TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#Update የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባኤ  አቶ #ገዙ_አሰፋ ዞኑን በምክትል ዋና አስተዳዳሪነት እንደመሩ ሾሟል፡፡

©ena(ዲላ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH_ETH v2.apk
4.3 MB
TIKVAH-ETH የሞባይል መተግበሪያ!
#UpdateSport በአፍሪካ ከ23 ዓመት በታች ዋንጫ ማጣርያ ከሶማሊያ ጋር ጅቡቲ ላይ የመልስ ጨዋውን ያደረገው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ቡድን 1-0 ተሸንፏል፡፡ በዚህም በድምር ውጤት 4-1 አሸንፎ ወደ ሁለተኛው ዙር ማጣርያ ማለፍ ችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ቀጣይ ተጋጣሚ ማሊ ስትሆን በመጋቢት ወር ላይ የሚከናወን ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ ሶከር ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወላይታ ሶዶ🔝

ለዘመናት በአንድነትና በፍቅር የቆዩ በወላይታና ሲዳማ ብሔረሰቦች መካከል ተከስተው የነበረውን አለመግባባትን በማስወገድ በፍቅር፣ በይቅርታና በዕርቅ አንድነታቸውን ዳግም እንዲቀጥሉ የሚያስችል #የዕርቀ_ሰላም_ኮንፈረንስ በወላይታ ሶዶ ተካሂዷል፡፡

ኮንፈረንሱ ከቀናት በፊት በሲዳማ ዞን የተጀመረ ሲሆን በተቀመጠለት መርሃ ግብሩ መሠረት በወላይታ ሶዶም ከሁለቱም ብሔረሰብ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶችና ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተደርጓል፡፡

የወላይታ ዞን ተጠባባቂ አስተዳደር አቶ #ዳጋቶ_ኩምቤ በኮንፈራንሱ መክፈቻ እንደተናገሩት በወላይታና ሲዳማ ብሔረሰብ መካከል ያለው አንድነት ከብረት የተጠናከረ ነው፤ በመሆኑም ዛሬ በሚናደርገው መድረክ አንድነታቸውን እናስቀጥላለን እንጅ አንፈጥርም ብለዋል፡፡ ስለሆነም ተከስተው የነበረውን አለመግባባትን በማስወገድ፤ ያለፈውን በመተው ወደፊት በመጓዝ ሁላችንም በሁሉም ዘርፍ አስፈላጊ ለሆነው ሠላም ዘብ መቆም ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

የደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ ርዕሰ መስተዳደር አቶ #ሚሊዮን_ማትዎስ በኮንፈረንሱ ተገኝተው እንደተናገሩት ሁለቱም ብሔረሰቦች ሠላም ፈላጊ ናቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የህዛባችን ሠላም የሚያደፈርሱ የትኛውም ኃይል ለሠላም ጤንቅ ናቸውና ፈልፍለን እያወጣን ለሁለቱም ህዝቦች ጋራ ተጠቃሚነት፣ ለሠላምና ለዴሞክራሲ መስፈን እንሠራለን ብለዋል፡፡

የኢፌዴሪ ሠላም ሚኒስተር ወ/ሮ #ሙፈሪያት_ካሚል እንደተናገሩት ስለ ሠላም የሁለቱም ህዘቦችና ሽማግሌዎች ያዉቃሉ፤ ጥበብ ጥበበኞች ዘንድ ትገኛለች፤ ዕዉቀትም በአስተማር ዘንድ፡፡ በመሆኑም ዛሬ በሁለቱ ህዝቦች ሠላም ፍላጎት መሠረት የዕርቅ ማዕድ ተቋዳሽ ሆነናል፡፡ ለሁላችንም እንኳን ደስ አለን ብለው የወላይታና ሲዳማ አንድነት አይበጠስም፣ አይሰበርም ይልቁንስ ሊበጥስ የሚጥር ኃይል ይበጠሳል እንጅ በማለት አንድነት ይበልጥ ይጠናከራል ብለዋል፡፡

በፕሮግራሙ ገልለተኛ አካል የሆነ የዕርቅ ሽማግሌም ከሐምሌ 23/2010 ዓ.ም ጀምረው የተሠራውን የዕርቅ ሂደቱንና ከሁለቱም ህዝቦች በኩል የተነሱና በጋራ መስማማት የተዳረሱ ጉዳዮችን በሪፖርት መልክ አቅርበዋል፡፡ በተነሱ ሀሳቦችም ሁለቱም በኩል የተገኑ ሽማግሌዎች ይቀር መባባላቸውን ዕርቅና ፍቅር እናውርድ ብለው በመስማማታቸው መሠረት ዕርቁ ልፈፀም መቻሉንም አስረድተዋል፡፡

ሽማግሌዎችም ከሁሉ በላይ ከጌታ ጋር ያለንን አንድነታችን ስናጣክር ሌላው ሁሉ ይሆናል የመንግስት አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችን ወደ ፈጣር እንቅርብ ፣ ያለፈውን እንተው ወደ ፊት እንጓዝ በማለት መክረዋል፡፡

በመድረኩም ከሁሉም ቤተ ክርሲቲያን የተገኙ መሪዎችም የፀሎትና ቃል ስብከት ፕሮግራም አድርገዋል ይህም የወላይታና ሲዳማ የጥንት መሠረቱ ወንጌል ነው ሲሉም አሳስበዋል፡፡

በመጨረሻ ከሁለቱም ብሔረሰብ ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን የሰጡት ላለፈው ይቅር ተባብለዋል፡፡ በመሆኑ የባህላዊ ዕርቅ ሥርዓትም ተደርጓል፡፡

ምንጭ፦ የወላይታ ሶዶ ከተማ ባ/ቱ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትኩረት ለቴፒ‼️ትኩረት ለቴፒ‼️ትኩረት ለቴፒ‼️ትኩረት ለቴፒ‼️ትኩረት ለቴፒ‼️ትኩረት ለቴፒ‼️
ሰብዓዊነት⁉️

ለ30 ደቂቃ በየቤታችሁ ተወያዩ!!
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደግሞ በየዶርማችሁ!!

#ሰብዓዊነት ከምንም ነገር ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል። ሰው ሲሞት፣ ሲደበደብ፣ ሲጎዳ፣ ሲሰደድ ስናይ ልባችን ሊደማ የሚገባው የኛ ወገን እና ብሄር ተወላጅ ስለሆነ ብቻ መሆን የለበትም። የሰው #ስቃይ እና #መከራ እንደሰውነቱ ካልተሰማን በህይወት መኖራችን ትርጉም አልባ ነው። ሰው ሲኖር ነው ሀገር፣ ብሄር፣ ዘር፣ ክልል፣ ባንዲራ የሚኖረው። ሰው በሰውነቱ ብቻ የሚከበርባትን ታላቅ ሀገር ለመፍጠር እኛ አስተዋፅኦ እያደረግን ነው???

3 እና ከዚያ በላይ ሆናችሁ በያላችሁበት ተወያዩ!! ውይይታቹ ላይ የተነሱ ሀሳቦችን ላኩልኝ!!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለወጣቶች እና ተማሪዎች‼️

ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የጥፋት ሀይሎች መጠቀሚያ እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። በተለያዩ ምክንያቶች የትምህርት ተቋማት ውስጥ እጃቸውን ሰደው ሀገሪቷን ዳግም ውጥረት ውስጥ ለመክተት የሚሞክሩ ትንንሽ አሳዎች አሉ እነዚህም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚለዩ እምነታችን ነው።

ተማሪዎች እና ወጣቶች በሰከነ መንገድ ትምህርታችሁን ትከታተሉ ዘንድ መልዕክታችን እናቀርባለን።

አንዲት ድሀ እና የመጨረሻ ድሀ ሀገር ነው ያለችን የዚህችን ሀገር ታሪክ የምንቀይረው በረባው ባልረባው አዲስ ነገር እየፈጠርን አይደለም።

ሀገር ምትቀየረው በስራ እና በትምህርት ብቻ ነው። ዘላለም አመማችንን የአለም ማፈሪያ ሆነን እንዳንኖር ጠንክረን እንስራ።

የማንም የፖለቲካ ደላላ መጠቀሚያ እንዳትሆኑ! እነሱ ችግር ቢፈጠር ነገ #ፈርጥጠው የሚሄዱበትን መንገድ አመቻችተው ነው እናተን የሚቀሰቅሱት ስለሆነም እኚህን የጥፋት ሀይሎች ከመከተለ ተቆጠቡ።

መንግስት ትልልቆቹ አሳዎች እንደያዘው በየመንደሩ ያሉትን ትንንሽ አሳዎች አድኖ የመያዝ ስራ ላይ መበርታት አለበት።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
የድህነት ታሪካችንን በትምህርት እና በስራ እንቀይር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ዶክተር ደብረፅዮን🔝

ኢትዮጵያና ኤርትራ የሚያገናኙ የሑመራ - ኡምሓጀርና የራማ -ዓዲዃላ የመንገድ መስመሮች በቅርብ ግዜ #ተከፍተው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ለማጠናከር ውይይት አመራሮች እያካሄድን ነው አሉ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በትናንትናው ዕለት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ:በክልሉ ደቡባዊና ምዕራባዊ ዞኖች ስላካሄዱት ጉብኝት ማብራርያ ሰጥተዋል።

#በትግራይና #አማራ ክልሎች ግንኙነት ለማጠናከር የህዝብ ለህዝብና የአመራሮች ግንኙነት መፍጠር ስራ በአዋሳኝ አከባቢዎች እየተፈፀመ ነው ብለዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶክተር መረራ ጉዲና!!

በኢትዮጵያ የሚፈለገውን ብሄራዊ መግባባት ለማምጣት የታሪክ ሂሳብ ማወራረድ ውስጥ መግባት አያስፈልግም ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዶክተር #መረራ_ጉዲና ተናገሩ።

”በኢትዮጵያ ብሄራዊ መግባባትና ብሔራዊ እርቅ ለማምጣት ምን መደረግ አለበት?” በሚል ዙሪያ ከተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተውጣጡ የኀብረተሰብ ክፍሎች ትናንት ምሽት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ውይይት አካሂደዋል።

‘ኢምፓውር አፍሪካ’ በተሰኘ ተቋም አዘጋጅነት የተካሄደው ውይይት አዲሲቷን ኢትዮጵያ እንዴት እንፍጠር? መልካም አጋጣሚዎችና ፈተናዎች ምንድን ናቸው? በሚሉ ጉዳዮች ላይ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል።

ዶክተር መረራ ጉዲና ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ በአገሪቱ ብሄራዊ መግባባትን ለማምጣት በታሪክ የተፈጸሙ ድርጊቶችን ለማወራረድ መሞከር አያስፈልግም።

”ለዘመናት በኢትዮጵያ ሁሉም የሚስማማበት፣ የጋራና ሞዴል ሊሆን የሚችል መሪ አለመኖር ትልቅ ፈተና ሆኖ ቆይቷል” ብለዋል።

አጼ ምኒሊክ በተወሰኑ አካባቢዎች ዘላለማዊ ጀግና ተደረገው ይወሰዳሉ፤ በሌላ አካባቢ ደግሞ ቀኝ ገዥ ተደርገው መታየታቸውን በማሳያነት የጠቀሱት ምሁሩ ብሄራዊ እርቅ ለማምጣት ከዚህ ዓይነት አስተሳሰብ መላቀቅ እንደሚገባ አስረድተዋል።

ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በኢትዮጵያ የሀሳብ የበላይነት አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ ሁሉም የኀብረተሰብ ክፍል የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለበት ዶክተር መረራ ገልጸዋል።

”በአገሪቱ ታሪክ የነበሩ የሚጋጩ ህልሞችን ይዞ መኳተን የትም አያደርስም” ያሉት ዶክተር መረራ ህልሞቹ በአግባቡ ካልተያዙ ወደለየለት አለመረጋጋት የሚወሰዱ በመሆናቸው ሁሉም የሚጠበቅበትን የቤት ሥራ መስራት እንደሚገባው አመልክተዋል።

ፖለቲከኞች፣ የሐይማኖት መሪዎች፣ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች አዲሲቷን ኢትዮጵያን እንዴት እንፍጠር? የሚለውን በጥልቀት ሊሰሩበት ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።

”መግባባት በሚቻልበት ቋንቋ ምን ያስፈልጋል? የነገዋ ኢትዮጵያ ምን መምሰል አለባት?” በሚሉና መሰል ጉዳዮች ላይ በሰከነ አእምሮ መወያየት እንደሚያስፈልግ ነው ዶክተር መረራ በመነሻ የውይይት ሀሳባቸው አጽንኦት የሰጡት።

”ህዝብ የእኔ መንግሥት ነው” የሚል አስተሳሰብ አለማምጣቱ በአገሪቱ የሚታይ ትልቁ ፈተና መሆኑን የተናገሩት ዶክተር መረራ ”በቀጣይ ህዝቡ የኔ መንግሥት ነው” እንዲል የሚያስችሉ ሥራዎችን መሥራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከነበረው የኢትዮጵያ ታሪክ ለምን መማር አልቻልንም? እስከ መቼ ነው በትንንሽ ቁርሾዎች መቃቃሩ የሚቀጥለው? እውነተኛ ለውጥ እንዲመጣ በመሸነጋገል ላይ የተመሠረቱ ሥራዎች መቆም እንዳለባቸው ተናግረዋል።

አቶ ብርሃኑ አሰፋ በሰጡት አስተያየት ”የኔ ብቻ ልክ ነው ከኔ ውጭ ያለው አስተሳሰብ የተሳሳተ ነው” የሚለው አመለካከት ከየት መጣ የሚለውን ከመሰረቱ መለየት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

በተለይ ደግሞ እንደዚህ አይነት ልዩነቶች የሚጎሉት ተማሩ በሚባሉ ሰዎች ላይ ነው ትምህርቱስ ምኑ ላይ ነው? ሲሉም ይጠይቃሉ።

ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ታምራት ነገራ ደግሞ ”ጠላትነት ተቋማዊ መዋቅር እንዲይዝ ተደርጓል” የሚል ሀሳብ ያነሱ ሲሆን ይህም ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ሳንካ ሆኗል ብለዋል።

በውይይት ብቻ ብሔራዊ መግባባት ሊመጣ አይችልም ያሉት አቶ ታምራት በትምህርትና በሐይማኖት ተቋማት በኩል ስለ ብሔራዊ መግባባት በኀብረተሰቡ ዘንድ የማስረጽ ሥራ መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሌላዋ የውይይት ተሳታፊ ወይዘሮ መቅደስ አዳነ በበኩላቸው ብሔራዊ መግባባትን አደጋ ላይ የጣለው ዋናው ምክንያት የነበረው የጥላቻ ትርክት እንደሆነም አስረድተዋል።

ዶክተር መረራ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ ብሔራዊ መግባባት በተጨባጭ ለማምጣት የታሪክ ሂሳብ ማወራረድ ውስጥ መግባት እንደማያስፈልግ አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው የለውጥ እንቅስቃሴ ለብሔራዊ መግባባት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ያብራሩት ዶክተር መረራ የነገውን ፖለቲካ ለማስተካከል ሁሉም የቤት ሥራውን መሥራት እንዳለበት አስረድተዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መከላከያ ሰራዊት🔝ዘመናዊና ብቁ የሆነ ሰራዊት መገንባት የሚያስችለው #የሪፎርም ትግበራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢ/ ሹም ጄኔራል #ሰዓረ_መኮንን አስታወቁ፡፡

ምንጭ~etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፒያሳ🔝ሚድሮክ #ለዓመታት ከልሎ ያስቀመጣቸውን ቦታዎች አጥር በመፍረስ ላይ ይገኛል።

ፎቶ፦GH & DAWIT (TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia