TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray ትናንተ የካቲት 12 /2017 ዓ.ም በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ በነዋሪዎችና በአከባቢው በሚገኘው የትግራይ ኃይል አባላት መካከል ግጭት ተከስተዋል። በግጭቱ ምክንያት በ20 የቀበሌው ነዋሪዎችና ቁጥራቸው ባልታወቀ የትግራይ ኃይል አባላት ላይ ጉዳት ደርሷል። ያጋጠመ ሞት የለም። ግጭቱ እንዴት እና በምን ምክንያት አጋጠመ ? በአዲስ አለም ቀበሌ ሁለት…
#UPDATE
" ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " - የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር
" ሃይል በመጠቀም የመንግስት መዋቅር ለማፍረስ የሚደረግ ህገ-ወጥ እርምጃ ተቀባይነት የለውም " አለ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ የካቲት 13 /2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ፤ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ ገበሬ ማህበር የትግራይ ኃይል አባላት በነዋሪ አርሶ አደሮች ላይ ያደረሱትን ጥቃት አውግዟል።
" የተወሰኑ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ መዋቅር ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ እየታዘብን ነው " ያለው መግለጫው " በሰሓርቲ ወረዳ የተከሰተው አሳዛኝ ተግባር እንደ አንድ ማሳያ መውሰድ ይቻላል " ብሏል።
" ሰራዊቱ የህዝብ ህልውና ለመጠበቅ እንጂ የአንድ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት የተሰለፈ አይደለም " ያለው ጊዚያዊ አስተዳደሩ " ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " ሲል አስጠንቅቋል።
" ማንኛውም የህግ ወይም የአስራር ክፍተት ሲኖር የሚሊሻና የፓሊስ ሃይል ከህዝባቸው በመተባበር የሚፈቱት እና የሚያርሙት እንጂ ሰራዊት ወደ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ማሰማራት የሚያስገድድ ሁኔታ ፈፅሞ እንደሌለ የለም " ሲል ገልጿል።
" ይህንን ህገ-ወጥ አካሄድ የሚያበረታቱ እና የሚያግዙ ፓለቲከኞች እና የሰራዊት አመራሮች አደብ እንዲገዙ " ሲልም አስጠንቅቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " - የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር
" ሃይል በመጠቀም የመንግስት መዋቅር ለማፍረስ የሚደረግ ህገ-ወጥ እርምጃ ተቀባይነት የለውም " አለ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ የካቲት 13 /2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ፤ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ ገበሬ ማህበር የትግራይ ኃይል አባላት በነዋሪ አርሶ አደሮች ላይ ያደረሱትን ጥቃት አውግዟል።
" የተወሰኑ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ መዋቅር ለማፍረስ ሲንቀሳቀሱ እየታዘብን ነው " ያለው መግለጫው " በሰሓርቲ ወረዳ የተከሰተው አሳዛኝ ተግባር እንደ አንድ ማሳያ መውሰድ ይቻላል " ብሏል።
" ሰራዊቱ የህዝብ ህልውና ለመጠበቅ እንጂ የአንድ ቡድን የስልጣን ጥማት ለማርካት የተሰለፈ አይደለም " ያለው ጊዚያዊ አስተዳደሩ " ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ወደ ማንወጣው ቀውስ እንደምንገባ የቅርብም የሩቁም ሊገነዘበው ይገባል " ሲል አስጠንቅቋል።
" ማንኛውም የህግ ወይም የአስራር ክፍተት ሲኖር የሚሊሻና የፓሊስ ሃይል ከህዝባቸው በመተባበር የሚፈቱት እና የሚያርሙት እንጂ ሰራዊት ወደ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ማሰማራት የሚያስገድድ ሁኔታ ፈፅሞ እንደሌለ የለም " ሲል ገልጿል።
" ይህንን ህገ-ወጥ አካሄድ የሚያበረታቱ እና የሚያግዙ ፓለቲከኞች እና የሰራዊት አመራሮች አደብ እንዲገዙ " ሲልም አስጠንቅቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#Update
በእግር ኳስ ተጫዋቹ አለልኝ አዘነ ግድያ የተከሰሱት ሚስቱና የእህቷ ባል የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻላቸዉ ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ሰጠ።
ባሳለፍነዉ ዓመት መጋቢት 17/2016 ዓ/ም የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንና የባህርዳር ከተማ ተጫዋች የነበረዉ አለልኝ አዘነ በአርባምንጭ ከተማ በድንገት ሕይወቱ ማለፉ በርካቶችን ያሳዘነ እንደነበር አይዘነጋም።
በተጫዋቹ አሟሟትና ሌሎች ሁኔታዎችን መነሻ አድርጎ ፖሊስ ሚስቱንና የእህቷን ባል በቁጥጥር ስር አዉሎ ክስ መመስረቱ የሚዘነጋ አይደለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቀደምሲ ል በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ መረጃዎችን ሲሰራ የቆየ ሲሆን ሰሞኑን ከጋሞ ዞን ፍትሕ መምሪያ ባገኘዉ መረጃ እስካሁን በነበረዉ ሂደት ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ክሱን ያስረዱልኛል ያላቸዉን የሰዉ፣ የሰነድና የምርመራ ማስረጃዎችን በማቅረብ ለፍርድ ቤቱ ክሱን አስረድቷል።
ጉዳዩን የያዘዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሾች የመከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ለየካቲት 10/2017ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ተከሳሾች አሟልተዉ ማቅረብ ባለመቻላቸዉ ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ለመጋቢት 10/2017 ዓ/ም መሰጠቱን የጋሞ ዞን ፍትህ አካላት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
አርባ ምንጭ ከተማ በተለምዶ ልማት ሰፈር ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ተወልዶ ያደገው አለልኝ አዘነ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸውና በኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ በተለያዩ ቡድኖች ዉጤታማ እንቅስቃሴ የነበረዉ አማካይ ተከላካይ ነበር።
ተጫዋቹ ሕይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ የባሕር ዳር ከተማ ቋሚ ተሰላፊ ተጫዋች የነበረ ሲሆን ከዚያ አስቀድሞ በሐዋሳ ከተማ እና በመቐለ 70 እንደርታ ዉጤታማ ጊዜ አሳልፏል።
ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል።
@tikvahethiopia
በእግር ኳስ ተጫዋቹ አለልኝ አዘነ ግድያ የተከሰሱት ሚስቱና የእህቷ ባል የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻላቸዉ ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ሰጠ።
ባሳለፍነዉ ዓመት መጋቢት 17/2016 ዓ/ም የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንና የባህርዳር ከተማ ተጫዋች የነበረዉ አለልኝ አዘነ በአርባምንጭ ከተማ በድንገት ሕይወቱ ማለፉ በርካቶችን ያሳዘነ እንደነበር አይዘነጋም።
በተጫዋቹ አሟሟትና ሌሎች ሁኔታዎችን መነሻ አድርጎ ፖሊስ ሚስቱንና የእህቷን ባል በቁጥጥር ስር አዉሎ ክስ መመስረቱ የሚዘነጋ አይደለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቀደምሲ ል በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ መረጃዎችን ሲሰራ የቆየ ሲሆን ሰሞኑን ከጋሞ ዞን ፍትሕ መምሪያ ባገኘዉ መረጃ እስካሁን በነበረዉ ሂደት ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ክሱን ያስረዱልኛል ያላቸዉን የሰዉ፣ የሰነድና የምርመራ ማስረጃዎችን በማቅረብ ለፍርድ ቤቱ ክሱን አስረድቷል።
ጉዳዩን የያዘዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሾች የመከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ለየካቲት 10/2017ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ተከሳሾች አሟልተዉ ማቅረብ ባለመቻላቸዉ ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ለመጋቢት 10/2017 ዓ/ም መሰጠቱን የጋሞ ዞን ፍትህ አካላት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
አርባ ምንጭ ከተማ በተለምዶ ልማት ሰፈር ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ተወልዶ ያደገው አለልኝ አዘነ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸውና በኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ በተለያዩ ቡድኖች ዉጤታማ እንቅስቃሴ የነበረዉ አማካይ ተከላካይ ነበር።
ተጫዋቹ ሕይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ የባሕር ዳር ከተማ ቋሚ ተሰላፊ ተጫዋች የነበረ ሲሆን ከዚያ አስቀድሞ በሐዋሳ ከተማ እና በመቐለ 70 እንደርታ ዉጤታማ ጊዜ አሳልፏል።
ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል።
@tikvahethiopia