እቅበተ ተዋሕዶ
Photo
✍️የቤተ ክህነቱን የስፍና ዕዳ፣ ጭምር የተሸከመው ማኅበር✍️
+++
በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የጥቂት ግለሰቦችን ፍላጎት መሠረት አድርገው የተሰባሰቡ እልፍ አእላፍ ስብስቦች (ማኅበራት) አሉ። ከጥቂቶች በቀር አብዛኛዎቹ ግብና ሥልታዊ ትኩረት የሌላቸው በሥጋዊ መሻት ብቻ የሚናውዙ ናቸው። ቤተ ክህነቱም ለአገልግሎት ሳይሆን ቤተ ክርስቲያንን ለማቆርቆዝ የተመሠረተ #ጋግሪን ተቋም ከሆነ 50 ዓመታት ተቆጥረዋል። (ቤተ ክህነትና ቤተ ክርስቲያን ልዩነታቸውን ልብ ይሏል) ። ባለፈው የቤተ ክህነት ልኬተ ዘመነ ውስጥ ግን እነ ፓትርያርክ አቡነ ቴዎፍሎስን የመሰሉ የንሥር ዓይን የተላበሱ አባቶችም አልፈውበት ነበር፣የዛሬውን አያድርገውና።
በ1980 ዎቹ እንደ ጠዋት ፀሐይ ቦግ ብለው ያጣናቸው አቡነ ጎርጎዮስ ካልዕን ስናስብ ልባችን ይደማል። ይሁን እንጂ እንደ ልቦናቸው መሻት እሳቸው ባሰቡት ልክና መጠን ባይደርስም ዛሬ ላይ ከፈጣሪ ቀጥለን የምንመካበት #ማኅበረ ቅዱሳን የሚባልን የአገልግሎት ተቋም በወኔ ለኩሰውልን አልፈዋል። በብጹዕነታቸው ዘመን የነበሩ እንደሚናገሩት አማናዊውን አገልግሎት "እኔ ለኩሸዋለው እናንተ አንድዱት" ይሉ ነበር ይባላል፣ አቡነ ጎርጎርዮስ ።
በአጭሩ በዚህ ዘመን ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ቤተ ክህነቱ ሊሠራው የነበረውን አልፎም ራሱ ቤተ ክህነቱ የፈጠረውን እልቆቢስ ችግር ለመፍታት #መከራውን የሚያይ ማኅበር ነው። ማኅበሩን ቤተ ክህነቱ እንኳንስ ሊያግዘው፣ በታላቅ ትግስት ሁሉን ችሎ፣ የቤተ ክህነቱን ስንፍና ጭምር ተሸክሞ ቤተ ክርስቲያኒቱን በዓለም አደባባይ ከሐፍረት ሰውሮ ከአቅሙ በላይ እየደከመ በመላው ዓለም አገልግሎት እየሰጠ ያለ ብቸኛ ተቋም ነው።
በስብከተ ወንጌል፣ በማኅበራዊ አገልግሎት፣ በዕቅበተ እምነት፣ በገዳማት አገልግሎት በጥናትና ምርምር እና በሌሎችም ዘርፎች ያለውን ስር የሰደደ ክፍተት ለመሙላት ባለፉት 32 ዓመታት ዕረፍት አልባ ትግል እያደረገ እዚህ ደርሷል።
ቤተ ክህነቱ ግን በማይድን ዘውገኝነትና በሙስና እጅ ከወርች ታስሮ ይማቅቃል። የምእመናን የሐዘንና የመከራ ምንጭም ሆኖ ቀጥሏል፣ ቤተ ክህነቱ። ማኅበረ ቅዱሳን ግን ዛሬም ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ከአቅሙ በላይ እየሰራ ቀጥሏል። ምእመናን ከመቼው ጊዜ በላይ ማኅበሩን በቻልነው አቅም ሁሉ ልናግዝ ይገባል። የዓይናችን ማረፊያ ብቸኛ ተቋም ነውና።
+++
በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የጥቂት ግለሰቦችን ፍላጎት መሠረት አድርገው የተሰባሰቡ እልፍ አእላፍ ስብስቦች (ማኅበራት) አሉ። ከጥቂቶች በቀር አብዛኛዎቹ ግብና ሥልታዊ ትኩረት የሌላቸው በሥጋዊ መሻት ብቻ የሚናውዙ ናቸው። ቤተ ክህነቱም ለአገልግሎት ሳይሆን ቤተ ክርስቲያንን ለማቆርቆዝ የተመሠረተ #ጋግሪን ተቋም ከሆነ 50 ዓመታት ተቆጥረዋል። (ቤተ ክህነትና ቤተ ክርስቲያን ልዩነታቸውን ልብ ይሏል) ። ባለፈው የቤተ ክህነት ልኬተ ዘመነ ውስጥ ግን እነ ፓትርያርክ አቡነ ቴዎፍሎስን የመሰሉ የንሥር ዓይን የተላበሱ አባቶችም አልፈውበት ነበር፣የዛሬውን አያድርገውና።
በ1980 ዎቹ እንደ ጠዋት ፀሐይ ቦግ ብለው ያጣናቸው አቡነ ጎርጎዮስ ካልዕን ስናስብ ልባችን ይደማል። ይሁን እንጂ እንደ ልቦናቸው መሻት እሳቸው ባሰቡት ልክና መጠን ባይደርስም ዛሬ ላይ ከፈጣሪ ቀጥለን የምንመካበት #ማኅበረ ቅዱሳን የሚባልን የአገልግሎት ተቋም በወኔ ለኩሰውልን አልፈዋል። በብጹዕነታቸው ዘመን የነበሩ እንደሚናገሩት አማናዊውን አገልግሎት "እኔ ለኩሸዋለው እናንተ አንድዱት" ይሉ ነበር ይባላል፣ አቡነ ጎርጎርዮስ ።
በአጭሩ በዚህ ዘመን ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ቤተ ክህነቱ ሊሠራው የነበረውን አልፎም ራሱ ቤተ ክህነቱ የፈጠረውን እልቆቢስ ችግር ለመፍታት #መከራውን የሚያይ ማኅበር ነው። ማኅበሩን ቤተ ክህነቱ እንኳንስ ሊያግዘው፣ በታላቅ ትግስት ሁሉን ችሎ፣ የቤተ ክህነቱን ስንፍና ጭምር ተሸክሞ ቤተ ክርስቲያኒቱን በዓለም አደባባይ ከሐፍረት ሰውሮ ከአቅሙ በላይ እየደከመ በመላው ዓለም አገልግሎት እየሰጠ ያለ ብቸኛ ተቋም ነው።
በስብከተ ወንጌል፣ በማኅበራዊ አገልግሎት፣ በዕቅበተ እምነት፣ በገዳማት አገልግሎት በጥናትና ምርምር እና በሌሎችም ዘርፎች ያለውን ስር የሰደደ ክፍተት ለመሙላት ባለፉት 32 ዓመታት ዕረፍት አልባ ትግል እያደረገ እዚህ ደርሷል።
ቤተ ክህነቱ ግን በማይድን ዘውገኝነትና በሙስና እጅ ከወርች ታስሮ ይማቅቃል። የምእመናን የሐዘንና የመከራ ምንጭም ሆኖ ቀጥሏል፣ ቤተ ክህነቱ። ማኅበረ ቅዱሳን ግን ዛሬም ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ከአቅሙ በላይ እየሰራ ቀጥሏል። ምእመናን ከመቼው ጊዜ በላይ ማኅበሩን በቻልነው አቅም ሁሉ ልናግዝ ይገባል። የዓይናችን ማረፊያ ብቸኛ ተቋም ነውና።
September 10, 2024