TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.5K photos
1.59K videos
216 files
4.33K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
በሌላ በኩል...

ባለፈው ሐምሌ #በሱማሌ_ክልል በተከሰተው ሁከት ከከሰስኳቸው ተከሳሾች መካከል ከድር አብዲ እስማኤልን #በስህተት ነው የከሰስኳቸው- ብሏል ዐቃቤ ሕግ፡፡ ተከሳሹ አርሶ አደር እንጅ የመንግሥት ባለስልጣን እንዳልነበሩ ባላፈው ለችሎቱ ካስረዱ በኋላ ዐቃቤ ሕግ ባደረገው ማጣራት ነው፡፡ ችሎቱም ተከሳሹ እንዲለቀቁ ማዘዙ ተሰምቷል፡፡ ተከሳሽ አብዲኑር መሐመድ አሕመድ በበኩላቸው የአያቴ ስም የሱፍ ነው ያሉ ሲሆን ሃኒ ሀሰን ደሞ ስማቸው ዘምዘም መሆኑን ጠቅሰው ተከራክረው ነበር፡፡ ሀሰን አይዲድ በደል ራጌ ማዕረጌ ሻምበል አይደለም፤ ምክትል ኢንስፔክተር ነኝ ሲሉ በስህተት መከሰሳቸውን አቤት ብለው ነበር፡፡ ዐቃቤ ሕግ ግን ስማቸውን ሆን ብለው ስለሚቀይሩ ነው በማለት ተከራክሯል፡፡ የችሎቱ ብያኔ ሐምሌ 11 ይጠበቃል፡፡

Via #wazema/የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ/
🗞ቀን 13/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#COVID19

የሱማሌ ክልል ሞያሌ ወረዳ ሰራተኞች ተመርመሮ ኮሮና ቫይረስ እንደያዘው የታወቀን ግለሰብ ከለይቶ ማቆያ መልቀቃቸው አግባብ አይደለም ሲሉ የቦረና ዞን የጤና ቢሮ ኃላፊዎች ተችተዋል።

ግለሰቡ የምርመራ ውጤቱ ከተላከበት ሳይመለስ ተለቋል ሲሉ የቦረና ዞን የጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሮባ ዴንጌ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

የሱማሌ ክልል የሞያሌ ወረዳ የጤና ክትትል ኃላፊ ግለሰቡ የተለቀቀው #በስህተት ነው ሲሉ ምላሻቸውን ለሬድዮ ጣቢያው ሰጥተዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DrLiaTadesse በኢትዮጵያ ተጨማሪ 15 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3,707 ላቦራቶሪ ምርመራ 15 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 287 ደርሷል። ቫይረሱ የተገኘባቸው ሁሉም ወንድ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ እድሜያቸው ከ17 እስከ 38 ዓመት የሆኑ ናቸው። ቫይረሱ የተገኘባቸው 8…
#DrLiaTadesse

ዛሬ በፌደራል ደረጃ በተሰጠው የኮቪድ-19 ዕለታዊ መረጃ ላይ በቤንሻንጉል ጉሙዝ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሁለት (2) ሰዎች ከታች ጉባ ለይቶ ማቆያ ተብሎ የተጠቀሰው #በስህተት መሆኑንና የጉባ ነዎሪዎች ቢሆኑም #በፓዌ ለይቶ ማቆያ የሚገኙ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ #ከይቅርታ ጋር አሳውቀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia