TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
🔴 " የቤንዚን አቅርቦት ባለባቸው ማደያዎች የፀጥታ መዋቅር እየተቆጣጠረ ተገቢዉ ስርጭት እየተካሄደ ነዉ " - ግብረ ኃይሉ
🔵 " ምንም እንኳን ማደያዎች አካባቢ ያለው ግብግብ ቢሻሻልም አሁንም ተሰልፎ መዋል ነው " - ነዋሪዎች
በሲዳማ ክልል፣ በሀዋሳ ከተማ የነበረዉን ሕገወጥ የቤንዚን ንግድ በተመለከተ ተደጋጋሚ መረጃዎችን መለዋወጣችን ይታወሳል።
ከሰሞኑን የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነ መገለጹም የሚዘነጋ አይደለም።
ምንም እንኳን የመፍትሄ አቅጣጫዎች ቢቀመጡም እርምጃዎችም እየተወሰዱ እንደሆነ ቢነገርም አሁንም ያልተቀረፉ ችግሮች መኖራቸውን መታዘቡን የሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ከስፍራው ያለውን ሁኔታ አድርሶናል።
በክልሉ የነዳጅ ሥርጭቱን ለመቆጣጠር ግብረ-ኃይል መቋቋሙን ተከትሎ የከተማዉ ንግድ ኃላፊ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን ፤ ሁለት ከፍተኛ ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን፤ ሦስት ማደያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱንና በአጠቃላይ ከ8 ሺህ ሊትር በላይ በሕገወጥ መንገድ የተከማቸ ቤንዚን መያዙ ተገልጿል።
ሆኖም ግን ግብረ-ኃይሉ ከቀናት በፊት ባካሄደው ውይይት ላይ " ከዚህ ቀደም ተሽከሪካሪ ተለይቶ ይደለደል የነበረዉ አሰራር ከአሁን ጀምሮ አይኖርም " ተብሎ ቢገለጽም ይህ የተሽከሪካሪ ምደባ አሁንም መቀጠሉን ታዝበናል።
ይህ ለምን ሆነ ? ብለን ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ መምሪያ ኃላፊ ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን " ምደባዉን ማስቆማችን አይቀርም አሁን ላይ ባለዉ እጥረት ለቁጥጥር ስለሚያስቸግር ነዉ ያላቆምነዉ። ከአራት በላይ ማደያዎች አቅርቦት ሲኖር ምደባዉን እናስቆማለን " የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።
በቀጣይም በባለሙያዎች እና ማደያዎች ላይ የተጀመረው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን የተረጋጋ የቤንዚን ስርጭት እስኪፈጠር ግብረሃይሉ በትኩረት ይሰራል ተብሏል።
በተጨማሪም ግብረኃይሉ፦
- የቤንዚን አቅርቦት ባለባቸው ማደያዎች የፀጥታ መዋቅር እየተቆጣጠረ ተገቢዉ ስርጭት እየተካሄደ ነዉ።
- በሕገወጥ ግብይትና ተባባሪነት የተጠረጠሩ 34 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዉለዋል።
- ለጥቁር ገበያዉ አመላላሽ የነበሩ ከ20 በላይ ተሽከርካሪዎች ተይዘዋል።
- የፀጥታ ሃይሎችና በእንግድነት ወደ ከተማዋ የሚገቡ ሰዎች እየተጣሩ ያለ ሰልፍ እንዲቀዱ ይደረጋል ... ብሏል።
ማደያዎች ምን አሉ ? ማደያዎች ግብረኃይሉ በሚመራው አካሄድ ስርጭት እየተካሄደ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
አሽከርካሪዎች እና ነዋሪዎች ምን ይላሉ ?
ያነጋገርናቸው አሽከርካሪዎች በማደያዎች አከባቢ ይስተዋሉ የነበሩ ግብግቦች መቀነሳቸውንና አሁን ላይ እየተቀዳ ያለዉ በተራ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
ሆኖም ግን የባጃጅ አሽከርካሪዎች " ከሰልፉ ብዛት የተነሳ አሁንም ተሰልፎ ዉሎ አለመቅዳት ስላለ፥ አይደለም የምንሰራበት ተሰልፈን ዉለን 12:ዐዐ ሲዘጋ ወደቤት መመለሻ እያጣን ነዉ " ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
አሁንም ቢሆን የቤንዚን ሰልፉ በጣም ረጃጅም መሆኑን የገለጹት አሽከርካሪዎች " የታክሲ አገልግሎት ሰጥተን ቤተሰቦቻችንን የምንመራ ሰዎች ለከፍተኛ ችግር ተዳርገናል " ሲሉ ሁኔታውን ገልጸዋል።
ቁጥጥሩ ወቅታዊ እንዳይሆን ስጋት ያላቸው አሽከርካሪዎቹ የዕለቱ የቤንዚን ስርጭት ከተዘጋ በኋላ በአንዳንድ ማደያዎች ያለ ተራ የመቅዳት ተግባራት እንደሚስተዋሉ ጠቁመዋል።
የሞተር ባለንበረቶችም እንደልብ ነዳጅ ማግኘትና መንቀሳቀስ አሁንም እንዳልተቻለ ፤ እርምጃዎች ተወሰዱ ከተባለ በኃላ በተጨባጭ የታየ ለውጥ መመልከት እንዳልሻሉ ጠቁመዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡ ሌሎች የከተማው ነዋሪዎች " በማደያዎች አከባቢ መሻሻሎች ቢኖሩም ችግሩ አልተቀረፈም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ መቀዛቀዞች ይስተዋላሉ " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
🔴 " የቤንዚን አቅርቦት ባለባቸው ማደያዎች የፀጥታ መዋቅር እየተቆጣጠረ ተገቢዉ ስርጭት እየተካሄደ ነዉ " - ግብረ ኃይሉ
🔵 " ምንም እንኳን ማደያዎች አካባቢ ያለው ግብግብ ቢሻሻልም አሁንም ተሰልፎ መዋል ነው " - ነዋሪዎች
