TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
የሪፐብሊኩ የጥበቃ ኃይል🔝

ጠቅላይ ሚነስትር ዶክተር #ዓብይ_አሕመድ በዛሬው ዕለት  ከሪፐብሊኩ የጥበቃ ኃይል አባላት ጋር ተገናኝተዋል።

የሪፐብሊክ የጥበቃ ኃይል የአገሪቱን ህገ መንግሥትና ህገ መንግስታዊ ስርዓት ከማንኛውም ጥቃት ለመከላከል በአዲስ የተቋቋመ የደህንነት መሳሪያ አካል መሆኑ ተገልጿል።

የሪፑብሊክ የጥበቃ ኃይል አባላት የመንግስት ባለስልጣናትንና እና ቤተሰቦቻቸውን የጥቃት ዓላማን አንግበው በሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ከሚሰነዘር ጠለፋና እንግልት ለመከላከል የተቋቋመ ነው።

ይህ የሪፐብሊክ የጥበቃ ኃይል በከፍተኛ የአመራር ስልጣን ላይ ያሉትን ኃላፊዎች ከማንኛውም ስጋት እና ጥቃቶች ለመጠበቅ አስፈላጊ የሆነውን ማንኛውንም ዘዴ መጠቀም ዋነኛ ተግባሩ ነው ተብሏል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጥበቃ አባላቱ ጋር በነበራቸው ቆይታ ላይም የሪፐብሊኩ የጥበቃ ኃይል አባላት የተሰጣቸውን ሃለፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን የሚያሳይ ትርዒት አቅርበዋል።

ባለፉት ስደስት  ወራትም ይህ ሃይል እራሱን በሰለጠኑ የደህንነት ባለሙያዎችና በተገቢው መንገድ ተግባሩን ለማከናወን የሚያስችሉ ቁሳቁሶችን እያደራጀና ስልጠናዎች እያደረገ መቆየቱን ከጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ምንጭ፦fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia