TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ኢንጅነር ታከለ ኡማ⬆️

#ከንቲባው_ሰኞን_በኩሺና_ጀመሩ !!
====================
የአዲስ አበባ መዘጋጃ ቤት የምግብ ሰራተኞች የከንቲባው ቢሮ ስታፎች ቢሆኑም ላለፉት 27 ዓመታት የከተማዋን ከንቲባ እንደማንኛውም ሰው በቴሌቪዥን ብቻ ነበር የሚያዩት።

#ዛሬስ_ምን_ተፈጠረ ??

=>> ዛሬ ሀምሌ 14 በእለተ ሰኞ ግን ሰርፕራይዝ ተደረጉ። ሰው ሰው የሚሸት መሪ ሀገርን ሲመራ ሁሉም አመራር ሰው ሰው ይሸታል ለካ ብለውም ተገረሙ።

#ምን_አስገረማቸው ??

=>> እንደተለመደው እነዚህ ታታሪ ሰራተኞች በጠዋት የስራ ገበታቸው ለይ ተገኝተዋል። በስራም ተጠምደው ደፋ ቀና ይላሉ።

=>> ከንቲባ ታከለ ኡማ ዛሬ በጠዋቱ ድንገት በግቢያቸው ውስጥ ያለውን ምግብ የሚሚያበስሉ ሰራተኞች ክፍል ድንገት ዘው ብለው #ተገኙ

ሰራተኞቹ በዱብዳው ተደናገጡ።
አይዝዋችሁ አትደንግጡ ገና ምን አያችሁ። አብረን እየተጨዋወትን ቁርስ እንብላ አሉ የተከበሩት ከንቲባ። ቁርሳቸውንም አብረው እየተሳሳቁ እየተጨዋወቱ ተመገቡ።

#ሰው_ሰው_የሚሸተውን_ያብዛልን!!

©Brook Senior Qawweessaa
@tsegabwolde @tivahethiopia
ከልዩነታች ይልቅ #አንድነታችን እጅግ እንደሚገዝፍ በቅዱሳን መፃህፍትም ሆነ በሳይንስ ተረጋግጦ ሳለ ይበልጥ #ልዩነታችን ላይ ማተኮራችን ምክንያቱ ምን ይሆን 🔅ሶስት ማዕዘን
.
.
ሁላችንንም #አንድ የሚያደርገን ከኢትዮጵያዊነታችን፤ የአንድ ብሄር ተወላጅ ከመሆናችን በላይ #ሰው መሆናችን ነው። ስለሰውነት በቅጡ #መረዳት ካልቻልን መጪው ጊዜ ይከፋብናል። ሁላችንም ስለሰው ክቡርነት እንነጋገር፤ ማንም ሰው በብሄሩ፣ በዘሩ፣ በሀይማኖቱ ሳይሆን ሰው በመሆኑ ብቻ #ሊከበር ይገባዋል!!

ለ30 ደቂቃ በዚህ ጉዳይ ተነጋገሩ...
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከሀዋሳ...

"እኛ ኢትዮጵያዊያን በሚያሳዝን ሁኔታ ለሰው ያለን ክብር እየተሸረሸረ ነው። አሁን አሁን ሁሉም ነገር ከብሔር ጋር ተያያዘና #ሰውነት ቦታን አጣ። በሚገርም ሁኔታ አሰፋ መዝገቡ የሚነግረን የትራፊክ አደጋ መረጃ ብቻ ሆኗል ብሔር ሳይለይ ይሄን ያህል #ሰው ሞተ እና ቆሰለን የምንሰማበት። ሌላው ነገር ሁሉ ከብሔር የተገናኘ ሆኗል።
መፍትሔ የሚመስለኝ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ወደ ቀልቡ ይመለስ። ድሮ ይወድ የነበረውን ወንድሙን ለምን ጠላሁ ብሎ ይጠይቅ?? ያኔ ወደየቀልቡ ይመለሳል። አማኑኤል ከሐዋሳ ዪኒቨርስቲ።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዜግነትና የብሄር ፖለቲካ ተቃርኖ መዳረሻ...

በኢትዮጵያ ማንኛውም ዓይነት የፖለቲካ አቋምን ማራመድ መብት ቢሆንም፤ ልቀው የወጡት የዜግነትና የብሄር የፖለቲካ አስተሳሰቦች ግን በተቃርኖ የተሞሉ በመሆናቸው፤በተለይ ከዜግነት ይልቅ የብሄር ፖለቲካ የበላይነትን እያገኘ በመምጣቱ የተቃርኗቸው መዳረሻ አሳሳቢ ሆኗል። #በአርባ_ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምርት ቤት ኃላፊ አቶ ደርሶልኝ የኔአባት እንደሚሉት፤ የዜግነት ፖለቲካ በአብዛኛው በሰለጠኑት በምዕራባውያን አገራት የሚቀነቀን ሲሆን፤ በግለሰቦች ነጻነትና በዜጎች እኩልነት ላይ የተመሠረተ ነው። የሰለጠነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ተደርጎም ይወሰዳል። ሰው #ሰው በመሆኑ ብቻ በየትኛውም የፖለቲካ ተሳትፎ ተጠቃሚ የሚሆንበት እንዲሁም ከየት መጣ፣ የትኛው ብሄር ነው የሚለውን ግንዛቤ ውስጥ የማያስገባ ነው።

ተጨማሪ ለማንበብ👇

https://telegra.ph/የዜግነትና-የብሄር-ፖለቲካ-ተቃርኖ-መዳረሻ-02-22-3
"ሀረር ለመኖር #ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው!" ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በመሩት ውይይት ላይ ከሀረር የመጡ የሀይማኖት አባት የተናገሩት!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሴትነት!

#ሴትነት ሰው የመሆን ሁለንተናነት ነው። አንድ ሰው የሴትነትን ታላቅነት ካልተረዳ ገና #ሰው የመሆንን ሚስጢር አልተገነዘበም ማለት ነው። ምክንያቱም ሴት እናት ነች። እናት ደግሞ የማያልቅ ዘላለማዊ ፍቅርን በስስት የምትለግሰን #የፍቅርን ምንነት መገለጫ ናት። ታዲያ ከፍቅርና ፍቅርን ከማወቅ በላይ ምን ታላቅ የህይወት ሚስጢር ይኖራል? ምንም አይኖርም።

ሌላው ታላቅ ከሚያደርጓት ነገሮች ደግሞ በህይወት ውስጥ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተጋፍጣ #በብልሃት እና #አሸናፊነት የምትወጣ ጠንካራ ፍጥረትነቷ ነው።

ሩህሩህነትን ከአፍቃሪነት ጋር ታድላ የተፈጠረች ለወንድ የህይወቱ ማገር እና ምሶሶ ናት። ወንድ ያለ ሴት ሙሉነት እና የህይወት ጣእም የሌለው ያላለቀ የእግዜር ጅምር ስራ ነው።

ሴት ልጅ ስቃይዋን እና ሃዘኗን መደበቅ ካስፈለጋት መከፋትዋን ሳታሳይ ደስተኛ በመምሰል ለምትወደው ሃሴትን መስጠት የምትችል ረቂቅ ፍጠረት ናት።

ሴትነትን ሆነው ካላዩት በእርግጥ ስለ ሴትነት ሙሉ በሙሉ መናገር የሚቻለው አይኖርም። ረቂቅ እና የህይወት ጣእም ሚስጢር አድርጎ ከፈጠራት ፈጣሪ በስተቀር።

ሴት ልጅ ከወንድ የጎን አጠንት ብትሰራም በህይወት ዘመኑ የጀርባ አጥንቱ ሆና ብርታትን እና ፀናትን የምትሰጠው “ሃይል” ናት። የታላላቅ ስኬቱ ጀንበር ሆና የምትፈነጥቅለት ነገር ግን ከእርሱ ልቃ የማትታይ የመድመቂያው ጮራ መፍለቂያ ናት።

ሴት ልጅ ከልብ የመነጨ ክብር ይገባታል። ሴትን የሚያከበር ራሱን #የሚያከብር ነው። ሴትን የማያከብር ቢኖር የህይወትን ጣእም እና ፍቅርን ካለማወቁም በላይ ሰው የመሆን ብቃት የጎደለው ነው።

ምንጭ ፦ ደንቢያ(ከማህበራዊ ድረ ገፅ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"#ሰው_መሆን"

