TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#ጥብቅ ማሳሰቢያ⬇️

"...ከምንም በላይ የግልና የቡድን ጥቅሞቻችሁን #ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማስጠበቅ እየቻላችሁ በተለያዩ ወንጀሎችና ሰላምን የማደፍረስ #እኩይ ተግባራት ላይ ለመሰማራት #የምታስቡ አካላት ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እያሳሰብኩ በማንኛውም የህዝብን ፀጥታ #በሚያደፈርሱና ህዝብን ከህዝብ #በሚያጋጩ ህገወጥ ተግባራት ላይ ተሰማርቶ የተገኘ እንዲሁም ለእንደዚህ አይነት ህገወጥ ተግባራት በምንም መልኩ ትብብር ያደረገ አካል ላይ ህግን ተከትሎ አስፈላጊውን #እርምጃ ለመውሰድ መንግስት #ቁርጠኛ እንደሆነ በጥብቅ ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡"

◾️◾️ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ◾️◾️

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በድጋሚ...#ጥብቅ ማሳሰቢያ⬇️

"...ከምንም በላይ የግልና የቡድን ጥቅሞቻችሁን #ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማስጠበቅ እየቻላችሁ በተለያዩ ወንጀሎችና ሰላምን የማደፍረስ #እኩይ ተግባራት ላይ ለመሰማራት #የምታስቡ አካላት ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እያሳሰብኩ በማንኛውም የህዝብን ፀጥታ #በሚያደፈርሱና ህዝብን ከህዝብ #በሚያጋጩ ህገወጥ ተግባራት ላይ ተሰማርቶ የተገኘ እንዲሁም ለእንደዚህ አይነት ህገወጥ ተግባራት በምንም መልኩ ትብብር ያደረገ አካል ላይ ህግን ተከትሎ አስፈላጊውን #እርምጃ ለመውሰድ መንግስት #ቁርጠኛ እንደሆነ በጥብቅ ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡"

◾️◾️ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ◾️◾️

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬆️

በአዲስ አበባ #በካርቶን የታሸገ 3 ሚሊዮን 5 መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር እና 61400 የአሜሪካ #ዶላር በነሐሴ ወር 2010 ዓ/ም #መያዙን የከተማይቱ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የቻይና ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦች ከቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን በየቀኑ ማታ ማታ በካርቶን የታሸጉ ብሮች ያወጡ እንደነበር ከአስራ አምስት ቀን በላይ ከፈጀ #ጥብቅ ክትትል በኋላ ፖሊስ ደርሶበታል፡፡

ነሀሴ 28 ቀን 2010 ዓ/ም ምሽት ላይ መነሻዋን ከቦሌ ሻላ ያደረገች ፕራዶ መኪና ወደ ቦሌ ሩዋንዳ ታመራለች፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የክትትልና ኦፕሬሽን ክፍል አባላትም መኪናዋን በቅርብ ርቀት መከታተል ይጀምራሉ፡፡

ፕራዶዋ ቦሌ ሩዋንዳ ከአንድ ሰዋራ ቦታ ትደርስና ከአንዲት ነጭ ዶልፊን መኪና አጠገብ ትቆማለች፡፡

ከዚያም ከፕራዶዋ ውስጥ የነበሩት ተጠርጣሪዎች በካርቶን የታሸጉት የገንዘብ ኖቶችን ወደ ዶልፊነኗ ሲያዛውሩ በክትትል ቡድኑ በቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡

በዕለቱ በቁጥጥር ስር የዋሉት ቀደም ሲል የተጠቀሱትና የቻይና ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦችና አንድ ኢትዮጵያዊ ግብረአበራቸው በድምሩ 3 ተጠርጣሪዎች ናቸው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በወቅቱ ለክትትል ፖሊስ አባላቱ 2 ሁለት ሚሊየን ብር እንስጣችሁነና ልቀቁን ሲሉ ተማፅነዋቸዉ የነበረ ቢሆንም የፖሊስ አባላቱ ግን ቀጥታ ጉዳዩን ለኃላፊዎቻቸው በመንገር ከእነ ኤግዚቢቱ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ተነግሯል፡፡

©ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን‼️

ህግን በመተላለፍ የክልሉን ሰላምና ደህንነት በሚያደፈርሱ አካላት ላይ #እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል #ጥብቅ ትዕዛዝ ለሁሉም ዞኖች መተላለፉን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በምዕራባዊ የክልሉ አካባቢዎች ያጋጠመውን የፀጥታ ችግር በውይይትና በትዕግስት ለመፍታት ሞክሬያለሁ ያለው ኮሚሽኑ እስከ ህይወት መስዋዕትነት የደረሰ ዋጋ አስከፍሎኛል ሲልም ገልጿል።

ትዕግስቱ የበዛ ነበር ያሉት ኮሚሽነር አለማየሁ እጅጉ በቄለም ወለጋ የተገደሉትን 2 የዞን ፖሊስ አመራሮችን ጨምሮ የ12 ፖሊስ አባላት ህይወት ማለፉንና 77 ፖሊሶች መቁሰላቸውን ተናግረዋል።

ኮሚሽነሩ አያይዘውም የሚሊሻ አባላትን ጨምሮ በ40 የፀጥታ አካላት ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል ያሉ ሲሆን፣ የ29 ነዋሪዎች ህይወት ማለፉን ገልፀዋል።

በቄለም ወለጋ፣ በምስራቅና በምዕራብ ወለጋ እንዲሁም በሆሮጉዱሩ አካባቢዎች የመንግስት መዋቅር ስራ መስራት ካለመቻልም በላይ እንዲፈርስ ተደርጓል ያሉት ኮሚሽነሩ በቄለም እና በምዕራብ ወለጋ አካባቢዎች የመንግስት ንብረት በኦነግ ታጣቂዎች መዘረፉን አስታውቀዋል።

በአካባቢው የሚደርሰው ጉዳት ከዚህም በላይ ነው ያሉ ሲሆን የግለሰቦችን ሳይጨምር ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ከባንክ መዘረፉን ገልፀዋል።

ታጣቂዎቹ በአካባቢው ካለ ፖሊስ ጣቢያ 2072 ክላሺንኮቭ ጦር መሳሪያ መዝረፋቸውም ነው የተገለፀው።

ትዕግስቱ ከአንድ ወገን መሆኑ ዋጋ አስከፍሎኛል ያለው ፖሊስ ኮሚሽኑ ህግን የሚያውኩ አካላትን ለህግ የማቅረብ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥሏል ብሏል። ለዚህም ለሁሉም ዞኖች ጥብቅ መመሪያ ተላልፏል ያለ ሲሆን የህዝቡ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ‼️

ጥር 17 አፄ #ቴዎድሮስ_ግቢ በ6 የተማሪ መኖሪያ ህንፃዎች በተደረገ #ድንገተኛ ፍተሻ፦

•395 ያልታደሰ፣ ሃሰተኛ እና ፎቶ የሌለው መታወቂያ ተይዟል።

•ከተማሪ መኖሪያ ክፍሎች ጩቤ፣ ድንጋይ፣ ብረት እና ዱላ ተገኝቷል።

•አንድ ተማሪ 9 ሲም ካርድ፤ ሌላ አንድ ተማሪ 7 ሲም ካርድ ይዘው ተገኝተዋል።

•8 ተማሪዎች አካውንት ላይ እያንዳንዳቸው ከ30 ሺ ብር እስከ 86 ሺ ብር ተገኝቷል።

•መታወቂያ ያልያዙ 37 ተማሪዎች ተይዘዋል።

•በቀን ጥር 16/2011 ዓ.ም. 3 ተማሪዎች 4 ጀሪካን ዘይት ጫካ ውስጥ ይዘው እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል፤ 3 ተማሪዎች ሴቶች ህንፃ ሲገቡ ተይዘዋል።

🔹ተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢው ማጣራት እየተደረገ ይገኛል፤ በቅርቡ #እርምጃ ተወስዶ #ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
.
.
ትምህርት የተቋረጠባቸው አፄ ቴዎድሮስ እና አፄ ፋሲል ግቢዎች ከሰኞ ጥር 20 ጀምሮ ተማሪዎች ትምህርት እንዲጀምሩ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። ትምህርት የማይጀምሩ ተማሪዎች ግቢውን #ለቀው እንዲወጡ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ተላልፏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥብቅ ማሳሰቢያ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር #በነገው ዕለት ምንም ዓይነት የሠላማዊ ሰልፍ ሆነ ስብሰባ እናድርግ የሚል #ጥያቄ አልቀረበለትም።

በመሆኑን በማህበራዊ ሚዲያ ተጠራ የተባለው ሰልፍ በከተማ አስተዳደሩ ይሁን በፖሊስ ኮሚሽኑ እውቅና የሌለው ነው።

ስለሆነም #ሰልፍ_እንወጣለን በሚል በህብረተሰቡ ላይ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት ከተግባራቸው እንዲታቀቡ ኮሚሽኑ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ይህን ተላልፎ በሚገኙ አካላት ላይም የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አስፈላጊውን ህጋዊ #እርምጃ_የሚወስድ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በርካቶች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው...

ፖሊስ በአዲስ አበባ በርካታ ሰዎችን በቁጥጥር እያዋለ መሆኑን DW የከተማይቱን ነዋሪዎች ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ/አብንና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትህ ፓርቲ/አዜማ አባላት እንደታሰሩም ተጠቁሟል፡፡ ጸጥታ ሃይሎች በከተማዋ #ጥብቅ ቁጥጥር እያደረጉ እንደሆነ የዐይን እማኞች ገልጸዋል፡፡

Via #dw/#wazema
🗞ሰኔ 20/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ATTENTION

በኳታር ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን!

(የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ዶሃ)

- በኳታር የፊት መሸፈኛ መጠቀም አስገዳጅ ህግ ሆኗል።

- የአገሪቱ የሚኒስትሮች ም/ቤት ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ማንኛውም ሰው በተለያየ ምክንያት ከመኖሪያ ቤቱ ሲወጣ የፊት መሸፈኛ መጠቀም ይኖርበታል።

- ውሳኔው ከፊታችን እሁድ ግንቦት 09 ቀን 2012 ዓ.ም /Sunday May 17/2020/ ጀምሮ የጸና ይሆናል።

- ህጉ ብቻውን ሆኖ መኪና የሚያሽከረክር ግለሰብን አይመለከትም።

- ህጉን ተላልፎ የሚገኝ ግለሰብ እስከ ሶስት ዓመት እስር ወይም እስከ 200,000 የኳታር ሪያል ይቀጣል።

በኳታር የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን የሀገሪቱ መንግስት የሚያወጣቸውን ህጎች በአግባቡ በመተግበር ራሳችሁንና ቤተሰባችሁን ከበሽታው እንድትጠብቁ ብሎም ከህግ ተጠያቂነት ነጻ እንድትሆኑ #ጥብቅ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ጥብቅ_ማሳሰቢያ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሀገሪቱ አሁን ባለችበት የፀጥታ ሁኔታ በምንም አይነት ምክንያት "ርችት መተኮስ" የተከለከለ መሆኑን በጥብቅ አሳስቧል።

ይህን መልዕክት በመተላለፍ ርችት ሲተኩስ የተገኘ ግለሰብ በህግ የሚጠየቅ መሆኑን አስታውቋል።

@tikvahethhiopiaBot @tikvahethiopia
#ጥብቅ_ማሳሰቢያ

በመስቀል በዓልም ሆነ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ርችት መተኮስ በጥብቅ መከልከሉን የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም ፖሊስ ያስተላለፈውን መልዕክት በመተላለፍ ርችት የተኮሱ ግለሰቦች ተይዘው በፍርድ ቤት በዋስ መለቀቃቸውን ፖሊስ ገልጿል፡፡

ጳጉሜ 5/2013 ዓ/ም ለመስከረም 1/2014 ዓ.ም አጥቢያ ከሌሊቱ 11 ሰዓት በአዲስ ከተማ ክ/ ከተማ ልዩ ቦታው ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ሦስት ግለሰቦች የ2014 አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ርችት ሲተኩሱ ተይዘው ምርመራ ተጣርቶባቸው እያንዳንዳቸው በ4ሺ ብር ዋስ ተለቀው ጉዳይቸው በፍርድ ቤት በመታየት ላይ የሚገኝ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውሷል፡፡

በተመሳሳይ በቦሌ ፣ በቂርቆስ እና በየካ ክፍለ ከተሞች ርችት ሲተኩሱ የተገኙ ግለሰቦች ጉዳይም በምርመራ ሂደት ላይ እንደሚኝም ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል፡፡

በበዓላት ወቅት የሚተኮሱ ርችቶችን ሽፋን በማድረግ ሰላምን የማደፍረስ ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች የሚፈነዱና ተቀጣጣይ ነገሮችን ሊጠቀሙ ስለሚችሉ ይህ ደግሞ የፀጥታ ስጋቶችን እንደሚፈጥሩ ፖሊስ አስገንዝቧል።

ፖሊስ የህገ-ወጦቹን ድርጊት ለመከላከል እንዲቻል መስከረም 16 ቀን 2014 ዓ/ም በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓልም ሆነ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ማንኛውም ግለሰብም ሆነ ተቋም ከሚመለከተው አካል ፍቃድ ሳያገኝ ርችቶችን መተኮስ እንደማይችል ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ዛሬ ህዳር 3/2016 ዓ.ም በመቐለ የተካሄደው የታክሲ አገልግሎት የማቆም አድማ ከማህበራቱ እውቅና ውጪ የተፈፀመና ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን ሶስት የታክሲ ማህበራት ባወጡት መግለጫ አሳወቁ። ማህበራቱ ከሰዓት በኃላ ባሰራጩት ይፋዊ መግለጫ ፤ " ለመንግስት ያቀረብነው ጥያቄ በህጋዊ መንገድ እንዲመለስ ጥረት እያካሄድን ባለንበት ጊዜ አገልግሎት ማቋረጥ አግባብ አይደለም " ብለዋል። አድማ…
#Update

" የምንሰጠውን ምክርና ማሳሰብያ ችላ ብሎ በአድማው የሚቀጥል ባለንብረትና አሽከርካሪ ላይ #ጥብቅ_እርምጃ ይወሰዳል " - ወ/ሪት ራሄል ሃይለ

የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ በመቐለ የተደረገው የታክሲ አገልግሎት ማቋረጥና አድማ " ህጋዊ አይደለም " ብሏል።

ቢሮው ከመቐለ የትራንስፓርት ፅህፈት ቤትና ፓሊስ በጋራ ' አካሄድኩት ' ባለው ግምገማ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች ቀድም ሲል አገልግሎት ለማቋረጥና አድማ ለመምታት የሚያበቃ ቅሬታና ጥያቄ አላቀረቡም ሲል ገልጿል።

የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወ/ሪት ራሄል ሃይለ ህዳር 3/2016 ዓ.ም አመሻሽ ለሚድያ በሰጡት መግለጫ ፤ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች አገልግሎት የማቋረጥና አድማ የመምታት ደርጊቱ ችላ ተብሎ የማይታለፍ ህጋዊ እርምጃና ተጠያቂነት የሚያስከትል በመሆኑ በመገንዘብ ስራቸው ይቀጥሉ ዘንድ መክረዋል።

የመንግስት ምክርና ማሳሰብያ ችላ ብሎ በአድማ የሚቀጥል ባለንብረትና አሽከርካሪ ግን ጥብቅ እርምጃ ይወሰድበታል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ለምለም ኪሓ ፣ ህዳሴና ሓወልቲ የተባሉ የመቐለ የታክሲ ማህበራት አመራሮች በማህተም አስደግፈው ህዳር 3/2016 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ለሚድያዎች በላኩት መግለጫ ፤ አግልግሎት ማቋረጡና አድማው ከእውቅናቸው ወጪ የተደረገ ኢ-ህጋዊ ነው ማለታቸው መዘገባችን ይታወሳል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

በመቐለ ከተማ የታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ባደረጉት አድማ ነዋሪዎች ለእንግልት እና አላግባብ ለሆነ ወጭ ተዳርገዋል።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ ያነጋገራቸው የታክሲ ባለንብረቶች እና አሽከርካሪዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ በመሄድ ላይ የሚገኘው የኑሮ ሁኔታ ፣ የመኪና እቃ መለዋወጫ መወደድ የሹፌርና የረዳት ክፍያ ገበያ ላይ ባለው ታሪፍ መሸፈን እጅግ እንደከበዳቸው ፤ ያለው ታሪፍ እንዲስተካከል ከአንድ ወር በፊት መንግሥትን በማህበራቸው በኩል ቢጠይቁም ምላሽ ስላላገኙ ወደ አድማ እንደገቡ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia