ። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አቶ አህመድ ቡህን የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሾመ።

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ የስራ ዘመን 6ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በዛሬው እለት አካሂዷል። ምክር ቤቱ በዛሬው እለት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤው ካለፈው መጋቢት ወር 2011 ዓ.ም መጀመሪያ ጀምሮ በከንቲባነት ያገለገሉትን የአቶ መሐዲ ጊሬን መልቀቂያ ተቀብሏል። በምትካቸውም አቶ አህመድ ቡህን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሹሟል፡፡

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በአስቸኳይ ጉባዔው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የአፈ ጉባኤ አብደላ አህመድን መልቀቂያ መቀበሉም ተገልጿል። በምትካቸውም ወይዘሮ ፈጡም ሙስጣፋን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የአፈ ጉባኤ አድርጎ ሾሟል።

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሰኔ_15 #ባህር_ዳር

የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ እና ፍትሕ አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰኔ 15/2011 ዓ.ም ለተፈጠረውን ችግር የፀጥታ ተቋማት መደማመጥ አለመቻል እና ወጥ የሆነ የአመራር ሂደት አለመስጠታቸው እንደሆነ አመለከተ፡፡

የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ እና ፍትሕ አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ በጋራ የተስማማባቸውን ዋና ዋና ጉዳዮች በክልሉ ምክር ቤት 5ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ አቅርቧል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ሰኔ 15/2011 ዓ.ም የተፈጠረውን ችግር የተመለከተ ጉዳይ አቅርቧል፡፡ የጥፋት መንስኤው የፀጥታ ተቋማት አመራሮች መደማመጥ አለመቻል እና ወጥ የሆነ የአመራር ሂደት ባለመኖሩ መሆኑን ለምክር ቤት አባላቱ ግልጽ አድርጓል፡፡

በክልሉ መንግሥት የሠላም እና ደኅንነት ተቋም ላይ ችግሮች ከመከስቱ በፊት የፖለቲካ አመራሩ አስቀድሞ ዋነኛ መንስኤዎችን እየለዬ መፍታት ባለመቻሉ የተከሰተ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ ሰኔ 15/2011ዓ.ም የተፈፀመው ድርጊት የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት በመቆጣጠር በወቅቱ ስብሰባ ላይ የነበሩ ከፍተኛ መሪዎችን በመክበብ ግድያ መፈጸሙ፤ በቡድን መሳሪያ ጭምር በመጠቀም ስልጣን ለመያዝ የተፈፀመ መሆኑን ነው ቋሚ ኮሚቴው ያቀረበው፡፡ የክልሉ ሕዝብ፣ የክልሉ እና የፌዴራል ፀጥታ አካላት ችግሩን ለመፍታት ባስተዋይነት ለወሰዱት ፈጣን እርምጃ እና መሰዋዕትነት ለከፈሉት ወዳጅ ዘመዶቻቸው የክልሉ ምክር ቤት መፅናናትን እየተመኘ በማንኛውም ወቅት ከጎናቸው መሆኑን አረጋግጧል፡፡

አሁንም ቢሆን በወቅቱ የተፈጸመውን ድርጊት ለመሸፋፈን መሞከር እና የድርጊቱ ፈፃሚዎችን ከተጠያቂነት እንዲያመልጡ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተቀባይነት እንደሌለው አስረድቷል፡፡

ተጨማሪ👇
https://telegra.ph/AM-07-23

@tikvahethiopia