ሰው ማህበረሰብን ይፈጥራል፣ ሰው አከባቢን ይገነባል፣ ሰው ሀገርን ይፈጥራል፣ ሰው የተለያየ የቆዳ ቀለም ሊኖረው ይችላል፣ ሰው ልዩ ልዩ ባህሎችም ይኖሩታል የተለያየም ቋንቋ ተናጋሪ ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉም ሰው ግን ሰው በመሆኑ ብቻ ክቡር ፍጥረት ነው፡፡

"ሰው መሆን" ልዩ የባህል አልባሳት ፋሽን ሾው

በዚህ ዝግጅት ላይ የተለያዩ የሀገራችን ባህላዊ አልባሳት ልዩነት ሳይገድባቸው በአርባምንጭ ከተማ በሀይሌ ሪዞርት በአንድ መድረክ ይደምቃሉ፡፡ በዝግጅቱ መሳተፍ የምትፈልጉ ዲዛይነሮች አልባሳቶቻችሁን በነጻ እንድታስተዋውቁ ተጋብዛችኋል፡፡ ዝግጅቱን በመደገፍ ለመሳተፍ የምትፈልጉም አግኙን፡፡

የዝግጅቱ ዓላማ
ሰው መሆንን ተረድተው ለዘመናት የሀገራችን ባህሎችና ቋንቋዎች በፍቅር አብረው መኖራቸውንና ዛሬም በአንድ ቦታ በአንድ መድረክ አብረው ሲሆኑ እንደሚደምቁ ማሳየት!

የዝግጅቱ ቦታ
ሀይሌ ሪዞርት /አርባምንጭ

ለበለጠ መረጃ
☎️ +251949142388
☎️ +251925114045
☎️ +251913134524

አዘጋጆች
ፒስ ሞዴል ኢቨንት እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋሞ ዞን አስተዳደር ጋር በመተባበር የተዘጋጀ!
በሃላይደጌ ፓርክ በተከሰተ የእሳት አደጋ እስካሁን ከ100 ኪሎ ሜትር እስኩየር በላይ ሳርና ቁጥቋጦ ወድሟል !

ባለፈው ሀሙስ ቀትር ላይ በፓርኩ ሰሜናዊ ክፍል የተከሰተውን የእሳት አደጋ በአብዛኛው መቆጣጠር እንደተቻለ የፓርኩ አስተባባሪ አቶ መሐመድ እድሪስ ተናግረዋል።

አደጋውን ለመቆጣጠር ባለፉት 3 ቀናት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።

የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር ፦

- የአፋር ክልል እሳት አደጋ መከላከያ ቡድን፣
- የክልሉ የልማት ድርጅቶች፣
- የአሚባራና ሃሩካ ወረዳ ነዋሪዎች እና አመራሮች
- የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ከፍተኛ ተሳትፎና ጥረት ማድረጋቸው ተገልጿል።

በአካባቢው ባለ ከፍተኛ ንፋስና ሙቀት ቃጠሎውን ፈጥኖ ለመቆጣጠር አላስቻለም ተብሏል።

እስከ ትናንት ምሽት ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ በነበረባቸው አካባቢዎች እሳቱን ለማጥፋት በተደረገ ጥረት አብዛኛውን ክፍል መቆጣጠር እንደተቻለ ተነግሯል።

ዛሬም በፓርኩ የተለያዩ ቦታዎች ላይ ተበታትነው የሚገኙ አነስተኛ እና ቀላል እሳቶችን የማጥፋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የተጠቆመ ሲሆን አደጋው በቁጥጥር ስር የሚውልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ተብሏል።

ለ3 ቀን በዘለቀው ቃጠሎ ከ100 ኪሎ ሜትር እስኩየር በላይ የሸፈነ ሳርና ቁጥቋጦ ሙሉ በሙሉ ውድሟል።

በቃጠሎው በዱር እንስሳት እንዲሁም በአእዋፎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተጠቁሟል።

የእሳት አደጋው መንሰኤ #ሰው_ሰራሽ መሆኑን ተገልጿል።

ዝርዝር የአደጋው መንስኤና የጉዳት መጠን በሚመለከታቸው አካላት ተመርመሮ ይገለፃል ተብሏል። ~ ENA

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሃላይደጌ ፓርክ በተከሰተ የእሳት አደጋ እስካሁን ከ100 ኪሎ ሜትር እስኩየር በላይ ሳርና ቁጥቋጦ ወድሟል ! ባለፈው ሀሙስ ቀትር ላይ በፓርኩ ሰሜናዊ ክፍል የተከሰተውን የእሳት አደጋ በአብዛኛው መቆጣጠር እንደተቻለ የፓርኩ አስተባባሪ አቶ መሐመድ እድሪስ ተናግረዋል። አደጋውን ለመቆጣጠር ባለፉት 3 ቀናት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል። የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር ፦ - የአፋር ክልል…
የእሳት አደጋው ከ4 ቀናት በኃላ በቁጥጥር ስር ዋለ።

በሃላይደጌ አሰቦት ዕጩ ብሄራዊ ፓርክ ተነስቶ የነበረውን የእሳት አደጋ ከአራት ቀናት ጥረት በኋላ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉ ተገልጿል።

በፓርኩ ሰሜናዊ ክፍል መጋቢት 2 ቀን 2013 ዓ/ም የተቀሰቀሰው የእሳት አደጋ መንስኤው #ሰው_ሰራሽ መሆኑ ከዚህ ቀደም መገለፁ አይዘነጋም።

ለአራት ቀናት የቆየው የእሳት አደጋ ከ100 ኪሎ ሜትር ስኩየር በላይ የሚሸፍን ቦታ ላይ በነበረ የፓርኩ ሳር ፣ ቁጥቋጦ ፣ የዱር እንስሳትና አእዋፍ ላይ ጉዳት ማድረሱን ኢዜአ ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እርምጃ ተወስዶባቸዋል " በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ሰው በማገት ፣ ሰው በመግደል ሲፈለጉ የነበሩ 3 ግለሰቦች እርምጃ እንደተወሰደባቸው የመተማ ወረዳ ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት አስታወቀ። የወረዳው ሰላምና ደህንነት ፅ/ቤት ፥ " የማህበረሰብ እንቅስቃሴ ሲያውኩ የነበሩ ሶስት ጸረ-ሰላም ኃይሎች በጥምር የጸጥታ ኃይል (ልዩ ኃይል ፣ ፀረሽምቅ እና ፖሊስ) ርምጃ ተወስዶባቸዋል " ብሏል። በጣምራ…
#Metema

የመተማ ወረዳ ፖሊስ #ሰው_በማገት_ወንጀል ሲፈለጉ የነበሩ ግለሠቦች በተካሄደ ኦፕሬሽን መመታታቸውን እንዲሁም ቆስለው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳወቀ።

ትላንት በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ መቃ ቀበሌ ልዩ ስሙ " ጎርድም " በተባለው ተራራ በተደረገ ኦፕሬሽን ሰው በማገት ወንጀል ሲፈለጉ የነበሩ 4 ግለሰቦች መመታታቸው እና ቆስለው በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።

ፖሊስ ይፋ ባደረገው መረጃ ባዜ ብርሀኑ እና ላቀው የኔሁን የተባሉ ግለሰቦች የተመቱ ሲሆን አያናው አማረ እና ወርቁ ድረስ የተባሉ ግለሰቦች ደግሞ ቆስለው በህግ ጥላ ስር መሆናቸው ተገልጿል።

ከቀናት በፊት በዚሁ በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ሰው በማገት ፣ ሰው በመግደል ሲፈለጉ የነበሩ 3 ግለሰቦች እርምጃ እንደተወሰደባቸው የወረዳው ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ማስታወቁ ይታወሳል።

በሌላ በኩል ፤ በወረዳው አኩርፈው ሆነ ሸፍተው የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በተደረገው የምህረት አዋጅ እድል ተጠቅመው በሰላም ገብተው ከህብረተሰቡ ጋር በሰላም እንዲኖሩ ፖሊስ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Adama ሰላም ሚኒስቴር " የአገር ግንባታ መሠረታዊያን በሚል ርዕስ ለሚዲያ አካላት ከቅን ልቦች በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር " ትላንት በአዳማ ከተማ የአንድ ቀን የምክክር መድረክ አካሂዶ ነበር። በመርሀ ግብሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላም ሚኒስትር አቶ ታዬ ደንደኣ፣ መሰል የውይይት መድረክ በኢትዮጵያ ለሚስተዋለው ግጭትና አለመግባባት መፍትሄ ሊያመጣ እንደሚችል…
#ETHIOPIA

