TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
‹‹ስለ #ድብቅ_እስር_ቤቶች የማውቀው ነገር የለም፡፡›› የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር

የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ስለ ድብቅ እስር ቤቶች የማውቀው ነገር የለም ብሏል፡፡

በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ስር ያሉ 6 ማረሚያ ቤቶች ቃሊቲ፣ቂሊንጦ ፣ ዝዋይ፣ ሸዋሮቢት፣ ድሬዳዋና ቃሊቲ የሴቶች ማረሚያ ቤት ብቻ ናቸው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ጀማል አባሶ ጠቅላይ አቃቢ ህግ በምርመራ ያገኛቸው እስር ቤቶች ከእኛ እውቅና ውጭ ያሉ ናቸው ብለዋል፡፡

የሰብዓዊ መብት አያያዝን ለማሻሻልም ዘመናዊ ማረሚያ ቤቶችን እየገነባን ነው ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ጀማል አባሶ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቀዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia