TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
🔈 #የሹፌሮችድምጽ

“ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው ለአጃቢ እስከ 2,000 ብር ለመክፈል ተገደናል። በቀናት ብቻ ከ12 በላይ ሹፌሮች ታግተዋል ” - ማኀበሩ

የጸጥታ መደፍረስ በሹፌሮችና ተሳፋሪዎች ግድያና እገታ ማስከተሉን፣ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው አሽከርካሪዎች ለአጃቢ 2,000 ለመክፈል መገደዳቸውን ጣና የአሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

“ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው ለአጃቢ እስከ 2,000 ብር ለመክፈል ተገደናል። በቀናት ብቻ ከ12 በላይ ሹፌሮች ታግተዋል ” ሲልም በሁነቱ ተማሯል።

በአማራ ክልል ከገንዳውሃ ወደ ጎንደር ባለው መንገድ ረቡዕ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ/ም አንድ ሰው ተገድሎ፣ ሁለቱ ደግሞ መቁሰላቸውን ገልጿል።

“ በአስር ቀናት ደቡብ ጎንደር 3 ሹፌሮች፣ በደባርቅ ዙሪያ 2 ረዳቶችና 6 ሹፌሮች፣ ገንዳውሃ 2 ሹፌሮች፣ አብርሃጀራ አንድ ሹፌር በታጠቁ አካላት ታግተዋል። በአብርሃጅራ ሹፌር ተተኩሶበት አምልጧል፤  ሁለት ቦቴዎችን ወቅንና ገደብዬ መካከል አግተዋቸዋል ” ነው ያለው።

ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል በዝርዝር  ምን አለ ?

“ ከአሸሬ እስከ ሶረቃ የሚያስፈራ ቦታ አለ። በፈቃድ ለታጠቁ የአካባቢው ሰዎች 2,000 ብር እየከፈልን ነው የምናልፈው። በቅርቡ አንድ አጃቢ አጋች መትቷል ሹፌር ሊያግት ሲል ወርዶ ተኮሰበት።

ጨንቆን ነው እንጂ ይሄ ሂደት ደግሞ መጥፎ ነው። ህግ ባለመከበሩ ምክንያት ለሹፌሮች እለታዊ መፍትሄ ሆኗል። ግን የአጃቢነት ስራ እየሰሩ ያሉ ሰዎች እንዴት ነው የአካባቢ ሰላም እንዲመለስ የሚፈልጉት?

ስለዚህ እገታ ያለባቸው ቦታዎች ይታወቃሉ። በአርማጭሆ በኩል ከከተማው አፍንጫ ስር ከ10 ጊዜ በላይ እገታ ተፈጽሞበት ቦታው ላይ የጸጥታ አካል አይቀመጥም። 

የጸጥታ ዘርፉ ትኩረት ቢሰጥ ችግሩን መቆጣጠር ይችላል። ምክንያቱም በአንድ አጃቢ ከፍለን የምናልፈው አካባቢ ነው። መዝረፊያ በሮች የሚታወቁ ናቸው”
ብሏል።

ለአጃቢ ከመክፈል በተጨማሪ ሹፌሮች ከጸጥታ ስጋት አንጻር በ100ዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን ዙሪያ ጥምጥም እንዲጓዙ እየተገደዱ መሆኑም ተገልጿል።

ማኀበሩ በመንገዱ ዙሪያ ምን አለ ?

“ በደባርቅ በኩል ባለው መንገድ ከደብረ ታቦር ጋይንት መንገዱ ችግር ትልቅ አለበት። መንገዱ አማራ ክልል ከጅቡቲ የሚገናኝበት ነው። ማደበሪያ የሚገባው በጋይንት ነው። በሚሌ፣ ጭፍራ፣ ሃራ፣ ወልዲያ አድርጎ በደብረ ታቦር አድርጎ ይመጣል።

ግን ማዳበሪያ የሚጭኑ ተሽከሪካሪዎች በዚህ አመት በጸጥታው ችግር ምክንያት ተጨማሪ መንገድ እየተጓዙ በአዲስ አበባ በኩል ለመምጣት ተገደዋል። ከደጀን በእጀባ ነው የሚመጡት ወደ ጎጃምና ጎንደር ጭምር።

በጸጥታው ችግር ተሽከርካሪዎች ከ500 ኪሎ ሜትር በላይ ተጨማሪ መንገድ ለመሄድ ተገደዋል። ይህ ለአርሶ አደሩም ጉዳት አለው። 1,950 ብር ነው አንድ ኩንታል ማዳበሪያ ከጅቡቲ የሚመጣው። ትራንስፓርት ኮስቱ 1,900 ብር ሲሆን፣ የማዳበሪያው ዋጋ ይንራል።

በጋይንት ቦቴዎች ይሄዳሉ። ጭነው ይመጡና በጸጥታው ችግር መመለሻ ሲያጡ በደባርቅ፣ ዛሪማ፣ በሽሬ፣ ከሽሬ መቀሌ፣ ከመቀሌ አብዓላ አድርገው በአፍዴራ ይወጣሉ። ይሄ ማለት ከ600 በላይ ተጨማሪ ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ።

በጎንደር መተማ መንገድ በመተማ በኩል ነው ኢምፖርት ኤክስፖርት የሚገባው። የመተማ ጎንደርን መንገድ የጸጥታ ችግሩን በመፍራት አሽከርካሪዎች በአብርሃጅራ ዙረው እየገቡ ነው። 

180 ኪሎ ሜትር ሲጓዙ የነበሩ አሽከርካሪዎች 140 ኪሎ ሜትር በመጨመር 320 ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ ”
ብሏል።

(ስለጉዳዩ ለጸጥታ አካላት ጥያቄ የምናቀርብ ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#GlobalBank

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የዲጅታል ባንኪንግ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።

አገልግሎት መስጠት የጀመረው የዲጂታል ባንኪንግ ማዕከል የባንክ ሂሳብ መክፈት፣ ገንዘብ ገቢ ማድረግና ወጪ ማድረግ፣ ቀሪ ሂሳብና የሂሳብ መግለጫ ማሳየት፣ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን መመንዘር፣ የተለያዩ ክፍያዎችን መፈፀም ያስችላል።

በተጨማሪም ያለ ኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ማግኘት፣ ቼክ መመንዘርና ገቢ ማድረግን  ጨምሮ ደንበኞች የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት መጠቀም በሚፈልጉበት ወቅት በማዕከሉ በመገኘት ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጁ ታብሌቶች መጠቀም ያስችላቸዋል።

ማዕከሉ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ክፍል ያለው መሆኑንና ተቀዳሚ (corporate) ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው የቪዲዮ ባንኪንግ አገልግሎት ማገኝት የሚያስችላቸው አገልግሎትም እንደሚሰጥ ጠቅሷል።

የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ይህ ማዕከል ሥራ መጀመሩ ባንኩ ተወዳዳሪ እንዲሆን ከማድረጉም ባሻገር የባለአክሲዮኖችን ጥቅም ከፍ ከማድረግ እና የሀገርን ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ጠቅሰዋል።

ባንኩ በዘንድሮው አመትም ከታክስ በፊት ብር 757.6 ሚሊዮን ማትረፉን የገለጸ ሲሆን የቅርንጫፍ ብዛቱንም ወደ 238( ሁለት መቶ ሰላሳ ስምንት ) ከፍ ማድረግ ችሏል። በአሁን ሰዓትም ባንኩ ከ 1.7 ሚሊየን በላይ ደንበኞች እንዳሉት አሳውቋል፡፡

የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ደ/ር ተስፋዬ ቦሩ ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን የባንክ ካፒታል ዕድገት ዝቅተኛ ጣሪያ በቀረው ጊዜ ውስጥ እንደሚያሳካ ገልጸዋል።

ባንኩ የተቀማጭ ሂሳቡን  ከ 20.6 ቢሊዮን ብር በላይ ያደረሰ መሆኑንና የባንኩ ጠቅላላ ሃብት ደግሞ ከ 26.6 ቢሊየን ብር በላይ መድረሱንም አስታውቋል።

ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሜክሲኮ አካባቢ  ለዋና መ/ቤት ግንባታ በተረከበው  5,550 ካ.ሜ ቦታ ላይ የወደፊት የዋና መ/ቤት ህንፃ ለመገንባት በሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች ላይ እየሰራ ይገኛል።

#GlobalBankEthiopia
" ለቅሬታችን ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን ለርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበናል " - የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መምህራን

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።

" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።

ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?

የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።

" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።

" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA " ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " - ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ በፊላደልፊያ ከተማ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከሰከሰ። የሕክምና አውሮፕላኑ ድርጅት-ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በሰጠው መግለጫ ፤ ጄቱ አርብ…
#USA : ከቀናት በፊት በአሜሪካ አላስካ ግዛት 9 መንገደኞችን እና 1 አብራሪን ይዞ ሲጓዝ የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ደብዛው ጠፍቶ ከቆየ በኃላ በአየር እና ምድር በተደረገ አሰሳ ስብርባሪው ተገኝቷል።

በአደጋው በሕይወት የተረፈ ሰው የለም።

የ3 ሰዎች አስክሬን በነፍስ አድን ሰራተኞች ተገኝቷል።

ይህ አደጋ በአሜሪካ ከ1 ሳምንት ባነሰ ጊዜ የደረሰ 3ኛው የአቬዬይሽን አደጋ መሆኑን የቪኦኤ ዘገባ ያሳያል።

በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከስክሶ በህይወት የተገኘ እንደሌለ ይታወቃል።

ከዚህ አደጋ በፊት ደግሞ በዋሽንግቶን ዲሲ 60 መንገደኞች እና 4 የበረራ ሰራተኞችን የያዘ የመንገደኞች አውሮፕላን 3 ሰዎች ከያዘ የጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ አንድም ሰው በህይወት አለመገኘቱ መገለጹ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#MPESASafaricom

ስለ M-PESA ኢትዮጵያ አዳዲስ ዜናዎች እና አገልግሎቶችን ለማወቅ ማህበራዊ ሚዲያ  ገፃችንን እንቀላቀል! 💚📲

Telegram-  https://yangx.top/+-cP9IxZdfKBkNTQ0
Facebook: https://www.facebook.com/share/14qsy45H7u/?mibextid=wwXIfr
Titkok- https://www.tiktok.com/@mpesa.ethiopia?_t=ZM-8tcz302wLwL&_r=1
LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/m-pesaethiopia/about/
Instagram: https://www.instagram.com/mpesa.ethiopia/
Youtube- http://www.youtube.com/@M-PESAEthiopia
Twitter- https://x.com/m_ethiopia58462?s=21

#MPESAEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እናትፓርቲ እናት ፓርቲ የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው የጣሪያ ግድግዳ/ ንብረት ግብር መመርያ እንዲቆም የመሠረተው ክስ በፍርድ ቤት ተቀባይነት አግኝቶ መመሪያው "ተፈጻሚ ሊሆን አይገባም" ሲል ፍርድ ቤት ጥር 9 ቀን ብይን መስጡቱን ፓርቲው አስታውቋቃ። ፓርቲው የወጣው መመርያ " ሕግን ባልተከተለ መንገድ እና የከተማ አስተዳደሩ ባልተሰጠው ሥልጣን የወጣ…
" ፋይናንስ ቢሮ ይግባኝ በመጠየቁ አፈጻጸሙ ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ ታግዶ ነው ያለው " - እናት ፓርቲ

እናት ፓርቲ የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው የጣሪያ ግድግዳ / ንብረት ግብር መመርያ እንዲቆም የመሠረተው ክስ በፍርድ ቤት ተቀባይነት አግኝቶ መመሪያው "ተፈጻሚ ሊሆን አይገባም " ሲል ፍርድ ቤት ጥር 9 ቀን ብይን መስጠቱን ፓርቲው ማስታወቁ ይታወሳል።

ይህንንም የፍርድ ቤት ውሳኔ በጋዜጣዊ መግለጫው አሳውቆ የነበረው ፓርቲው የፋይናንስ ቢሮ ይግባኝ በመጠየቁ ምክንያት የውሳኔው አፈጻጸም ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ መታገዱን የፓርቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰይፈሥላሴ አያሌው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የፓርቲው ፕሬዝዳንት በዝርዝር ለቲክቫህ በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?

" ጥር 9 ቀን 6:30 ላይ ውሳኔውን ከፍተኛ ፍ/ቤት አሳልፎ 7:30 ላይ የፋይናንስ ቢሮ አቃቢ ህግ በቃለ መሃላ ' ለከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ይግባኝ እስከምል ድረስ አፈጻጸሙ ይታገድልን ለ15 ቀንም ፓርቲው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳይሰጥ ' አሉ።

የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ መጠበቅ ስለነበረብን እኛም ለ15 ቀናት ጠበቅን 15 ቀኑ የሞላው አርብ ነበር ሰኞ መግለጫ ሰጠን።

በ15 ቀን ውስጥ ይግባኝ ባይጠይቁም ከትላንት በስቲያ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት አፈጻጸሙ ታግዶ እንዲቆይ በሚል ይግባኝ መጠየቃቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ቢሮአችን ላይ ተለጥፎ አግኝተናል።

እየተነጋገርን ያለነው ስለ ህግ ጉዳይ ነው ክፍያው ይቀጥል አይቀጥል አይደለም እኛ እያልን ያለነው ከተማ መስተዳደሩ የጣለው ግብር ከህግ አግባብ ውጪ እንደሆነ ነው መሆኑን ደግሞ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አረጋግጦልናል።

እያንዳንዱ ከህዝብ የሚሰበሰብ ሳንቲም የህግ መሰረት ሊኖረው ያስፈልጋል ይህ የጣራና ግድግዳ ግብር እየተሰበሰበ ያለው ከህግ አግባብ ውጪ ነው የሚከፈለው ገንዘብ መቆም አለበት ብለን ነው ክስ የመሰረትነው።

ፍርድ ቤቱም ክፈሉ አትክፈሉ አይደለም እያለ ያለው ነገር ግን ለክፍያ መመሪያ የነበረው በሚያዝያ 2015 የወጣው እና እንዲፈጸም የሚያስገድደው መመሪያ መሻሩን ነው የገለጸው።

በዚህም መሰረት የህግ ውሳኔ አፈጻጸም አካሄድ ቢኖረውም የከተማ መስተዳደሩ ይህንን ግብር ወደ ፊት እንዲሽረው ይጠበቃል።

የፋይናንስ ቢሮ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቢጠይቅም የከፍተኛ ፍ/ቤትን ውሳኔ ያጸድቀዋል ብለን ነው የምናምነው ቢሽረው እንኳ ሰበር ሰሚ ችሎት በመኖሩ ጉዳዩን እስከመጨረሻው እንገፋበታለን።

የኢትዮጵያ ህዝብ 10 ሺ፣20 ሺ እና ሚሊየን ለጣራ እና ግድግዳ በሚል ከፍሎ አያውቅም እንዲህ መክፈል የተጀመረው ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ ነው መቼም ይጀመር መመሪያው ህገ ወጥ ነው " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

" የመክፈያ ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ግብራችሁን ያልከፈላችሁ እንድትከፍሉ እናሳስባለን " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ " በተለመዶ የጣራና ግድግዳ ግብር እየተባለ የሚጠራው የቤትና ቦታ ግብር የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች ግብሩን ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ እንድትከፍሉ እናሳስባለን " ብሏል።

በዚሁ መግለጫው ግብሩ የከተማ ቦታና ቤት ግብር በከተማ ቤት ግብር አዋጅ ቁጥር 80/1968 መሰረት የሚሰበሰብ ግብር መሆኑ መገንዘብ እንደሚገባ ያሳሰበ ሲሆን 429 ሺህ 829 ግብርከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር ክፍያ እንዲፈፅሙ ይጠበቃል ብሏል።

የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " ግብር ከፋይ ነዋሪዎች ያለቅጣት መክፈያው ጊዜ ሳይጠናቀቅ ከየካቲት 30 በፊት እንዲከፍሉ እና ያልከፈሉ ነዋሪዎች ግን ቅጣቱን ከነወለዱ ለመክፈል እንደሚገደዱ " ገልጸዋል።

አቶ ሰውነት " እናት ፓርቲ ካስተላለፈው መልእክት ጋር በተያያዘ እኛን የሚመለከተን ነገር የለም " ያሉ ሲሆን ለቢሮው የደረሰው ምንም አይነት የፍርድ ቤት እግድም ሆነ መመሪያ አለመኖሩን በመግለጽ " ሰው ጋር መዘናጋት ይታያል ይህ ደግሞ ለቅጣት ሊዳርጋቸው ይችላል በቀረው ጊዜ ክፍያችሁን ፈጽሙ " ሲሉ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መቄዶንያ

" ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው !! "

መቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በሚያስገነባው ሆስፒታል ጭምር ያለው ህንፃ ለማጠናቀቅ የገንዘብ እጥረት ስለገጠመው እግዛ እንዲደረግ ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ መቅረቡ ይታወሳል።

ዛሬ “ በሰይፉ ኢቢኤስ የዩቱብ ቻነል ” ድጋፍ ማድረጊያ መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው።

ደጋጎች ሁሉ ድጋፍ እንድታደርጉ ጥሪ እናቀርባለን።

የድጋፍ ማድረጊያ አማራጮች ከላይ ተያይዘዋል።

መቄዶንያ “ ህንፃው ለማጠናቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። ለማጠናቀቅ ወደ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልገናል ” ማለቱ አይዘነጋም።

በቀጥታ ይከታተሉ 👇
https://www.youtube.com/live/q0bMjwt9PvM?feature=shared

@tikvahethiopia