" ለመሆኑ ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ ? " - አቶ ወንድሙ ኢብሳ

" መከላከያ ወንድሞቹን መግደል የለበትም፤ ወንድሞቹም መከላከያን መግደል የለባቸውም " - አቶ ታዬ ደንደአ


ሰላም ሚኒስቴር ረቡዕ ኅዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም አዳማ ከተማ አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ የተጋበዙት ጠበቃና የሕግ አማካሪ አቶ ወንድሙ ኢብሳ፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሌሎችም ጋዜጠኞች ፦
° ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ለማምጣት እየሄደበት ያለው ሁኔታ ፣
° ሁለት ጊዜ የከሸፈው የመንግሥትና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት / " ኦነግ ሸኔ " ድርድርን በተመለከተ የተሻለ አማራጭ ሊመጣ የሚችለው ምን ቢደረግ እንደሆነ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ተከታዮቹን ምላሾች እንካችሁ ብለዋል።

አቶ ወንድሙ ኢብሳ ስለሰላም ሚኒስቴር ምን አሉ?

* የሰላም ሚኒስቴር ላይ ጥያቄ አለኝ። ለመሆኑ እራሱ ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ ? ሰላም ሚኒስቴር በራሱ ጊዜ ሰላምን መስበክ አለበት በስውርም በአደባባይም ፡ አሁን ላይ ሰላም ሚኒስቴር ውስጥ የማያቸው ሰዎች በስውር አማፂያንን ሲደግፉ አያለሁ።

* ለምሳሌ የሁለተኛው የ " ሸኔ " እና የመንግሥት ድርድር ሲደረግ ከሰላም ሚኒስቴር ውስጥ የሆኑ ሰዎች (ስማቸው ከተፃፈ አላውቅም) ከሕውሓት ጋር የተደራደርክ፣ ሰላም የፈጠርክ " ሸኔ " ኦሮሞዎችን ለምንድን ነው እነርሱ የጠየቁትን ጥያቄ በሙሉ መልስ እሺ ያላልከው ? ያሉ አሉ።

* ጥያቄያቸው ደግሞ (የሸኔ) " የሽመልስ አብዲሳ ቦታ ለእኛ ይሰጠን፣ የኦሮሚያ መንግሥት አሁን ያለው ይፍረስና አዲስ ምርጫ ይካሄድ የሚል ነበር። ሰላም ሚኒስቴስ ውስጥ ሆኖ ይህን የሚጠይቅ ሰው ስላለ ሰላም ሚኒስቴር ጤናማ አይመስለኝም።

* አንድ ኢንጅነር ቢመረቅና ሥራ ቢያገኝ ለበርካታ ሰዎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል። ፖለቲከኛ ግን 'ስንት ሰው ልግደል' ነው የሚለው። በእኔ ምክንያት አንድ። ሰው መሞት የለበትም የሚል ፓርቲ ያስፈልጋል። በፖርቲ ሥም የሚፈጠር ሞትን የኢትዮጵያ ሕዝብ #ማውገዝ አለበት።

የመንግሥትና የሸኔ (ኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) ድርድር ዘላቂ መፍትሄው ምንድን ነው ? ለሚለው ጥያቄም፣ መንግሥትና የ " ሸኔ " ድርድር አሁንም መቀጠል አለበት ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ተሳታፊ ጋዜጠኞችና ሌሎች ምሁራን በበኩላቸው ፦

° ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየሄደበት ባለው ተደጋጋሚ መንገድ ለሰላም ለውጥ ማምጣት ይችላል ወይ ?

° በግጭት ምክንያት
#የሚፈናቀሉ ሰዎችን አሁንም ማስቆም አልቻለም በዚህ ሁኔታ እንዴት ሰላምን መፍጠር ይቻላል ?

° መስሪያ ቤቱ ሰላምን ልማስረፅ ምን እየሰራ ነው ?

° የሚቀርቡ ጥናታዊ ፅሑፎች ለችግሮችን ይመጥናሉ ወይ ?

° በተጨባጭ መሬት ላይ ያለው ችግር እንዴት ይታያል ?

° በአማራና በኦሮሚያ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመፍታት ለምን መግባባት ላይ ማድረስ አልተቻለም ?.... የሚሉ ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል።


የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንድአ ምን ምላሽ ሰጡ ?

- ብዙ ሥራ እየሰራን መጥተናል ገና ብዙ ይቀረናል። ነገር ግን የሚገባንን ሁሉ #ሥልጣን ተሰጥቶናል ብለን አናምንም እንደ ሰላም ሚኒስቴር። አዎንታዊ ሰላም ከማስረፅ አኳያ ትልቅ ስልጣን አለን እየሰራን ነው። የሰላም ችግር ሲፈጠር፣ #ሰው ሲፈናቀል ያንን የማስቆም ስልጣን ግን ለእኛ አልተሰጠንም። ይሄ #የአወቃቀር ችግር ነው።

- የአደጋ ሥጋት እንኳ #ለእኛ አይደለም ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስቴር ፅሕፈት ቤት ነው። #ፓሊስ ለእኛ ተጠሪ አይደለም። መሆን የነበረበት እዚህ ነው። #የግጭት ሥጋት ሲኖር የምናዘው አንድም #ሚሊሻ የለንም። ስለዚህም ለሚፈጠሩ ግጭቶች የሰላም ሚኒስቴር #ሊወቀስ_አይገባም

- ትክክል ነው በተመሳሳይ አይነት ሥራ የተለየ ውጤት አይፈጠርም። በእኛ በኩል ግን ተመሳሳይ ሥራ እየሰራን ነው ብለን አናምንም። 

- ጥናታዊ ፅሑፎች እና በመሬት ላይ ያለውን ችግር በተመለከተ ለተነሳው ጥያቄ፣ የስልጣን፣ የኢኮኖሚ፣ የፍትህ ችግሮች አሉብን። ሥልጣን ካልተገደበ፣ ተጠያቂነት ካልተረጋገጠ፣ ኢኮኖሚው በፍትሃዊነት ካልተሰራጨ፣ ሌቦች ከተቆጣጠሩት…ሰላም ሊመጣ አይችልም።

- የተሰጠን ስልጣን ወቅታዊ ችግር መፍታት ሳይሆን ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት ነው። 

- ተጠያቂነትን መስፈን አለበት። ከተጠያቂነት አኳያ ደግሞ ሥልጣን የተሰጣቸው አሉ። ለምሳሌ የፍትህ ሚኒስቴሩ ሥራው ተጠያቂነትን ከማስፈን አኳያ መሆን ነበረበት #ድርድር ከመሄድ ይልቅ።

- ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ? ለሚለው ጥያቄ አዎ ሰላም ነው። ሰላም የማንሆንበት ምክንያት የለንም። እኛ እያደረግን ያለነው የአገር አንድነት እንዲጠናከር፣ ሰላም እንዲሰፍን ተባብረን እየሰራን ነው።

- በኦሮሚያ ክልል ለ5 ዓመታት ጦርነት እየተካሄደ በአማራ፣ በኦሮሚያ ክልል የሚስተዋለው ችግር አለ። የትግራይ ክልሉም በጣም ይጸጽተናል። ግን ይህንን የሚያደርገው ከጀርባ ያለው ማነው? እሱን ነው ማወቅ የሚያስፈልገው።

- መከላከያ ሰራዊት ወንድሞቹን መግደል የለበትም፤ ወንድሞቹም መከላከያን መግደል የለባቸውም። ከብሔርተኝነት አኳያ ኦሮሞም ፣ አማራም ፣ ትግራይም በጣም አስቸጋሪ ችግር ነው ያለው። ለአማራ ችግር ኮዙ ኦሮሞ ነው፣ ለትግራይ አማራ ነው ተብሎ ይወሰዳል። ግን ችግሩ በእውነት ምንድን ነው ? ከዚያ ጀርባ ያሉት እነማን ናቸው? ይህንን ሚዲያዎች ለሕዝብ ማስገንዘብ አለባቸው ብለዋል።

ጥንቅሩ በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia