TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " አሁንም አንዳንድ የቤት ባለቤቶች ወደ ቤታቸው ለመግባት ምንም እንቅስቃሴ እያደረጉ አይደለም ፤ ይህ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነው " - ኮርፖሬሽኑ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ ጊዜያት በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች አስመልክቶ እስከ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ድረስ የቤት ባለቤቶቹ ወደ ቤታቸው የማይገቡ ከሆነ በህግ አግባብ ውል…
#የጋራመኖሪያቤቶች

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ ጊዜያት በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች የቤት ባለቤቶቹ እንዲገቡባቸው የሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነገ ህዳር 30/2017 ዓ/ም ያበቃል።

ኮርፖሬሽኑ በሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የቤት ባለቤቶቹ ወደ ቤታቸው የማይገቡ ከሆነ በህግ አግባብ ውል የሚቋረጥ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።

ቀደም ብሎ የተሰጠው ገደብ ጥምቅት 30 የነበረ ቢሆንም ቤታቸውን አድሰው ለመግባት የጊዜ እጥረት ላጋጠማቸው የቤት ባለቤቶች ተብሎ እስከ ህዳር 30 ተራዝሞ ነበር።

ይህ ለመጨረሻ ጊዜ የተሰጠ የጊዜ ገደብ መሆኑን ኮርፖሬሽኑ ገልጾ ነበር።

ቀኑ ነገ ሰኞ ያበቃል።

በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይገቡ ነዋሪዎች የሽያጭ ውላቸው የሚቋረጥ እና በቤታቸው ውስጥ ለሚፈጸም ማንኛውም ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂ እንደሚሆኑ መግለጹ ይታወሳል።

ከዘህ ቀደም ኮርፖሬሽኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥቶት በነበረው ማብራሪያ ምን ነበር ያለው ?

- ማስታወቂያው የወጣበት ዋናው ምክንያት ሰዎች ‘ ተቸገርን፣ ክፍት በሆኑ ቤቶች ወንጀል እየተሰራ ነው፣ እየተዘረፍን ነው፣ ሴቶች እየተደፈሩብን ነው፣ የጸጥታ ስጋትም እየሆኑብን ’ ብለው ቅሬታ ስላቀረቡ እንደሆነ፤

- ቤቶቹ ቼክ ሲደረጉ እጣ የወጣባቸው ፤ ውል የተፈጸመባቸው፣ በጨረታ የተላለፉ ነገር ግን ሰው ያልገባባቸው እንደሆኑ፤

- ነዋሪው በከፍተኛ ሁኔታ እየተቸገረ ፤ የጸጥታ ኃይሉም ጥያቄ እያነሳ እንደሆነ ፤

- " የቤት ባለቤቶች ቤታችሁን አድሳችሁ ግቡ " የተባለውም የግድ እራሳቸውን እንዳይደለ ፤ ቢፈልጉ አድሶ ማከራየት መብታቸው እንደሆነ፤

- የራሳቸው ቤት እስከሆነ ድረስ አድሰው ማከራት ከፈለጉ ደግሞ እራሳቸው መግባት መብታቸው እንደሆነ ዞሮ ዞሮ ሰው በቤቱ ሊኖርበት እንደሚገባ ማብራራቱ ይታወሳል።


#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ
በብርሃን ቅፅበት ካርድዎን በእጅዎ ያስገቡ!

#ልዩ_የኤቲኤም_ካርድ #liyuatmcard #atmcard #berhanbank #bank #finance
#Stressfreebanking #bankinethiopia

ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
➡️ Facebook
➡️ Telegram
➡️ Instagram
➡️ Twitter
➡️ LinkedIn
➡️ YouTube
#TecnoAI

የፈለጉትን ቢጠይቁት የሚመልስ እንደ እርሶ ሆኖ ስራዎትን የሚከውን የቀዱትን ድምፅ በፅሁፍ ቀይሮ የሚሰጥ፣ አስተርጓሚ ሆኖ ስራዎትን የሚያቀል፣ የሂሳብ ስራዎን በራሱ የሚከውን አባ መላ የተባለለት ቴክኖ ኤ አይ እየመጣ ነው፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡

https://www.tiktok.com/@tecnoet

@tecno_et @tecno_et
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA " እውነት ነው " - ትራምፕ ዶናልድ ትራምፕ ሰነድ አልባ ስደተኞችን በገፍ በጅምላ ከሀገር ለማባረር ጦሩን (መከላከያውን) ሊጠቀሙ ይችላሉ ተብሏል። ተመራጩ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፤ በምርጫ ዘመቻ ወቅት ለደጋፊዎቻቸው በገቡት ቃል መሰረት ሰነድ የሌላቸውን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደየመጡበት ሀገር ያባርራሉ። ለዚህም በመላ ሀገሪቱ አስቸኳይ የአደጋ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ እንደሚችሉ…
" ቤተሰብ መበታተን አልፈልግም ፤ ቤተሰቦች የማይለያዩበት ብቸኛው መንገድ ሁሉንም አንድ ላይ ከአገር ማባረር ነው " - ትራምፕ

ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከNBC ጋር ቆይታ አድርገው ነበር።

በዚህም ቆይታቸው ከስድተኞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን አንስተዋል።

ምን አሉ ?

ትራምፕ ወላጆቻቸው በውጭ አገራት ቢወለዱም በአሜሪካ የተወለዱ ልጆቻቸው ዜግነት የሚያገኙበትን መብት እሽራለሁ ብለዋል።

ወላጆቻቸው ሌላ ቦታ ቢወለዱም በአሜሪካ የሚወልዷቸው ልጆች የአሜሪካ ፓስፖርት የማግኘት መብት የሚሰጠውን በመወለድ የሚገኝ የዜግነት መብት ለማስቆም ፕሬዚዳንታዊ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፉ አሳውቀዋል።

በተለያዩ ምክንያቶች ተሰደው ወደ አሜሪካ የሄዱ ሰዎች የመኖሪያም ሆነ የዜግነት መብት ባያገኙም አሜሪካ ውስጥ የወለዷቸው ልጆች ዜግነትን ማግኘት ይችላሉ ታዲያ ትራምፕ ስራ ሲጀምሩ ይህንን ነው የሚሽሩት።

ሆኖም በልጅነታቸው ወደ አሜሪካ የመጡ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ለመርዳት ከዴሞክራቶች ጋር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

🇺🇸 በመወለድ የሚገኝ የዜግነት መብት የአሜሪካ ህገ መንግሥት አንቀጽ 14ን መሰረት ያደረገ ነው። '' ማንኛውም አሜሪካ ውስጥ የተወለደ ወይም ተገቢውን ግዴታዎች የተወጣ ሰው የአሜሪካ ዜጋ የመሆን ሙሉ መብት አለው '' ይላል።

በሌላ በኩል ፤ ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው የቤተሰብ አባላት ያላቸውን ጨምሮ ህጋዊ ሰነዶች ያላሟሉ ስደተኞችን ከአገር ለማባረር የገቡትን ቃል ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

" ቤተሰብ መበተታተን አልፈልግም " ያሉት ትራምፕ " ስለዚህ ቤተሰቦች የማይለያዩበት ብቸኛው መንገድ ሁሉንም አንድ ላይ ከአገር ማባረር ነው " ብለዋል።

ትራምፕ በአንድ ወቅት ለመሰረዝ ሞክረው የነበረውን ወደ አሜሪካ ብቻቸውን ለሚመጡ ህጻናት ከለላ የሰጠውን የኦባማ 'ዲፈርድ አክሽን ፎር ቻይልድ ሁድ አራይቫልስ' በተሰኘው ፕሮግራም የታቀፉትን በተመለከተ ከምክር ቤቱ ጋር አብሬ እሰራለሁ ብለዋል።

" ከዴሞክራቶች ጋር በአንድ ዕቅድ ላይ እሰራለሁ " ያሉት ትራምፕ ከነዚህ ስደተኞች መካከል ጥቂቶች ጥሩ ስራ የያዙ በንግድ ላይ የተሰማሩም አሉ ሲሉ አክለዋል።

መረጃውን ኤንቢሲን ዋቢ በማድረግ ያጋራው ቢቢሲ ነው።

#USA #MASSDEPORTATION

@tikvahethiopia
#MoE : በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳወቀ።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምግብ በጀት ማስተካከያ መደረጉንም ይፋ አድርጓል።

" ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየሰሩ ነው " ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

ወቅታዊውን የምግብ ዋጋ መጨመር መነሻ በማድረግ ትምህርት ሚኒስቴር ጥናት ማድረጉን በጥናቱ ውጤት መነሻነትም የከፍትኛ ትምህርት ተቋማት / የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምግብ በጀት በቀን ወደ 100 ብር ከፍ እንዲል መደረጉን አሳውቋል።

በተደረገው የበጀት ማሻሻያ መሰረት በተቋማቱ የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን ይሰራል ተብሏል።

በአዲሱ የበጀት ተመን መሰረት ለዩኒቨርስቲዎቹ ባላቸው ተማሪ ቁጥር ልክ ገንዘቡ እንደሚለቀቅላቸው ተጠቁሟል።

ዩኒቨርሲቲዎች ከዚህ ቀደም በቀን አንድ ተማሪ ቁርስ፣ ምሳ እና እራት ለመመገብ በመንግሥት የሚመድብላቸው 22 ብር በጀት ብቻ እንደነበር ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE : በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳወቀ። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምግብ በጀት ማስተካከያ መደረጉንም ይፋ አድርጓል። " ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየሰሩ ነው " ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። ወቅታዊውን የምግብ ዋጋ መጨመር መነሻ በማድረግ ትምህርት ሚኒስቴር…
የምግብ ዋጋ ጣሪያ መንካት 💥

ዛሬ ላይ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የቀን የምግብ ወጪ የሚመደበው ገንዘብ እንዲጨምር ተደርጓል።

ይህ የሆነው ደግሞ የምግብ ዋጋ በመጨመሩ ነው።

በፊት ለአንድ ተማሪ ይመደብ የነበረው 22 ብር  ዛሬ ላይ ወደ 100 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።

የተቋማት የምግብ ሜኑም ተመሳሳይ እንዲሆን ተወስኗል።

በፊት በፊት ምንም እንኳን ከግቢ ግቢ ጥራቱ ቢለያይም የዩኒቨርሲቲ ካፌዎች ከዓመት ዓመት በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ያለ ሰቀቀን መግበው ያስመርቁ ነበር።

የጥራቱ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ ካለው የተማሪዎች ቁጥር ብዛት አንጻር ተቋማት በየዕለቱ ያለ ችግር ተማሪዎችን የተለያየ አይነት ምግብ ነበር የሚመግቡት።

ዛሬ ላይ ያለው የምግብ ዋጋ መናር ግን ፈተና ሆኗል። ለዚህም የመስላል የቀን የተማሪዎች የምግብ ዋጋ ላይ ማስተካከያ የተደረገው።

ሌላው ግን በአጭር አመታት በሀገሪቱ የታየው የምግብ ዋጋ መጨመር ግርምትን የሚያጭር ፤ ልብን ቀጥ የሚያደርግ ነው።

ከዛሬ 4 እና 5 ዓመት በፊት በዩኒቨርሲቲዎች የነበሩ ተማሪዎች በተለይም ደግሞ ግቢ መመገብ የማይፈልጉ ምግብ በርካሽ ዋጋ ያገኙ ነበር።

500 ብር የማትሞላውን ወርሃዊ ኮስት ተቀብለው እዛ ላይ ከቤተሰብ የሚላከውን ጨምረው ወጣ ብለው የምግብ ኮንትራት ይዘው የሚበሉ በርካቶች ነበሩ።

ከኮቪድ በፊት እጅግ ጥሩና ፅድት ብሎ የተዘጋጀ በየአይነቱ በየዩኒቨርሲቲው ዙሪያ ባሉ መንደሮች በኮንትራት ከ12 ብር እስከ 17 ብር ድረስ ይገኝ ነበር።

የስጋ ነክ ምግቦችንም ከ23 ብር 35 ብር ድረስ ማግኘት ይቻል ነበር።

እንጅራው ወጡም ፍጹም ጤነኛ።

በግቢ ባሉ የተለያዩ የኢንተርፕራይዝ ካፌዎችም ምግብ በቅናሽ ማግኘት ቀላል ነበር።

ዛሬ ላይ የበፊቱ የበየአይነቱ ዋጋ ደረቅ እንጀራ ለመግዛት አይበቃም።

በበፊቱ የስጋ ነክ ምግቦች ዋጋ ዛሬ ላይ ወጥቼ ልብላ ማለት ቅንጦት ነው፤ አይታሰብም።

ይህ እንግዴ የዛሬ 4 ፣ 5 ፣ 6 ዓመት ታሪክ ነው የረጅም ጊዜ መስሎ የሚወራው።

በአጭር አመታት የታየው የምግብ ዋጋ መተኮስ የሚያስደንግጥ ነው።

ምንም እንኳን በኮስት ከተቋማት የሚገኘው ብር ትንሽ ቢሆንም እሱ ላይ የቤተሰብ ትንሽ ብር ከተጨመረበት ዘና ብሎ ያለሰቀቀን ወር ሙሉ ውጭ መመገብ ይቻል ነበር።

ዛሬ ላይ በሀገራችን ያልጨመረ ነገር ባይኖርም ለመኖር መሰረታዊ ያሆነው የምግብ ዋጋ ተተኩሶ የደረሰበት ደረጃ ብዙዎችን የሚያስጨንቅ ነው።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ትላንት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በቻይና ምድር የመጀመሪያዋን ደብር በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ አከናውናለች።

ለሐዋርያዊ አገልግሎት ቻይና እንደሚገኙት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቻይና ምድር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጀመርያዋን ቤተ ክርስቲያን ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ብለው በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ በመፈጸም ምዕምናንን አቁርበዋል።

በቻይና የመጀመሪያው አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆንም ሾመዋል።

ከቻይና ክፍላተ ግዛቶች የተሰባሰቡ ምዕመናን ፣ ቻይናውያንና ትውልደ ቻይናውያን በሥርዓተ ቅዳሴው ተሳፍተዋል።

ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም !

Photo Credit - EOTC Far East Diocese & ETOC TV

@tikvahethiopia