TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
61.5K photos
1.55K videos
215 files
4.26K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ ጥሎ የቆየውን ማእቀብ #ሊያነሳ ነው። ማእቀቡ የሚነሳው ከ11 ቀናት በሁዋላ በሚደረግ ስብሰባ ላይ ሲሆን ይህም የሚሆነው አሜሪካ በኤርትራ ላይ ይዛው የቆየችውን አቋም በመቀየሯ ነው ተብሏል። ማእቀቡ ከተነሳ በሁዋላ ኤርትራ እንደፈለገች የጦር መሳርያ መግዛት ትችላለች።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት(AP)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኤርትራ ማዕቀቡ ሊነሳላት ነው‼️

የመንግስታቱ ድርጅት የኤርትራን #ማዕቀብ በነገው ዕለት #ሊያነሳ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ ላለፉት 10 ዓመታት ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ለማንሳት ውሳኔዎች እንደሚያስተላልፍ ተገልጿል፡፡

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ያደረገችውን የሰላም ስምምነት እንዲሁም ከጅቡቲ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሻሻል ያደረገችውን ጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው ማዕቀቡን ለማንሳት የፀጥታው ምክር ቤት አባላት ተደራድረው የጨረሱት፡፡

ሮይተርስ የድርጅቱን ዲፕሎማቶች ጠቅሶ እንደዘገበው ማዕቀቡን ለማንሳት በእንድሊዝ የቀረበውን ረቂቅ 15 የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባላትያለልዩነት እንደሚቀበሉት ይጠበቃል፡፡

ኤርትራ የሶማሊያውን አልሸባብ ለሚባለው ቡድን እገዛ ታደርጋለች በሚል እንደአውሮፓዊያኑ አቆጣተር በ2009 አ.ም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማዕቀቡን እንደጣለባት ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia