ሲፋን ሀሰን በአራት ርቀቶች ልትወዳደር ነው !
ለኔዘርላንድ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን በቀጣዩ የፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር በአራት ርቀቶች ልትወዳደር መሆኑን የሀገሪቱ ፌዴሬሽን አረጋግጧል።
አትሌቷ በፓሪስ ኦሎምፒክ በ10000 ፣ 5000 ፣ 1500 ሜትር እና ማራቶን ውድድሮች እንደምትሳተፍ ተገልጿል።
የ 31ዓመቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን በሁሉም ውድድሮች ፍፃሜ የምትደርስ ከሆነ በድምሩ በዘጠኝ ቀናት ውስጥ 65.5 ኪሎ ሜትር ያህል መሮጥ የሚጠበቅባት ይሆናል።
አትሌት ሲፋን ሀሰን በቶኪዮ ኦሎምፒክ ውድድር በሶስት ርቀቶች መሳተፏ የሚታወስ ሲሆን ሁለት የወርቅ እና አንድ የነሀስ ሜዳልያ ማስመዝገቧ አይዘነጋም።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ለኔዘርላንድ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን በቀጣዩ የፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር በአራት ርቀቶች ልትወዳደር መሆኑን የሀገሪቱ ፌዴሬሽን አረጋግጧል።
አትሌቷ በፓሪስ ኦሎምፒክ በ10000 ፣ 5000 ፣ 1500 ሜትር እና ማራቶን ውድድሮች እንደምትሳተፍ ተገልጿል።
የ 31ዓመቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን በሁሉም ውድድሮች ፍፃሜ የምትደርስ ከሆነ በድምሩ በዘጠኝ ቀናት ውስጥ 65.5 ኪሎ ሜትር ያህል መሮጥ የሚጠበቅባት ይሆናል።
አትሌት ሲፋን ሀሰን በቶኪዮ ኦሎምፒክ ውድድር በሶስት ርቀቶች መሳተፏ የሚታወስ ሲሆን ሁለት የወርቅ እና አንድ የነሀስ ሜዳልያ ማስመዝገቧ አይዘነጋም።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
የባየር ሙኒክ ጥያቄው ተቀባይነት አገኘ ! የጀርመን ቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሙኒክ የፉልሀሙን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጇ ፓልሂንሀ ለማስፈረም ከክለቡ ጋር ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። ከተጨዋቹ ጋር ቀደም ብለው በግል ከስምምነት የደረሱት ባየር ሙኒኮች አሁን ላይ ለፉልሀም ያቀረቡት 56 ሚልዮን ዩሮ የሚደረሰስ ሒሳብ ተቀባይነት ማግኘቱ ተገልጿል። ፉልሀም ከተጨዋቹ ዝውውር የሚያገኙት 51 ሚልዮን…
ባየር ሙኒክ በይፋ ተጨዋች አስፈረሙ !
የጀርመን ቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሙኒክ የፉልሀሙን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጇ ፓልሂንሀን ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።
ፖርቹጋላዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጇ ፓልሂንሀ በባየር ሙኒክ ቤት እስከ 2028 የሚያቆየውን የአራት አመት ኮንትራት መፈረሙ ይፋ ተደርጓል።
ፉልሀም ከተጨዋቹ ዝውውር 50 ሚልዮን ዩሮ ቋሚ ክፍያ እና ተጨማሪ ታይት የሚከፈል ክፍያ እንደሚቀበሉ ተነግሯል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የጀርመን ቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሙኒክ የፉልሀሙን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጇ ፓልሂንሀን ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።
ፖርቹጋላዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጇ ፓልሂንሀ በባየር ሙኒክ ቤት እስከ 2028 የሚያቆየውን የአራት አመት ኮንትራት መፈረሙ ይፋ ተደርጓል።
ፉልሀም ከተጨዋቹ ዝውውር 50 ሚልዮን ዩሮ ቋሚ ክፍያ እና ተጨማሪ ታይት የሚከፈል ክፍያ እንደሚቀበሉ ተነግሯል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የዩራጓይ ተጨዋቾች ከደጋፊዎች ጋር ለምን ተጋጩ ?
በትላንት ምሽቱ የኮሎምቢያ እና ዩራጓይ ኮፓ አሜሪካ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዳርዊን ኑኔዝ እና ሌሎች የዩራጓይ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች ከኮሎምቢያ ደጋፊዎች ጋር ፀብ ውስጥ ገብተው ነበር።
ዩራጓይ ሽንፈት ካስተናገደችበት ጨዋታ በኋላ ዳርዊን ኑኔዝ እና የቡድን አጋሮቹ ወደ ተመልካች መቀመጫ ወንበሮች በማምራት ከደጋፊዎች ጋር ሲደባደቡ ተስተውለዋል።
ተጨዋቾቹ ይህንን ያደረጉት የኮሎምቢያ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች የዩራጓይ ተጨዋቾች ቤተሰቦች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
የዩራጓይ አምበል ጆዜ ሂሚኔዝ በሰጠው አስተያየትም " የተፈጠረው አደገኛ ነበር ምንም ፖሊስ አልነበረም እኛም ቤተሰቦቻችንን መጠበቅ ነበረብን " ሲል ሁኔታውን አስረድቷል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
በትላንት ምሽቱ የኮሎምቢያ እና ዩራጓይ ኮፓ አሜሪካ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዳርዊን ኑኔዝ እና ሌሎች የዩራጓይ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች ከኮሎምቢያ ደጋፊዎች ጋር ፀብ ውስጥ ገብተው ነበር።
ዩራጓይ ሽንፈት ካስተናገደችበት ጨዋታ በኋላ ዳርዊን ኑኔዝ እና የቡድን አጋሮቹ ወደ ተመልካች መቀመጫ ወንበሮች በማምራት ከደጋፊዎች ጋር ሲደባደቡ ተስተውለዋል።
ተጨዋቾቹ ይህንን ያደረጉት የኮሎምቢያ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች የዩራጓይ ተጨዋቾች ቤተሰቦች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
የዩራጓይ አምበል ጆዜ ሂሚኔዝ በሰጠው አስተያየትም " የተፈጠረው አደገኛ ነበር ምንም ፖሊስ አልነበረም እኛም ቤተሰቦቻችንን መጠበቅ ነበረብን " ሲል ሁኔታውን አስረድቷል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜን ማን ይመራዋል ?
የፊታችን እሁድ በስፔን እና እንግሊዝ መካከል የሚደረገውን የአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ የሚመሩት ዳኛ ታውቀዋል።
በግዙፉ ኦሎምፒያስታድዮን ስታዲየም የሚደረገውን ተጠባቂ የፍፃሜ ጨዋታ ፈረንሳዊው ዳኛ ፍራንኮይስ ሌቴዤር በመሀል ዳኝነት እንደሚመሩት ይፋ ተደርጓል።
ጨዋታውን ማን ያሸንፋል❓
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የፊታችን እሁድ በስፔን እና እንግሊዝ መካከል የሚደረገውን የአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ የሚመሩት ዳኛ ታውቀዋል።
በግዙፉ ኦሎምፒያስታድዮን ስታዲየም የሚደረገውን ተጠባቂ የፍፃሜ ጨዋታ ፈረንሳዊው ዳኛ ፍራንኮይስ ሌቴዤር በመሀል ዳኝነት እንደሚመሩት ይፋ ተደርጓል።
ጨዋታውን ማን ያሸንፋል❓
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ምባፔ የዘጠኝ ቁጥር ማልያ ይለብሳል ! ሪያል ማድሪዶች ለሚቀጥለው የውድድር ዘመን ለስድስት ተጨዋቾች አዲስ ቁጥር ማልያ አስተዋውቀዋል። ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ የዘጠኝ ቁጥር ማልያ እንደሚለብስ ሲገለፅ ከነገ ጀምሮ በማድሪድ የሽያጭ ሱቅ በገበያ ላይ ይቀርባልም ተብሏል። በተጨማሪም በሚቀጥለው አመት :- ካማቪንጋ 6 ቁጥር ፣ ቫልቬርዴ 8 ቁጥር ፣ ቹዋሜኒ 14 ቁጥር ፣…
የምባፔ ማልያ ከፍተኛ ፈላጊዎች ማግኘቱ ተገለጸ !
በቅርቡ ሪያል ማድሪድን የተቀላቀለው ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ማልያዎች በክለቡ የሽያጭ ሱቅ ከፍተኛ ፈላጊዎች ማግኘቱ ተገልጿል
የማልያው ፈላጊዎች ቁጥር ከተጠበቀው በላይ በመሆኑ ምክንያት ማልያውን ለመረከብ ከአራት እስከ ስድስት ሳምንታት ሊወስድ እንደሚችል ሪያል ማድሪድ አሳውቋል።
በዚህም ምክንያት ዛሬ ማልያውን የሚያዙ የሪያል ማድሪድ ደጋፊዎች እስከ ላሊጋው የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ድረስ እንደማይቀበሉ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
በቅርቡ ሪያል ማድሪድን የተቀላቀለው ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ማልያዎች በክለቡ የሽያጭ ሱቅ ከፍተኛ ፈላጊዎች ማግኘቱ ተገልጿል
የማልያው ፈላጊዎች ቁጥር ከተጠበቀው በላይ በመሆኑ ምክንያት ማልያውን ለመረከብ ከአራት እስከ ስድስት ሳምንታት ሊወስድ እንደሚችል ሪያል ማድሪድ አሳውቋል።
በዚህም ምክንያት ዛሬ ማልያውን የሚያዙ የሪያል ማድሪድ ደጋፊዎች እስከ ላሊጋው የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር ድረስ እንደማይቀበሉ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
📢 ከ #ዋናው በቴሌግራም የስፖርት አልባሳትን እንዴት ያዛሉ?
👉🏾 በቴሌግራም ሊንክ @Wanawsales በመጠቀም የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ይዘዙን።
🏅 ዋናው ወደፊት...
@wanawsportwear
👉🏾 በቴሌግራም ሊንክ @Wanawsales በመጠቀም የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ይዘዙን።
🏅 ዋናው ወደፊት...
@wanawsportwear
ቡናማዎቹ ተጋጣሚያቸውን አውቀዋል !
ሀገራችን ኢትዮጵያን በመወከል በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውድድር የሚሳተፈው ኢትዮጵያ ቡና የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚውን አውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና የመጀመሪያ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ከኬንያው ኬንያ ፖሊስ እግርኳስ ክለብ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።
ቡናማዎቹ ይህንን ጨዋታ ካሸነፉ በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ ጨዋታ ከግብፁ ክለብ ዛማሊክ ጋር የሚገናኙ ይሆናል።
ጨዋታዎቹ መቼ ይደረጋሉ ?
የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች :- የመጀመሪያው ጨዋታ ከነሀሴ 10-12/2016 ዓ.ም እንዲሁም የመልስ ጨዋታ ከነሀሴ 17-19/2016 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች ይደረጋሉ።
ሁለተኛ ዙር :- የመጀመርያ ጨዋታዎች ከመስከረም 3-5/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንዲሁም የመልስ ጨዋታ ከመስከረም 10-12/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንደሚደረጉ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ሀገራችን ኢትዮጵያን በመወከል በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውድድር የሚሳተፈው ኢትዮጵያ ቡና የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚውን አውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና የመጀመሪያ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ከኬንያው ኬንያ ፖሊስ እግርኳስ ክለብ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።
ቡናማዎቹ ይህንን ጨዋታ ካሸነፉ በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ ጨዋታ ከግብፁ ክለብ ዛማሊክ ጋር የሚገናኙ ይሆናል።
ጨዋታዎቹ መቼ ይደረጋሉ ?
የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች :- የመጀመሪያው ጨዋታ ከነሀሴ 10-12/2016 ዓ.ም እንዲሁም የመልስ ጨዋታ ከነሀሴ 17-19/2016 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች ይደረጋሉ።
ሁለተኛ ዙር :- የመጀመርያ ጨዋታዎች ከመስከረም 3-5/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንዲሁም የመልስ ጨዋታ ከመስከረም 10-12/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንደሚደረጉ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ንግድ ባንኮች ተጋጣሚያቸውን አውቀዋል !
ሀገራችን ኢትዮጵያን በመወከል በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር የሚሳተፈው የሊጉ ሻምፒዮን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚውን አውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመጀመሪያ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ከዩጋንዳው ቪላ ጆጎ ክለብ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።
ንግድ ባንክ ይህንን ጨዋታ ካሸነፉ በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ ጨዋታ የታንዛኒያው ያንግ አፍሪካ እና የቡሩንዲውን ቪታሎ እግርኳስ ክለብ አሸናፊን የሚያገኙ ይሆናል።
ጨዋታዎቹ መቼ ይደረጋሉ ?
የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች :- የመጀመሪያው ጨዋታ ከነሀሴ 10-12/2016 ዓ.ም እንዲሁም የመልስ ጨዋታዎች ከነሀሴ 17-19/2016 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች ይደረጋሉ።
ሁለተኛ ዙር :- የመጀመርያ ጨዋታዎች ከመስከረም 3-5/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንዲሁም የመልስ ጨዋታዎች ከመስከረም 10-12/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንደሚደረጉ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ሀገራችን ኢትዮጵያን በመወከል በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር የሚሳተፈው የሊጉ ሻምፒዮን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚውን አውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመጀመሪያ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ከዩጋንዳው ቪላ ጆጎ ክለብ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።
ንግድ ባንክ ይህንን ጨዋታ ካሸነፉ በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ ጨዋታ የታንዛኒያው ያንግ አፍሪካ እና የቡሩንዲውን ቪታሎ እግርኳስ ክለብ አሸናፊን የሚያገኙ ይሆናል።
ጨዋታዎቹ መቼ ይደረጋሉ ?
የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች :- የመጀመሪያው ጨዋታ ከነሀሴ 10-12/2016 ዓ.ም እንዲሁም የመልስ ጨዋታዎች ከነሀሴ 17-19/2016 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች ይደረጋሉ።
ሁለተኛ ዙር :- የመጀመርያ ጨዋታዎች ከመስከረም 3-5/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንዲሁም የመልስ ጨዋታዎች ከመስከረም 10-12/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች እንደሚደረጉ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ዩናይትድ ዝውውሮቹን በፍጥነት ማጠናቀቅ ይፈልጋሉ !
በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት ማንችስተር ዩናይትዶች የማትያስ ዴሊትን እና ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል።
ማንችስተር ዩናይትድ አሁን ላይ ከባየር ሙኒክ ጋር በማትያስ ዴሊት የዝውውር ሒሳብ ዙሪያ ለስምምነት መቃረባቸው ተነግሯል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር ለማጠናቀቅ የተወሰኑ ስራዎች እንደሚቀሯቸው ተነግሯል።
ተጨዋቹ የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ወደ ማንችስተር ለመጓዝ በዝግጅት ላይ መሆኑ ሲገለፅ በሚቀጥሉት ቀናት ዝውውሩ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት ማንችስተር ዩናይትዶች የማትያስ ዴሊትን እና ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል።
ማንችስተር ዩናይትድ አሁን ላይ ከባየር ሙኒክ ጋር በማትያስ ዴሊት የዝውውር ሒሳብ ዙሪያ ለስምምነት መቃረባቸው ተነግሯል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር ለማጠናቀቅ የተወሰኑ ስራዎች እንደሚቀሯቸው ተነግሯል።
ተጨዋቹ የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ወደ ማንችስተር ለመጓዝ በዝግጅት ላይ መሆኑ ሲገለፅ በሚቀጥሉት ቀናት ዝውውሩ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የርገን ክሎፕ ወደ አሜሪካ ያመሩ ይሆን ?
የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ጀርመናዊውን አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ በቀጣይ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርገው በሀላፊነት ለመሾም ጥረት ሊያደርጉ መሆኑ ተገልጿል።
አሜሪካ ካዘጋጀችው የዘንድሮው የኮፓ አሜሪካ ምድብ ጨዋታ መሰናበቷን ተከትሎ አሰልጣኝ ግሬግ ቤርሀልተርን ከአሰልጣኝነት ማሰናበቷ ይታወቃል።
አሜሪካ በቀጣይ በጣምራ በምታዘጋጀው የ2026 አለም ዋንጫ ውድድር አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ቡድኑን እንዲመሩ ፍላጎት እንዳላት ተዘግቧል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ጀርመናዊውን አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ በቀጣይ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርገው በሀላፊነት ለመሾም ጥረት ሊያደርጉ መሆኑ ተገልጿል።
አሜሪካ ካዘጋጀችው የዘንድሮው የኮፓ አሜሪካ ምድብ ጨዋታ መሰናበቷን ተከትሎ አሰልጣኝ ግሬግ ቤርሀልተርን ከአሰልጣኝነት ማሰናበቷ ይታወቃል።
አሜሪካ በቀጣይ በጣምራ በምታዘጋጀው የ2026 አለም ዋንጫ ውድድር አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ቡድኑን እንዲመሩ ፍላጎት እንዳላት ተዘግቧል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዩናይትድ ዝውውሮቹን በፍጥነት ማጠናቀቅ ይፈልጋሉ ! በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት ማንችስተር ዩናይትዶች የማትያስ ዴሊትን እና ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል። ማንችስተር ዩናይትድ አሁን ላይ ከባየር ሙኒክ ጋር በማትያስ ዴሊት የዝውውር ሒሳብ ዙሪያ ለስምምነት መቃረባቸው ተነግሯል። ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር ለማጠናቀቅ…
ጆሽዋ ዚርክዜ ዛሬ ምሽት ወደ እንግሊዝ ያመራል !
ኔዘርላንዳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ ከቦሎኛ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ ዛሬ ምሽት ወደ እንግሊዝ እንደሚያመራ ተገልጿል።
የ 23ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ በነገው ዕለት የህክምና ምርመራውን በማድረግ በይፋ ማንችስተር ዩናይትድን ይቀላቀላል።
ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን በ 42.5 ሚልዮን ዩሮ በሆነ የዝውውር ሒሳብ በአምስት አመት ኮንትራት እንደሚያስፈርሙት ተገልጿል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ሩድ ቫን ኔስትሮይ እና ሬኔ ሀኬን በክለቡ የአሰልጣኞች ቡድን ውስጥ ማካተታቸውን በይፋ አስታውቀዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ኔዘርላንዳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ ከቦሎኛ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ ዛሬ ምሽት ወደ እንግሊዝ እንደሚያመራ ተገልጿል።
የ 23ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ በነገው ዕለት የህክምና ምርመራውን በማድረግ በይፋ ማንችስተር ዩናይትድን ይቀላቀላል።
ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን በ 42.5 ሚልዮን ዩሮ በሆነ የዝውውር ሒሳብ በአምስት አመት ኮንትራት እንደሚያስፈርሙት ተገልጿል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ሩድ ቫን ኔስትሮይ እና ሬኔ ሀኬን በክለቡ የአሰልጣኞች ቡድን ውስጥ ማካተታቸውን በይፋ አስታውቀዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዩናይትድ ከቫን ዴ ቢክ ዝውውር ስንት ያገኛል ? የማንችስተር ዩናይትዱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዶኒ ቫን ዴቢክ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊውን የስፔን ክለብ ጂሮና ለመቀላቀል ከጫፍ መድረሱ ተገልጿል። ቀያዮቹ ሴጣኖች ከተጨዋቹ ዝውውር 500,000 ዩሮ እንደሚቀበሉ ሲገለፅ በውሉ ውስጥ ታይቶ የሚጨምር እስከ አራት ሚልዮን ዩሮ የሚሆን ክፍያ እንደሚካተት ተነግሯል። ኔዘርላንዳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች…
ዶኒ ቫን ዴ ቢክ በይፋ ጂሮናን ተቀላቀለ !
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊው የስፔኑ ክለብ ጂሮና ኔዘርላንዳዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዶኒ ቫን ዴቢክ ከማንችስተር ዩናይትድ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።
ጂሮና ለተጨዋቹ ዝውውር 500,000 ዩሮ የዝውውር ሒሳብ ለማንችስተር ዩናይትድ መክፈላቸው ተገልጿል።
ዶኒ ቫን ዴቢክ በጂሮና እስከ 2028 የሚያቆየውን የአራት አመት ኮንትራት መፈረሙ ይፋ ተደርጓል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊው የስፔኑ ክለብ ጂሮና ኔዘርላንዳዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዶኒ ቫን ዴቢክ ከማንችስተር ዩናይትድ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።
ጂሮና ለተጨዋቹ ዝውውር 500,000 ዩሮ የዝውውር ሒሳብ ለማንችስተር ዩናይትድ መክፈላቸው ተገልጿል።
ዶኒ ቫን ዴቢክ በጂሮና እስከ 2028 የሚያቆየውን የአራት አመት ኮንትራት መፈረሙ ይፋ ተደርጓል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
የርገን ክሎፕ ወደ አሜሪካ ያመሩ ይሆን ? የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ጀርመናዊውን አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ በቀጣይ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርገው በሀላፊነት ለመሾም ጥረት ሊያደርጉ መሆኑ ተገልጿል። አሜሪካ ካዘጋጀችው የዘንድሮው የኮፓ አሜሪካ ምድብ ጨዋታ መሰናበቷን ተከትሎ አሰልጣኝ ግሬግ ቤርሀልተርን ከአሰልጣኝነት ማሰናበቷ ይታወቃል። አሜሪካ በቀጣይ በጣምራ በምታዘጋጀው የ2026 አለም ዋንጫ ውድድር…
ክሎፕ የአሜሪካን ጥያቄ ውድቅ አደረጉ !
በቅርቡ ከሊቨርፑል ጋር የተለያዩት ጀርመናዊው አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የቀረበላቸውን የአሰልጣኝነት ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸው ተገልጿል።
የአሜሪካ እግርኳስ ፌዴሬሽን ባለፈው ሳምንት ከአሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ጋር ተነጋግረው የነበረ ቢሆንም ብሔራዊ ቡድኑን የሚቀላቀሉበት እድል አለመኖሩ ተነግሯል።
አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከዚህ በፊት እንደተናገሩት አሁን ላይ ወደ ሀላፊነት መመለስ እንደማይፈልጉ እና እረፍት ማድረግ እንደሚፈልጉ ማረጋገጣቸው ተዘግቧል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
በቅርቡ ከሊቨርፑል ጋር የተለያዩት ጀርመናዊው አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የቀረበላቸውን የአሰልጣኝነት ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸው ተገልጿል።
የአሜሪካ እግርኳስ ፌዴሬሽን ባለፈው ሳምንት ከአሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ጋር ተነጋግረው የነበረ ቢሆንም ብሔራዊ ቡድኑን የሚቀላቀሉበት እድል አለመኖሩ ተነግሯል።
አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከዚህ በፊት እንደተናገሩት አሁን ላይ ወደ ሀላፊነት መመለስ እንደማይፈልጉ እና እረፍት ማድረግ እንደሚፈልጉ ማረጋገጣቸው ተዘግቧል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
#BiniyamGirmay🇪🇷 ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢንያም ግርማይ በዓለም ላይ ከፍተኛ የሆነ ስፍራ የሚሰጠውን ቱር ደ ፍራንስ የተሰኘውን የፈረንሳዩን የብስክሌት ውድድር ‘ስቴጅ 3’ በማሸነፍ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ በመሆን ለኤርትራ እና ለአፍሪካ ታሪክ ሰርቷል። ከውድድሩ መጠናቀቅ በኋላ የውድድሩ ተሳታፊዎች ወደ ቢኒያም በመሄድ " እንኳን ደስ አለህ ! አንተ በጣም ምርጡ ነበርክ ፤ በጣምም ጠንካራ…
ቢኒያም ግርማይ ለሶስተኛ ጊዜ አሸናፊ ሆነ !
ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ በታላቁ የቱር ደ ፍራንስ ውድድር በአስራ ሁለተኛው ቀን ውድድር ቀድሞ በመግባት ለሶስተኛ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል።
በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች የነበረውን ከባድ ፉክክር መርታት የቻለው ቢኒያም ግርማይ በቱር ደ ፍራንስ በርካታ ነጥብ በመሰብሰብ አረንጓዴ ማሊያውን ( Green Jersey ) አስጠብቋል።
ቢኒያም 203 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ12ኛ ቀን ውድድር በ4 ሰዓት ከ17 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት አጠናቋል።
በዘንድሮው ውድድር በአጠቃላይ ውጤት ታዴ ፖጋቻር የቢጫ ማሊያውን ውድድር እየመራ ሲሆን ፣ ቢኒያም ግርማይ ደግሞ በርካታ ነጥብ በመሰብሰብ የአረንጓዴ ማሊያ መሪ ነው።
ቢኒያም ግርማይ ከድሉ በኋላ በሰጠው አስተያየት " ከአሁን ጀምሬ የአረንጓዴ ማልያውን ለማስቀጠል ትኩረት ማድረጌን እቀጥላለሁ ፣ ይህንን ክብር ካገኘሁ በኋላ ፈጣንነት እየተሰማኝ ነው።"ሲል ተደምጧል።
ቢኒያም ባለፈው ሳምንት ሶስተኛውን መድረክ በማሸነፍ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ ሆኖ ታሪክ መፃፉ አይዘነጋም።
ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ በተለያዩ ጊዜያት ባስመዘገባቸው ስኬቶች “ የአፍሪካ የብስክሌት ንጉሥ “ የሚል ቅፅል ስም ተሰጥቶታል።
Credit - BBC News Amharic
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ በታላቁ የቱር ደ ፍራንስ ውድድር በአስራ ሁለተኛው ቀን ውድድር ቀድሞ በመግባት ለሶስተኛ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል።
በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች የነበረውን ከባድ ፉክክር መርታት የቻለው ቢኒያም ግርማይ በቱር ደ ፍራንስ በርካታ ነጥብ በመሰብሰብ አረንጓዴ ማሊያውን ( Green Jersey ) አስጠብቋል።
ቢኒያም 203 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ12ኛ ቀን ውድድር በ4 ሰዓት ከ17 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት አጠናቋል።
በዘንድሮው ውድድር በአጠቃላይ ውጤት ታዴ ፖጋቻር የቢጫ ማሊያውን ውድድር እየመራ ሲሆን ፣ ቢኒያም ግርማይ ደግሞ በርካታ ነጥብ በመሰብሰብ የአረንጓዴ ማሊያ መሪ ነው።
ቢኒያም ግርማይ ከድሉ በኋላ በሰጠው አስተያየት " ከአሁን ጀምሬ የአረንጓዴ ማልያውን ለማስቀጠል ትኩረት ማድረጌን እቀጥላለሁ ፣ ይህንን ክብር ካገኘሁ በኋላ ፈጣንነት እየተሰማኝ ነው።"ሲል ተደምጧል።
ቢኒያም ባለፈው ሳምንት ሶስተኛውን መድረክ በማሸነፍ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ ሆኖ ታሪክ መፃፉ አይዘነጋም።
ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ በተለያዩ ጊዜያት ባስመዘገባቸው ስኬቶች “ የአፍሪካ የብስክሌት ንጉሥ “ የሚል ቅፅል ስም ተሰጥቶታል።
Credit - BBC News Amharic
@tikvahethsport @kidusyoftahe