ፎቶ ፦ ትላንት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በቻይና ምድር የመጀመሪያዋን ደብር በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ አከናውናለች።
ለሐዋርያዊ አገልግሎት ቻይና እንደሚገኙት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቻይና ምድር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጀመርያዋን ቤተ ክርስቲያን ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ብለው በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ በመፈጸም ምዕምናንን አቁርበዋል።
በቻይና የመጀመሪያው አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆንም ሾመዋል።
ከቻይና ክፍላተ ግዛቶች የተሰባሰቡ ምዕመናን ፣ ቻይናውያንና ትውልደ ቻይናውያን በሥርዓተ ቅዳሴው ተሳፍተዋል።
ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም !
Photo Credit - EOTC Far East Diocese & ETOC TV
@tikvahethiopia
ለሐዋርያዊ አገልግሎት ቻይና እንደሚገኙት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቻይና ምድር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጀመርያዋን ቤተ ክርስቲያን ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ብለው በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ በመፈጸም ምዕምናንን አቁርበዋል።
በቻይና የመጀመሪያው አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆንም ሾመዋል።
ከቻይና ክፍላተ ግዛቶች የተሰባሰቡ ምዕመናን ፣ ቻይናውያንና ትውልደ ቻይናውያን በሥርዓተ ቅዳሴው ተሳፍተዋል።
ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም !
Photo Credit - EOTC Far East Diocese & ETOC TV
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
📽 😍 የምርጥ አስሩን ቆይታ እንከታተል!
የሳፋሪኮም #1Wedefit ዲጂታል የሙዚቃ ውድድር ኮከቦቻችን ያደረጉትን አስደሳች ቆይታ የመጀመሪያው ክፍል ቅዳሜ ምሽት 3 ሰአት በአርትስ ቲቪ እንዲሁም እሁድ ከሰአት 9፡00 ደግሞ በአባይ ቲቪ እንድትከታተሉ እንጋብዛችኋለን!
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
📽 😍 የምርጥ አስሩን ቆይታ እንከታተል!
የሳፋሪኮም #1Wedefit ዲጂታል የሙዚቃ ውድድር ኮከቦቻችን ያደረጉትን አስደሳች ቆይታ የመጀመሪያው ክፍል ቅዳሜ ምሽት 3 ሰአት በአርትስ ቲቪ እንዲሁም እሁድ ከሰአት 9፡00 ደግሞ በአባይ ቲቪ እንድትከታተሉ እንጋብዛችኋለን!
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
" በመሳሪያ የሚደረገው ፍልሚያ ይጎዳል እንጂ ለአገሪቱ አይጠቅማትም " - የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
በኦሮሚያ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ መድረክ ከታህሳስ 7 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ በአዳማ ከተማ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
ማህበረሰቡ በአጀንዳ ልዬታ ወቅት የመረጣቸው ከ7 ሺሕ በላይ ተወካዮች እንደሚገኙ፣ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ በቀጣዩ ሳምንት እንደሚጠናቀቅ በቦታው የተገኙት ኮሚሽነር መሐመድ ድሪር ተናግረዋል።
ኮሚሽነር መሐመድ ድሪር ምን አሉ?
“ ኮሚሽኑ አሁን በአጠቃላይ በአገራቱ ያለውን ሁኔታ ወደ ተሻለ ሰላም ለማድረስ የጸና፣ ዴሞክራሲያዊ፣ የመመካከር ባህልን ያዳበረ ማህበረሰብ እንዲኖረን እየሰራ ይገኛል።
ላለፉት ሦስት ዓመታት በ10 ክሌሎች፣ ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን ስራችንን ስንሰራ ቆይተናል። አሁን ደግሞ ኦሮሚያም ክልልም እንዲሁም በአማራ ክልል ሥራው ተጀምሯል።
ኦሮሚያ ውስጥ ሆነን መናገር የምንችለው 7,000 የተለያዩ የኦሮሚያ የማህበረሰብ ክፍሎች ከዚህኛው በፊት በተሳታፊ ልዬታ ውስጥ ህዝቡ የመረጣቸው ተወካዮችን እናገኛለን።
በቀጣዩ ሳምንት የምንሰራቸው ሥራዎች ለሰላም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ብለን እናምናለን። በሂደቱ የሚሳተፉ በሙሉ በነቂስ ወጥተው እንዲሳተፉ ጥሪ አቀርባለሁ።
በትግራይ የተካሄደው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በመሠረቱ እንዲጸና እና ክልሉ ደግሞ ኮሚሽኑ ሥራውን እንዲጀምር ፍላጎቱ እንደሆነ በዚሁ አጋጣሚ እንገልጻለን " ብለዋል።
በኦሮሚያ ክልል የሚካሄደውን አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በተመለከተ ተጠይቀው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ምን አሉ ?
° ኮሚሽኑ ሰዎችን አይመርጥም።
° በማህበረሰብ፣ ክልል፣ አገር፣ ከተማ ያሉ ዜጎች የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች አሏቸው። የማህበረሰብ ክፍሎቹን በአሰራር ዜዬ ለይተናል።
° አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የሚገፉ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ በግጮቶች ምክንያት ከቄያቸው የተፈናቀሉ፣ በሌላ አካባቢ ሰቆቃቸውን የሚያዩ ዜጎችም አሉ። እነርሱም እንዲሳፉ ነው የሚደረጉት።
° ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ሳይቀሩ። ከዚህ በፊት የፓለቲካ ፓርቲዎች ጥርጣሬዎች ነበሯቸው ከዚያ ጥርጣሬ የወጡ በርካታ የፓለቲካ ፓርቲዎች በሂደቱ ውስጥ እየተሳተፉ ነው። አሁንም ልዩነት ያላቸው እንዳሉ እናውቃለን። ለእነርሱም ጥሪያችንን እያቀረብን እንገኛለን።
ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ያለውን ሁነት በተመለከተ ምን አሉ ?
" ግጭቶች ባሉባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች (ለምሳሌ በምዕራብ ወለጋ የነበረውን ሁኔታ ሁላትንም የማንስተው ነው) ጅማ ላይ መጥተው ተወካዮቻቸውን መርጠው፣ በሰላም ወደ አካባቢያቸው ተመልሰዋል እነርሱ ናቸው የሚሳተፉት።
እየተሟላ ያለ ሂደት እየሰራን ነው። በኦሮሚያ ውስጥ አሁን ያለውን ሰላም ቸር አምላክ ያጽናልን። ሌሎች ብረት ያነሱ ከመንግስት ጋር ግጭት ያላቸው ወገኖችም ወንድሞቻቸው እንደተመለሱት ሁሉ ሰላምን ተቀብለው ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ እንፍታ።
በመሳሪያ የሚደረገው ፍልሚያ ይጎዳል እንጂ ለአገሪቱ አይጠቅማትም ብለው የወሰኑ ወገኖች አሉ። ለሌሎችም ይሄንኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ መድረክ ከታህሳስ 7 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ በአዳማ ከተማ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
ማህበረሰቡ በአጀንዳ ልዬታ ወቅት የመረጣቸው ከ7 ሺሕ በላይ ተወካዮች እንደሚገኙ፣ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ በቀጣዩ ሳምንት እንደሚጠናቀቅ በቦታው የተገኙት ኮሚሽነር መሐመድ ድሪር ተናግረዋል።
ኮሚሽነር መሐመድ ድሪር ምን አሉ?
“ ኮሚሽኑ አሁን በአጠቃላይ በአገራቱ ያለውን ሁኔታ ወደ ተሻለ ሰላም ለማድረስ የጸና፣ ዴሞክራሲያዊ፣ የመመካከር ባህልን ያዳበረ ማህበረሰብ እንዲኖረን እየሰራ ይገኛል።
ላለፉት ሦስት ዓመታት በ10 ክሌሎች፣ ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን ስራችንን ስንሰራ ቆይተናል። አሁን ደግሞ ኦሮሚያም ክልልም እንዲሁም በአማራ ክልል ሥራው ተጀምሯል።
ኦሮሚያ ውስጥ ሆነን መናገር የምንችለው 7,000 የተለያዩ የኦሮሚያ የማህበረሰብ ክፍሎች ከዚህኛው በፊት በተሳታፊ ልዬታ ውስጥ ህዝቡ የመረጣቸው ተወካዮችን እናገኛለን።
በቀጣዩ ሳምንት የምንሰራቸው ሥራዎች ለሰላም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ብለን እናምናለን። በሂደቱ የሚሳተፉ በሙሉ በነቂስ ወጥተው እንዲሳተፉ ጥሪ አቀርባለሁ።
በትግራይ የተካሄደው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በመሠረቱ እንዲጸና እና ክልሉ ደግሞ ኮሚሽኑ ሥራውን እንዲጀምር ፍላጎቱ እንደሆነ በዚሁ አጋጣሚ እንገልጻለን " ብለዋል።
በኦሮሚያ ክልል የሚካሄደውን አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት በተመለከተ ተጠይቀው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ምን አሉ ?
° ኮሚሽኑ ሰዎችን አይመርጥም።
° በማህበረሰብ፣ ክልል፣ አገር፣ ከተማ ያሉ ዜጎች የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች አሏቸው። የማህበረሰብ ክፍሎቹን በአሰራር ዜዬ ለይተናል።
° አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የሚገፉ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ በግጮቶች ምክንያት ከቄያቸው የተፈናቀሉ፣ በሌላ አካባቢ ሰቆቃቸውን የሚያዩ ዜጎችም አሉ። እነርሱም እንዲሳፉ ነው የሚደረጉት።
° ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ሳይቀሩ። ከዚህ በፊት የፓለቲካ ፓርቲዎች ጥርጣሬዎች ነበሯቸው ከዚያ ጥርጣሬ የወጡ በርካታ የፓለቲካ ፓርቲዎች በሂደቱ ውስጥ እየተሳተፉ ነው። አሁንም ልዩነት ያላቸው እንዳሉ እናውቃለን። ለእነርሱም ጥሪያችንን እያቀረብን እንገኛለን።
ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ያለውን ሁነት በተመለከተ ምን አሉ ?
" ግጭቶች ባሉባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች (ለምሳሌ በምዕራብ ወለጋ የነበረውን ሁኔታ ሁላትንም የማንስተው ነው) ጅማ ላይ መጥተው ተወካዮቻቸውን መርጠው፣ በሰላም ወደ አካባቢያቸው ተመልሰዋል እነርሱ ናቸው የሚሳተፉት።
እየተሟላ ያለ ሂደት እየሰራን ነው። በኦሮሚያ ውስጥ አሁን ያለውን ሰላም ቸር አምላክ ያጽናልን። ሌሎች ብረት ያነሱ ከመንግስት ጋር ግጭት ያላቸው ወገኖችም ወንድሞቻቸው እንደተመለሱት ሁሉ ሰላምን ተቀብለው ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ እንፍታ።
በመሳሪያ የሚደረገው ፍልሚያ ይጎዳል እንጂ ለአገሪቱ አይጠቅማትም ብለው የወሰኑ ወገኖች አሉ። ለሌሎችም ይሄንኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Democracy👏
" የህዝቤን ውሳኔ አከብራለሁ " - በምርጫ የተሸነፉት ባውሚያ
አፍሪካ ውስጥ የተረጋጋ ምርጫና የስልጣን ሽግግር ከሚደረግባቸው ሀገራት አንዷ ጋና ናት።
ሀገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አካሂዳለች።
ለውድድር የቀረቡትም ተቃዋሚው የናሽናል ዴሞክራቲክ ኮንግረስ ፓርቲው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ እና የአሁን የገዢው ኒው ፓትርዮቲክ ፓርቲ ዕጩና የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት መሃሙዱ ባውሚያ ናቸው።
ውጤት ?
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ የገዢውን ፓርቲና የአሁኑ ምክትል ፕሬዜዳንት ባውሚያን አሸንፈዋቸዋል።
በምርጫው የተሸነፉት የገዢው ፓርቲ ዕጩ ለተፎካካሪያቸው " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
ምርጫውን የተሸነፉት የገዢው ዕጩ ባውሚያ ህዝባቸውን / ጋናውያንን ለለውጥ የሰጡትን ድምጽ እና ውሳኔ እንደሚያከብሩ ተናግረዋል።
" የጋና ፕሬዜዳንት ሆነው ለተመረጡት የተከበሩ ጆን ማሃማ ስልክ ደውዬ እንኳን ደስ አለህ ብዬዋለሁ " ሲሉም ገልጸዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ምርጫውን በማሸነፋቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው በሀገሪቱ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ከዚህ ቀደም እ.ኤ አ. ከሃምሌ 2012 እስከ ጥር 2017 ሀገሪቱን መርተዋል።
የምርጫው ውጤት ለሁለት ስልጣን ዘመን የቆየው የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ገዢ ፓርቲ ማብቂያ ሆኗል።
ባለፉት የስልጣን ዘመናት ጋና አይታ የማይታውቀው የኢኮኖሚ ቀውስ እንዳጋጠማት ፣ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እንዲሁም ከፍተኛ ዕዳ ጉድለት እንደተመዘገበ ተገልጿል።
ህዝቡም በተለይ ለተሻለ የኢኮኖሚ ለውጥ ፤ ያለው የከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ መፍትሄ እንዲያገኝ በማሰብ የገዢውን ፓርቲ ዕጩ በድምጹ በመቅጣት ተቀናቃኙን የቀድሞውን ፕሬዜዳንት ወደ ቢሮ ለመመለስ እንደወሰነ ተመላክቷል።
የሀገሪቱ ምርጫ ትልቁ ማጠንጠኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንደነበሩ ተሰምቷል።
አጠቃላይ የምርጫው ውጤት ግፋ ቢል ማክሰኞ ይፋ ይደረጋል።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ለምን ምርጫ አልተወዳደሩም ?
በጋና የፕሬዜዳንቱ ስልጣን ገደብ አለው።
ሁለት የስልጣን ዘመን አሸንፎ ሀገር ከመራ ለሌላ የስልጣን ዘመን " ልወዳደር " ቢል አይፈቀድለትም።
በዚህም ሀገር ለመምራት የሚፈቀድላቸው የስልጣን ዘመን ገደቡ ላይ ስለደረሰና መወዳደር ስለማይችሉ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ነው የተወዳደሩት።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ወንበሩን ለሌላ የሀገራቸው ልጅ ያስረክባሉ።
#Ghana
#Democracy #Election
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" የህዝቤን ውሳኔ አከብራለሁ " - በምርጫ የተሸነፉት ባውሚያ
አፍሪካ ውስጥ የተረጋጋ ምርጫና የስልጣን ሽግግር ከሚደረግባቸው ሀገራት አንዷ ጋና ናት።
ሀገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አካሂዳለች።
ለውድድር የቀረቡትም ተቃዋሚው የናሽናል ዴሞክራቲክ ኮንግረስ ፓርቲው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ እና የአሁን የገዢው ኒው ፓትርዮቲክ ፓርቲ ዕጩና የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት መሃሙዱ ባውሚያ ናቸው።
ውጤት ?
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ የገዢውን ፓርቲና የአሁኑ ምክትል ፕሬዜዳንት ባውሚያን አሸንፈዋቸዋል።
በምርጫው የተሸነፉት የገዢው ፓርቲ ዕጩ ለተፎካካሪያቸው " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
ምርጫውን የተሸነፉት የገዢው ዕጩ ባውሚያ ህዝባቸውን / ጋናውያንን ለለውጥ የሰጡትን ድምጽ እና ውሳኔ እንደሚያከብሩ ተናግረዋል።
" የጋና ፕሬዜዳንት ሆነው ለተመረጡት የተከበሩ ጆን ማሃማ ስልክ ደውዬ እንኳን ደስ አለህ ብዬዋለሁ " ሲሉም ገልጸዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ምርጫውን በማሸነፋቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው በሀገሪቱ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ከዚህ ቀደም እ.ኤ አ. ከሃምሌ 2012 እስከ ጥር 2017 ሀገሪቱን መርተዋል።
የምርጫው ውጤት ለሁለት ስልጣን ዘመን የቆየው የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ገዢ ፓርቲ ማብቂያ ሆኗል።
ባለፉት የስልጣን ዘመናት ጋና አይታ የማይታውቀው የኢኮኖሚ ቀውስ እንዳጋጠማት ፣ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እንዲሁም ከፍተኛ ዕዳ ጉድለት እንደተመዘገበ ተገልጿል።
ህዝቡም በተለይ ለተሻለ የኢኮኖሚ ለውጥ ፤ ያለው የከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ መፍትሄ እንዲያገኝ በማሰብ የገዢውን ፓርቲ ዕጩ በድምጹ በመቅጣት ተቀናቃኙን የቀድሞውን ፕሬዜዳንት ወደ ቢሮ ለመመለስ እንደወሰነ ተመላክቷል።
የሀገሪቱ ምርጫ ትልቁ ማጠንጠኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንደነበሩ ተሰምቷል።
አጠቃላይ የምርጫው ውጤት ግፋ ቢል ማክሰኞ ይፋ ይደረጋል።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ለምን ምርጫ አልተወዳደሩም ?
በጋና የፕሬዜዳንቱ ስልጣን ገደብ አለው።
ሁለት የስልጣን ዘመን አሸንፎ ሀገር ከመራ ለሌላ የስልጣን ዘመን " ልወዳደር " ቢል አይፈቀድለትም።
በዚህም ሀገር ለመምራት የሚፈቀድላቸው የስልጣን ዘመን ገደቡ ላይ ስለደረሰና መወዳደር ስለማይችሉ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ነው የተወዳደሩት።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ወንበሩን ለሌላ የሀገራቸው ልጅ ያስረክባሉ።
#Ghana
#Democracy #Election
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#TecnoAI
ቴክኖ ኢትዮጵያ ያዘጋጀው በሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል እጅግ በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል፡፡ ከፍ ያሉ የአርቴፊሻል ቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ይዞ ብቅ ካለው ከቴክኖ ኤ አይ በተጨማሪ አጅግ የተራቀቁ አዳዲስ የቴክኖ የምርት ውጤቶች ለዕይታ ይፋ ይሆናሉ፡፡
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et
ቴክኖ ኢትዮጵያ ያዘጋጀው በሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል እጅግ በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል፡፡ ከፍ ያሉ የአርቴፊሻል ቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ይዞ ብቅ ካለው ከቴክኖ ኤ አይ በተጨማሪ አጅግ የተራቀቁ አዳዲስ የቴክኖ የምርት ውጤቶች ለዕይታ ይፋ ይሆናሉ፡፡
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et