በሲዳማ ክልል፣ በሀዋሳ ከተማ የነበረዉን ሕገወጥ የቤንዚን ንግድ በተመለከተ ተደጋጋሚ መረጃዎችን መለዋወጣችን ይታወሳል።
ከሰሞኑን የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነ መገለጹም የሚዘነጋ አይደለም።
ምንም እንኳን የመፍትሄ አቅጣጫዎች ቢቀመጡም እርምጃዎችም እየተወሰዱ እንደሆነ ቢነገርም አሁንም ያልተቀረፉ ችግሮች መኖራቸውን መታዘቡን የሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ከስፍራው ያለውን ሁኔታ አድርሶናል።
በክልሉ የነዳጅ ሥርጭቱን ለመቆጣጠር ግብረ-ኃይል መቋቋሙን ተከትሎ የከተማዉ ንግድ ኃላፊ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸውን ፤ ሁለት ከፍተኛ ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን፤ ሦስት ማደያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱንና በአጠቃላይ ከ8 ሺህ ሊትር በላይ በሕገወጥ መንገድ የተከማቸ ቤንዚን መያዙ ተገልጿል።
ሆኖም ግን ግብረ-ኃይሉ ከቀናት በፊት ባካሄደው ውይይት ላይ " ከዚህ ቀደም ተሽከሪካሪ ተለይቶ ይደለደል የነበረዉ አሰራር ከአሁን ጀምሮ አይኖርም " ተብሎ ቢገለጽም ይህ የተሽከሪካሪ ምደባ አሁንም መቀጠሉን ታዝበናል።
ይህ ለምን ሆነ ? ብለን ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ መምሪያ ኃላፊ ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን " ምደባዉን ማስቆማችን አይቀርም አሁን ላይ ባለዉ እጥረት ለቁጥጥር ስለሚያስቸግር ነዉ ያላቆምነዉ። ከአራት በላይ ማደያዎች አቅርቦት ሲኖር ምደባዉን እናስቆማለን " የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።
በቀጣይም በባለሙያዎች እና ማደያዎች ላይ የተጀመረው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን የተረጋጋ የቤንዚን ስርጭት እስኪፈጠር ግብረሃይሉ በትኩረት ይሰራል ተብሏል።
በተጨማሪም ግብረኃይሉ፦
- የቤንዚን አቅርቦት ባለባቸው ማደያዎች የፀጥታ መዋቅር እየተቆጣጠረ ተገቢዉ ስርጭት እየተካሄደ ነዉ።
- በሕገወጥ ግብይትና ተባባሪነት የተጠረጠሩ 34 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዉለዋል።
- ለጥቁር ገበያዉ አመላላሽ የነበሩ ከ20 በላይ ተሽከርካሪዎች ተይዘዋል።
- የፀጥታ ሃይሎችና በእንግድነት ወደ ከተማዋ የሚገቡ ሰዎች እየተጣሩ ያለ ሰልፍ እንዲቀዱ ይደረጋል ... ብሏል።
ማደያዎች ምን አሉ ? ማደያዎች ግብረኃይሉ በሚመራው አካሄድ ስርጭት እየተካሄደ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
አሽከርካሪዎች እና ነዋሪዎች ምን ይላሉ ?
ያነጋገርናቸው አሽከርካሪዎች በማደያዎች አከባቢ ይስተዋሉ የነበሩ ግብግቦች መቀነሳቸውንና አሁን ላይ እየተቀዳ ያለዉ በተራ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
ሆኖም ግን የባጃጅ አሽከርካሪዎች " ከሰልፉ ብዛት የተነሳ አሁንም ተሰልፎ ዉሎ አለመቅዳት ስላለ፥ አይደለም የምንሰራበት ተሰልፈን ዉለን 12:ዐዐ ሲዘጋ ወደቤት መመለሻ እያጣን ነዉ " ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
አሁንም ቢሆን የቤንዚን ሰልፉ በጣም ረጃጅም መሆኑን የገለጹት አሽከርካሪዎች " የታክሲ አገልግሎት ሰጥተን ቤተሰቦቻችንን የምንመራ ሰዎች ለከፍተኛ ችግር ተዳርገናል " ሲሉ ሁኔታውን ገልጸዋል።
ቁጥጥሩ ወቅታዊ እንዳይሆን ስጋት ያላቸው አሽከርካሪዎቹ የዕለቱ የቤንዚን ስርጭት ከተዘጋ በኋላ በአንዳንድ ማደያዎች ያለ ተራ የመቅዳት ተግባራት እንደሚስተዋሉ ጠቁመዋል።
የሞተር ባለንበረቶችም እንደልብ ነዳጅ ማግኘትና መንቀሳቀስ አሁንም እንዳልተቻለ ፤ እርምጃዎች ተወሰዱ ከተባለ በኃላ በተጨባጭ የታየ ለውጥ መመልከት እንዳልሻሉ ጠቁመዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡ ሌሎች የከተማው ነዋሪዎች " በማደያዎች አከባቢ መሻሻሎች ቢኖሩም ችግሩ አልተቀረፈም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ መቀዛቀዞች ይስተዋላሉ " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአቶ በቴ ኡርጌሳ ምርመራ ከምን ደረሰ ? “ ... ምርመራው ተጀምሯል ፤ እየቀጠለ ነው ” - ኢሰመኮ በኦሮሚያ ክልል፣ መቂ ከተማ ተገደሉትን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር አቶ በቴ ኡርጌሳን ጉዳይ በተመለከተ በርካታ መረጃዎች አድርሰናችሁ ነበር። ሰሞኑን ደግሞ ፦ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ ላይ የጀመረውን ምርመራ በደረሰበት ጫና ማቆሙን…
የፖለቲከኛ ጃል በቴ ኡርጌሳ ግድያ ምርመራ ምን ደረሰ ?
🔴 “ መረጃ የማሰባብ ሥራችን እንደቀጠለ ነው ” - ኢሰመኮ
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ፓለቲከኛ ጃል በቴ ኡርጌሳ በትውልድ ቦታቸው መቂ ከተማ በግፍ መገደላቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ ባለቤቱም ሰሞኑን ልጆቻቸውን ይዘው ወደ አሜሪካ መሄዳቸው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በወቅቱ ስለግድያው ምርመራ ጀምሮ የነበረ ሲሆን፣ በኦሮሚያ ክልል በኩል በደረሰበት ጫና ምርመራውን ማቆሙን ለክልሉ በደብዳቤ ማሳወቁ በኋላ ደግሞ እንደገና ምርመራው እንደተጀመረ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።
ምርመራው ቁሞ የነበረው፣ “ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተሳትፎ መኖሩን የሚያመለክት ምስክሮችን ማሰባሰብ ከጀመረ ከሦስት ቀናት በኋላ የምርመራው ቡድን ምርመራውን እንዲያቋርጥ በመገደዱ ” መሆኑ በወቅቱ በኢሰመኮ ደብዳቤ መጠቀሱ ተነግሮ ነበር።
የፓለቲከኛውን ግድያ ከተፈጸመ ከስድስት ወራት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን፣ የግድያው ምክንያት እውቅና ግን የተነገረ ውጤት የለም።
ስለምርመራው አሁንስ ምን አዲስ ነገር አለ ?
እንዲያው የፓለቲከኛ ጃል በቴ ኡሬጌሳ ግድያን በተመለከተ የተጀመረው ምርመራ ከምን ደረሰ ? ያለው ሂደትስ ምንድን ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)ን ጠይቋል።
ኮሚሽኑም ምርመራው እንደቀጠለ ገልጿል።
“ ሥራችንን ስናጠናቅቅ ውጤቱን ይፋ የምናደርግ ይሆናል። አሁን ግን መረጃ የማሰባብ ሥራችን እንደቀጠለ ነው ” ብሏል።
ሂደቱን በተመለከተ “ ከክልሉ የሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጋርም እየተነጋገርን ነው ” ሲል ገልጿል።
ስለግድያ የሚያደርገውን ምርመራ በተመለከተ ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም የኦሮሚያ ክልል አካላት ጋር መንገራገጭ ገጥሞት እንደነበር ይታወሳል፤ ለመሆኑ አሁን በምን ደረጃ ላይ ነው ? ችግሩ ተፈታ ወይስ አልተፈታም ? ሲልም ቲክቫህ ለኮሚሽኑ ጥያቄ አቅርቧል።
ኮሚሽኑም፣ “ ከክልሉ ጋር ያለው ግንኙኘት በተመለከተ አሁን መረጀ መስጠት አልችልም ” ከማለት ውጪ ስለግንኙነታቸው አሁናዊ ሁኔታ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥቧል።
አክሎ ደግሞ፣ “ ግን ሥራ እየሰራን ነው። አልተውንነውም ጉዳዩን ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጃል በቴ ኡርጌሳ መቂ ላይ በግፍ በተገደሉበት ወቅት በሚዲያ ቀርቦ ግድያው ' ባልታወቁ ሰዎች መፈጸሙን ' ገልጾ መርምሬ ለህዝብ ውጤቱን ይፋ አደርጋለሁ ማለቱ ይታወሳል። ይህን ካለ ወራት ቢያልፉም እስካሁን ለህዝብ የተሰጠ ግልጽ እና ተጨባጭ መረጃም ሆነ ማብራሪያ የለም።
ሁነቱን እስከመጨረሻ በመከታተል መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ መረጃ የማሰባብ ሥራችን እንደቀጠለ ነው ” - ኢሰመኮ
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ፓለቲከኛ ጃል በቴ ኡርጌሳ በትውልድ ቦታቸው መቂ ከተማ በግፍ መገደላቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ ባለቤቱም ሰሞኑን ልጆቻቸውን ይዘው ወደ አሜሪካ መሄዳቸው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በወቅቱ ስለግድያው ምርመራ ጀምሮ የነበረ ሲሆን፣ በኦሮሚያ ክልል በኩል በደረሰበት ጫና ምርመራውን ማቆሙን ለክልሉ በደብዳቤ ማሳወቁ በኋላ ደግሞ እንደገና ምርመራው እንደተጀመረ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።
ምርመራው ቁሞ የነበረው፣ “ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተሳትፎ መኖሩን የሚያመለክት ምስክሮችን ማሰባሰብ ከጀመረ ከሦስት ቀናት በኋላ የምርመራው ቡድን ምርመራውን እንዲያቋርጥ በመገደዱ ” መሆኑ በወቅቱ በኢሰመኮ ደብዳቤ መጠቀሱ ተነግሮ ነበር።
የፓለቲከኛውን ግድያ ከተፈጸመ ከስድስት ወራት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን፣ የግድያው ምክንያት እውቅና ግን የተነገረ ውጤት የለም።
ስለምርመራው አሁንስ ምን አዲስ ነገር አለ ?
እንዲያው የፓለቲከኛ ጃል በቴ ኡሬጌሳ ግድያን በተመለከተ የተጀመረው ምርመራ ከምን ደረሰ ? ያለው ሂደትስ ምንድን ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)ን ጠይቋል።
ኮሚሽኑም ምርመራው እንደቀጠለ ገልጿል።
“ ሥራችንን ስናጠናቅቅ ውጤቱን ይፋ የምናደርግ ይሆናል። አሁን ግን መረጃ የማሰባብ ሥራችን እንደቀጠለ ነው ” ብሏል።
ሂደቱን በተመለከተ “ ከክልሉ የሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጋርም እየተነጋገርን ነው ” ሲል ገልጿል።
ስለግድያ የሚያደርገውን ምርመራ በተመለከተ ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም የኦሮሚያ ክልል አካላት ጋር መንገራገጭ ገጥሞት እንደነበር ይታወሳል፤ ለመሆኑ አሁን በምን ደረጃ ላይ ነው ? ችግሩ ተፈታ ወይስ አልተፈታም ? ሲልም ቲክቫህ ለኮሚሽኑ ጥያቄ አቅርቧል።
ኮሚሽኑም፣ “ ከክልሉ ጋር ያለው ግንኙኘት በተመለከተ አሁን መረጀ መስጠት አልችልም ” ከማለት ውጪ ስለግንኙነታቸው አሁናዊ ሁኔታ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥቧል።
አክሎ ደግሞ፣ “ ግን ሥራ እየሰራን ነው። አልተውንነውም ጉዳዩን ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጃል በቴ ኡርጌሳ መቂ ላይ በግፍ በተገደሉበት ወቅት በሚዲያ ቀርቦ ግድያው ' ባልታወቁ ሰዎች መፈጸሙን ' ገልጾ መርምሬ ለህዝብ ውጤቱን ይፋ አደርጋለሁ ማለቱ ይታወሳል። ይህን ካለ ወራት ቢያልፉም እስካሁን ለህዝብ የተሰጠ ግልጽ እና ተጨባጭ መረጃም ሆነ ማብራሪያ የለም።
ሁነቱን እስከመጨረሻ በመከታተል መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ
🔴" ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ ንግድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ አረጋግጠናል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
🔵 " ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል " - ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
በህገወጥ የነዳጅ ግብይት የታየዘ ግለሰብ ነዳጁ ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስራትና እስከ 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ።
ረቂቁ ምን ይላል ?
- አዲስ የነዳጅ ምርት አከፋፋዮች ስራ ለመጀመር ቢያንስ 500 ሺህ ሊትር የነዳጅ ውጤቶች መያዝ የሚችል ማከማቻ / ዴፖ እና 4 ማደያዎችን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ያስገድዳል።
- በስራ ላይ ያሉ ማደያዎች ደግሞ አዋጁ ከሚጸድቅበት ጊዜ ጀምሮ ለአዲስ አከፋፋዮች የተጣሉትን ግዴታዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- አዲስ ጀማሪ ሆኑ ነባሮቹ በ3 ዓመታት ውስጥ ተጨማሪ 6 ማደያዎችን የመገንባት ግዴታ አለባቸው።
- የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ያከማቸ፣ ሊሸጥ ከሚገባው ሰው ቦታና የግብይት ስርዓት ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ወይም አደጋ ያስከትላሉ በተባሉ መያዣዎች ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ የተያዘው የነዳጅ ውጤት ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስርና ከብር 50 ሺህ እስከ ብር 100 ሺህ የሚደርስ ቅጣት ይፈጸምበታል።
- መንግሥት ከሚያወጣው የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ተመን ውጪ በተደጋጋሚ የመገበያየት ወንጀል እንዲሁም የነዳጅ ምርቶችን ከባዕድ ነገሮች ጋር መቀላቀል እስከ 3 ዓመት እስርና እስከ 300 ሺህ ብር ቅጣት ያስጥላል።
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ እስመለአለም ምህረቱ ምን አሉ ?
አሁን አሁን ወደነዳጅ አቅራቢነት ስራ ለመሰማራት ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ነው ብለዋል።
በድርጅቱ በተደረገው ጥናት ይህ ፍላጎት የኮንትሮባንድ ንግድ እና ከባንክ ብድር ለመወሰድ ተብሎ የሚደረግ እንደሆነ ተደርሶበታል ሲሉ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ፥ በዚህ 9 እና 10 ዓመት ውስጥ ከነበሩት 8 ወይም 9 ካምፓኒዎች አሁን 59 መድረሳቸውን ጠቁመዋል።
3ቱ የመንግሥት ገንዘብ አባክነው በፍርድ ቤት ክርክር ላይ ናቸው።
56ቱ ካምፓኒዎችን በማርኬትሼር በመደልደል ነዳጅ እየተሰጠ መሆኑን የገለጹ ሲሆን " ይህ ሁኔታ እራሱ እስካሁን ስምምነት የሌለበት ሁልጊዜ ጭቅጭቅ ያለበት ድርጊት ነው " ብለዋል።
ወደ ነዳጅ ግብይት አዲስ የሚገቡ ካምፓኒዎችን በተመለከተ ምንድነው አላማቸው ? ለምንድነው እንዲህ እያደገ የመጣው የሚለው መጠናቱን ገልጸዋል።
በጥናቱ ውጤትም " ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ ነው የተረጋገጠው " ብለዋል።
እነዚህ የነዳጅ ካምፓኒዎች ባንኮች ጋር ሄደው ብድር በሚጠይቁበት ጊዜ ባንኮቹ " ከናተ ጋር ያላቸው የሥራ አፈጻጸም ይጻፍልን " እየተባለ ደብዳቤ እንደሚጻፍ ገልጸዋል።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
° አዋጁ አላማ መንግሥት በየዓመቱ በሚሊዮን ዶላሮች የሚያወጣበትን ለነዳጅ ምርት በአግባቡ ለማስተዳደር ነው።
° በመንግሥት በኩል የነዳጅ አቅርቦትን የማበራከት አላማ የለም።
° አዋጁ በእያንዳዱ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ ባሉት ተዋናዮች ላይ የህግ ሪስትሪክሽኖችን ይጥላል። የአቅራቢ፣ የማደያ ... ግዴታዎች አሉ።
° ግብይታችን ችግር አለበት። የአቅርቦት ችግር ሳይኖር ስርጭት ላይ ትልቅ ችግር አለ። የታሰበላቸው ቦታ ያለመድረስን በተመለከተ በክልሎች የሚቀርበው ቅሬታ ገሚሱ ትክክል ነው።
° ነዳጅ አለ !! ሳምንት ሁለት ሳምንት ገበያ ማስራብ ፣ በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ ነዳጅ ይዞ ' ቤንዚን የለም ፤ ናፍጣ የለም ' ብሎ መለጠፍ ይሄ ደግሞ ተጠያቂነት የማያስከትልበት ሴክተራል ባህሪው እንዲቀየር ይታሰባል፤ ይፈለጋል በመንግሥት በኩል ለዛም ነው ይሄ አዋጅ የሚወጣው።
° ከዚህ በኃላ ንግድን አንከለክልም እናሰፋዋለን ፤ ግብይቱ እንዲሳለጥ እንፈልጋለን ነገር ግን ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል።
° የነዳጅ ኮታ እና ስርጭት ላይ ፍትሃዊ ስርዓት ለመፍጠር ይሰራል።
° ከአቅርቦት እና ስርጭት ይልቅ ማስተዳደሩ ከባድ ነው።
° ነዳጅ እያላቸው ዘግተው የሚቀመጡ ማደያዎች በስፋት አሉ። የቅጣት መጠኑ ላይ ጠንካራ ስራ ይሰራል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሪፖርተር እንዲሁም ከህ/ተ/ም/ቤት የቀጥታ ስርጭት ማግኘቱን ይገልጻል።
#ኢትዮጵያ #ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ
@tikvahethiopia
🔴" ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ ንግድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ አረጋግጠናል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
🔵 " ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል " - ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
በህገወጥ የነዳጅ ግብይት የታየዘ ግለሰብ ነዳጁ ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስራትና እስከ 100 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ።
ረቂቁ ምን ይላል ?
- አዲስ የነዳጅ ምርት አከፋፋዮች ስራ ለመጀመር ቢያንስ 500 ሺህ ሊትር የነዳጅ ውጤቶች መያዝ የሚችል ማከማቻ / ዴፖ እና 4 ማደያዎችን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ያስገድዳል።
- በስራ ላይ ያሉ ማደያዎች ደግሞ አዋጁ ከሚጸድቅበት ጊዜ ጀምሮ ለአዲስ አከፋፋዮች የተጣሉትን ግዴታዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- አዲስ ጀማሪ ሆኑ ነባሮቹ በ3 ዓመታት ውስጥ ተጨማሪ 6 ማደያዎችን የመገንባት ግዴታ አለባቸው።
- የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ያከማቸ፣ ሊሸጥ ከሚገባው ሰው ቦታና የግብይት ስርዓት ውጭ ሲሸጥ የተገኘ ወይም አደጋ ያስከትላሉ በተባሉ መያዣዎች ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ የተያዘው የነዳጅ ውጤት ተወርሶ ከ3 ዓመት በማይበልጥ እስርና ከብር 50 ሺህ እስከ ብር 100 ሺህ የሚደርስ ቅጣት ይፈጸምበታል።
- መንግሥት ከሚያወጣው የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ተመን ውጪ በተደጋጋሚ የመገበያየት ወንጀል እንዲሁም የነዳጅ ምርቶችን ከባዕድ ነገሮች ጋር መቀላቀል እስከ 3 ዓመት እስርና እስከ 300 ሺህ ብር ቅጣት ያስጥላል።
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ እስመለአለም ምህረቱ ምን አሉ ?
አሁን አሁን ወደነዳጅ አቅራቢነት ስራ ለመሰማራት ከፍተኛ ፍላጎት እየታየ ነው ብለዋል።
በድርጅቱ በተደረገው ጥናት ይህ ፍላጎት የኮንትሮባንድ ንግድ እና ከባንክ ብድር ለመወሰድ ተብሎ የሚደረግ እንደሆነ ተደርሶበታል ሲሉ ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ፥ በዚህ 9 እና 10 ዓመት ውስጥ ከነበሩት 8 ወይም 9 ካምፓኒዎች አሁን 59 መድረሳቸውን ጠቁመዋል።
3ቱ የመንግሥት ገንዘብ አባክነው በፍርድ ቤት ክርክር ላይ ናቸው።
56ቱ ካምፓኒዎችን በማርኬትሼር በመደልደል ነዳጅ እየተሰጠ መሆኑን የገለጹ ሲሆን " ይህ ሁኔታ እራሱ እስካሁን ስምምነት የሌለበት ሁልጊዜ ጭቅጭቅ ያለበት ድርጊት ነው " ብለዋል።
ወደ ነዳጅ ግብይት አዲስ የሚገቡ ካምፓኒዎችን በተመለከተ ምንድነው አላማቸው ? ለምንድነው እንዲህ እያደገ የመጣው የሚለው መጠናቱን ገልጸዋል።
በጥናቱ ውጤትም " ዋናው ነገር ኮንትሮባንድ መስራታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከባንኮች ብድር መውሰጃ እንደሆነ ነው የተረጋገጠው " ብለዋል።
እነዚህ የነዳጅ ካምፓኒዎች ባንኮች ጋር ሄደው ብድር በሚጠይቁበት ጊዜ ባንኮቹ " ከናተ ጋር ያላቸው የሥራ አፈጻጸም ይጻፍልን " እየተባለ ደብዳቤ እንደሚጻፍ ገልጸዋል።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
° አዋጁ አላማ መንግሥት በየዓመቱ በሚሊዮን ዶላሮች የሚያወጣበትን ለነዳጅ ምርት በአግባቡ ለማስተዳደር ነው።
° በመንግሥት በኩል የነዳጅ አቅርቦትን የማበራከት አላማ የለም።
° አዋጁ በእያንዳዱ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ ባሉት ተዋናዮች ላይ የህግ ሪስትሪክሽኖችን ይጥላል። የአቅራቢ፣ የማደያ ... ግዴታዎች አሉ።
° ግብይታችን ችግር አለበት። የአቅርቦት ችግር ሳይኖር ስርጭት ላይ ትልቅ ችግር አለ። የታሰበላቸው ቦታ ያለመድረስን በተመለከተ በክልሎች የሚቀርበው ቅሬታ ገሚሱ ትክክል ነው።
° ነዳጅ አለ !! ሳምንት ሁለት ሳምንት ገበያ ማስራብ ፣ በነዳጅ ማደያዎች ውስጥ ነዳጅ ይዞ ' ቤንዚን የለም ፤ ናፍጣ የለም ' ብሎ መለጠፍ ይሄ ደግሞ ተጠያቂነት የማያስከትልበት ሴክተራል ባህሪው እንዲቀየር ይታሰባል፤ ይፈለጋል በመንግሥት በኩል ለዛም ነው ይሄ አዋጅ የሚወጣው።
° ከዚህ በኃላ ንግድን አንከለክልም እናሰፋዋለን ፤ ግብይቱ እንዲሳለጥ እንፈልጋለን ነገር ግን ለኮንትሮባንድ ንግድና ብድር ማግኛ ብሎ የገባው ኩባንያ ስርዓት ይይዛል።
° የነዳጅ ኮታ እና ስርጭት ላይ ፍትሃዊ ስርዓት ለመፍጠር ይሰራል።
° ከአቅርቦት እና ስርጭት ይልቅ ማስተዳደሩ ከባድ ነው።
° ነዳጅ እያላቸው ዘግተው የሚቀመጡ ማደያዎች በስፋት አሉ። የቅጣት መጠኑ ላይ ጠንካራ ስራ ይሰራል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሪፖርተር እንዲሁም ከህ/ተ/ም/ቤት የቀጥታ ስርጭት ማግኘቱን ይገልጻል።
#ኢትዮጵያ #ነዳጅ #ረቂቅአዋጅ
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ፋይዳ #ዲጂታል_መታወቂያ
በፋይዳ ይታወቁ ፣ በፋይዳ ይገልገሉ ፣ በፋይዳ ይዘምኑ!!!
ፋይዳ ለኢትዮዺያ!
Addis Ababa CRRSA - Civil Registration and Residency Service Agency Ethio telecom
#ፋይዳ #መታወቅ #DigitalID #fayda
በፋይዳ ይታወቁ ፣ በፋይዳ ይገልገሉ ፣ በፋይዳ ይዘምኑ!!!
ፋይዳ ለኢትዮዺያ!
Addis Ababa CRRSA - Civil Registration and Residency Service Agency Ethio telecom
#ፋይዳ #መታወቅ #DigitalID #fayda
📣 ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል መታወቂያ ካርድ ኅትመት በቴሌብር ሱፐርአፕ ጀመረ!!
💁♂️ ቴሌብር ሱፐርአፕ ላይ ‘’NID (Fayda) Printing’’ በሚለው ሚኒ መተግበሪያ ተጠቅመው የፋይዳ ቁጥርዎን በማስገባትና ክፍያዎን በመፈጸም በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ የዲጂታል መታወቂያ ካርድዎን ይረከቡ፡፡
📍 በመዲናችን የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/3UT6rY3
🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ይጫኑ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
💁♂️ ቴሌብር ሱፐርአፕ ላይ ‘’NID (Fayda) Printing’’ በሚለው ሚኒ መተግበሪያ ተጠቅመው የፋይዳ ቁጥርዎን በማስገባትና ክፍያዎን በመፈጸም በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ የዲጂታል መታወቂያ ካርድዎን ይረከቡ፡፡
📍 በመዲናችን የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/3UT6rY3
🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ይጫኑ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
#ሴጅ_ማሰልጠኛ
ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principles and Practices of Accounting) የ3 ወር እና 6 ወር የቀንና የማታ መርሐግብር ስልጠና በፒያሣ እና መገናኛ ካምፓስ ካምፓስ ሰኞ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
ስልክ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://yangx.top/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principles and Practices of Accounting) የ3 ወር እና 6 ወር የቀንና የማታ መርሐግብር ስልጠና በፒያሣ እና መገናኛ ካምፓስ ካምፓስ ሰኞ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
ስልክ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://yangx.top/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለ2017 በጀት አመት 971.2 ቢሊዮን ብር በጀት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። ከጸደቀው ገንዘብ ውስጥ ፦ ➡️ 451,307,221,052 ለመደበኛ ወጪዎች ➡️ 283,199,335,412 ለካፒታል ወጪዎች ➡️ 222,694,109,445 ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ ➡️ 14,000,000,000 ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የተመደበ ነው፡፡ @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ
የዘንድሮው በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የአጠቃላይ በጀት 1.5 ትሪሊየን ብር ሆኗል።
ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 582 ቢሊየን ብር ተጨማሪ የፌደራል መንግስት በጀት አፅድቋል።
ለ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ ሆኖ የፀደቀው በጀት ፦
- ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ዕዳ ክፍያ፣
- ለማህበራዊ በጀት ድጎማ (ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያ፣ ለመድሐኒት፣ ለምግብ ዘይትና ሌሎች)፣
- ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፋፊያ፣
- ለማህበራዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም እና ለመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ እንደሚውል የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አሳውቀዋል።
ከተጨማሪ በጀቱ ለመደበኛ ወጪ 393 ቢሊዮን ፣ ለካፒታል ወጪ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለወጪ አሸፋፈን ማስተካከያ 119 ቢሊዮን ብር ይውላል።
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ?
- ተጨማሪ በጀቱ አልባዛም ወይ ?
- በገበያ ውስጥ የዋጋ ግሽበትን አያስከትምልም ወይ ?
- ከተጨማሪ በጀቱ 282 ቢሊየን ብር ከግብር የሚሰበሰብ ከሆነ በግብር ከፋዮች ላይ ጫና አያሳድርም ወይ ? የሚል ጥያቄ አቅርበዋል።
የገንዘብ ሚኒትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ " የቀረበው ተጨማሪ በጀት120 ሚሊየን ህዝብ ላላትና በኢኮኖሚ በማደግ ላይ ላለች ሀገር ብዙ የሚባል አይደለም " ብለዋል።
" በጀቱ ከሀገር ውስጥ እና ከውጪ ከሚገኝ ገቢ የሚሸፈንና ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች እንዲሁም ለሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች የሚውል በመሆኑ በዋጋ ግሽበቱ ላይ ለውጥ አያመጣም " ሲሉ መልሰዋል።
ምክር ቤቱ ተጨማሪ በጀቱን በ3 ተቃውሞ እና በ5 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቆታዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
@tikvahethiopia
የዘንድሮው በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የአጠቃላይ በጀት 1.5 ትሪሊየን ብር ሆኗል።
ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 582 ቢሊየን ብር ተጨማሪ የፌደራል መንግስት በጀት አፅድቋል።
ለ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ ሆኖ የፀደቀው በጀት ፦
- ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ዕዳ ክፍያ፣
- ለማህበራዊ በጀት ድጎማ (ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያ፣ ለመድሐኒት፣ ለምግብ ዘይትና ሌሎች)፣
- ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፋፊያ፣
- ለማህበራዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም እና ለመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ እንደሚውል የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አሳውቀዋል።
ከተጨማሪ በጀቱ ለመደበኛ ወጪ 393 ቢሊዮን ፣ ለካፒታል ወጪ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለወጪ አሸፋፈን ማስተካከያ 119 ቢሊዮን ብር ይውላል።
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ?
- ተጨማሪ በጀቱ አልባዛም ወይ ?
- በገበያ ውስጥ የዋጋ ግሽበትን አያስከትምልም ወይ ?
- ከተጨማሪ በጀቱ 282 ቢሊየን ብር ከግብር የሚሰበሰብ ከሆነ በግብር ከፋዮች ላይ ጫና አያሳድርም ወይ ? የሚል ጥያቄ አቅርበዋል።
የገንዘብ ሚኒትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ " የቀረበው ተጨማሪ በጀት120 ሚሊየን ህዝብ ላላትና በኢኮኖሚ በማደግ ላይ ላለች ሀገር ብዙ የሚባል አይደለም " ብለዋል።
" በጀቱ ከሀገር ውስጥ እና ከውጪ ከሚገኝ ገቢ የሚሸፈንና ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች እንዲሁም ለሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች የሚውል በመሆኑ በዋጋ ግሽበቱ ላይ ለውጥ አያመጣም " ሲሉ መልሰዋል።
ምክር ቤቱ ተጨማሪ በጀቱን በ3 ተቃውሞ እና በ5 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቆታዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ የዘንድሮው በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የአጠቃላይ በጀት 1.5 ትሪሊየን ብር ሆኗል። ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 582 ቢሊየን ብር ተጨማሪ የፌደራል መንግስት በጀት አፅድቋል። ለ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ ሆኖ የፀደቀው በጀት ፦ - ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ዕዳ ክፍያ፣ - ለማህበራዊ በጀት ድጎማ (ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያ፣ ለመድሐኒት፣ ለምግብ ዘይትና ሌሎች)፣ - ለካፒታል ፕሮጀክቶች…
#ኢትዮጵያ
" ... የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል የደመወዝ ጭማሪ መጨመር ነበረበት " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
🔴 " አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል !! "
የህ/ተ/ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በተጨማሪ በጀቱ ዙሪያ ስጋቶች እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማሻሻያው ሀገራዊ ውጥቅጥ ውስጥ እንዳስገባን በግልጽ እንደሚታይ ተናግረው ይሄ በጀት እሱን ምን ያህል አ
ተደራሽ ያደርጋል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከዚህ ባለፈም ደሳለኝ (ዶ/ር) ፤ ስለ ኑሮ ውድነት ፣ ስለሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ፣ በጀቱን ለመሸፈን ስለሚጣል ግብር አንስተው ጠይቀዋል ፤ ሃሳባቸውን አካፍለዋል።
ምን አሉ ?
" በኑሮ ውድነት ላይ / ቋሚ ደመወዝተኛ በሆነው አካል ላይ የውጭ ምንዛሬው (Foreign exchange) ለውጡ የፈጠረው ጫና አለ።
አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል ፤ በውጭ ምንዛሬው ለውጥ ምክንያት።
መንግሥት የደመወዝ ማሻሻያ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ተቀጣሪዎችን ደመወዝ ማሻሻያ አድርጊያለሁ ቢልም አብዛኛው ደመወዝተኛ ከ1 ሺህ ብር እና ከ2 ሺህ ብር በላይ ጭማሪ አልተደረገለትም። ስለዚህ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች ኑሯቸውን እንዴት እንዲመሩ ታስቦ ነው ?
በእኔ በኩል ቢያንስ መንግሥት ሌሎች የmarket variables ትቶ የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል ጭማሪ መጨመር ነበረበት።
አንድ የ12 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ከምንዛሬ ለውጡ በፊት ወደ 300 እስከ 350 ዶላር አካባቢ ያገኝ ነበር አሁን መንግሥት ጨመርኩ ያለው 1 ሺህ ብር ነው ወደ ዶላር ሲቀየር ደመወዙ የሚወድቀው ወደ 150 ዶላር አካባቢ ነው።
ይህ ከፍተኛ ጫና፣ የመንግሥት ሰራተኛውን ወደ ልመና፣ ወደ ጎዳና እያስወጣው እንደሆነ መሸፈን በማንችልበት ሁኔታ ዘገባዎች እየወጡ ነው።
ስለዚህ ይህን በስነስርዓት address በሚያደርግ መንገድ የደመወዝ ማስተካከያው መስተካከል ነበረበት። ጭማሪውም ለዛ ትኩረት መስጠት ነበረበት።
ሌላው የ281.5 ቢሊዮን ተጨማሪ ታክስ raise በማድረግ ይሄን 532 ቢሊዮን ተጨማሪ በጀት ለመሸፈን ከሚደረገው ውስጥ አንደኛው ታክሱ ነው።
ይህ ከፍተኛ የታክስ ጫና (burden) ነጋዴው ላይ የሚጭን ነው። ነጋዴው ላይ ከፍተኛ የታክስ ጫና እየፈጠረ ነው። የንግዱ ማህበረሰብን ከፍተኛ confusion (መደናገር) ውስጥ እየተከተተው ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ ቀድሞውኑ shock ውስጥ ነው ቢዝነሱ ፤ ብዙ ነጋዴዎች confusion ውስጥ እንደገቡ ይናገራሉ ከዛ ላይ ተጨማሪ confusion እና ተጨማሪ መደናገጥ እንዲሁም shock የሚፈጥር ነው ይሄ እንዴት ታስቦ ነው ?
መንግሥት fair በሆነ መንገድ ከከፍተኛ ታክስ ከፋዩ ላይ ከሚደበቁትን፣ የታክስ ሆሎችን ተጠቅመው የሚሰወሩትን እሱን መሰብሰብ አለበት በእርግጠኝነት ፤ ግን ደግሞ ከአቅም በላይ የሆነውን የመንግሥት spending compensate ለማድረግ ሲባል የታክስ ጫናውን ከአቅም በላይ መለጠጥ በንግድ እንቅስቃሴው ላይ በተለይ በሀገር ውስጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለው ችግር በደንብ ተገምግሟል ? የሚኒስትሮች ም/ቤት ይሄን እንዴት አይቶት ነው ?
ሌው ጭማሪው 532 ቢሊዮኑ በዋነኝነት ለዕዳ ክፍያ፣ ለማህበራዊ ድጎማ ፣ ለደመወዝ ጭማሪ እንደሚውል ነው የተገለጸው።
ባለፈው 971 ቢሊዮኑ በጀቱ ሲፀድቅ አሁንም የካፒታል ፕሮጀክቶችን ጉዳይ አንስቼ ነበር። መንግሥት literally ትቶታል።
- አዲስ መንገድ
- አዲስ ግድብ
- አዲስ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ ሆስፒታል ... አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን መተው የሚታየው አሁን በተጨመረው 582 ቢሊዮን ውስጥ 90 ቢሊዮን ብቻ የካፒታል ፕሮጀክት ማሻሻያ ብቻ ነው የተካተተው።
ሌላው ነገር የለም። already እያልን ያለነው ኮሪደር ልማት ብቻ እንስራ ነው። እንደዚህ ሆኖ ሀገር እንዴት ሊለማ ይችላል ? መሰረታዊ የሚባሉ የ irrigation development ፣ ግድቦች ላይ ፣ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ፣ ፈጣን መንገዶች ላይ ፣ የኃይል ተቋማት ላይ፣ ሆስፒታሎች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እንዲህ አይነት critical የሆኑ የህዝብ መሰረተ ልማቶች ላይ በጀታችንን ካላዋልነው አሁንም ዞሮ ዞሮ የማብለጭለጭ አይነት ልማት structurally ምንም ለውጥ የማያመጣ ልማት ላይ ነው እንዳለ ገንዘባችንን ፈሰስ እያደረግን ያለነው። እዚህ ላይ ስጋት አለኝ።
መሰረታዊ የሚባሉ investment ላይ መንግሥት ውጪውን ቅድሚያ መስጠት አለበት። "
#TikvahEthiopia #ደመወዝ #ዶክተርደሳለኝጫኔ
@tikvahethiopia
" ... የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል የደመወዝ ጭማሪ መጨመር ነበረበት " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
🔴 " አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል !! "
የህ/ተ/ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በተጨማሪ በጀቱ ዙሪያ ስጋቶች እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማሻሻያው ሀገራዊ ውጥቅጥ ውስጥ እንዳስገባን በግልጽ እንደሚታይ ተናግረው ይሄ በጀት እሱን ምን ያህል አ
ተደራሽ ያደርጋል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከዚህ ባለፈም ደሳለኝ (ዶ/ር) ፤ ስለ ኑሮ ውድነት ፣ ስለሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ፣ በጀቱን ለመሸፈን ስለሚጣል ግብር አንስተው ጠይቀዋል ፤ ሃሳባቸውን አካፍለዋል።
ምን አሉ ?
" በኑሮ ውድነት ላይ / ቋሚ ደመወዝተኛ በሆነው አካል ላይ የውጭ ምንዛሬው (Foreign exchange) ለውጡ የፈጠረው ጫና አለ።
አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል ፤ በውጭ ምንዛሬው ለውጥ ምክንያት።
መንግሥት የደመወዝ ማሻሻያ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ተቀጣሪዎችን ደመወዝ ማሻሻያ አድርጊያለሁ ቢልም አብዛኛው ደመወዝተኛ ከ1 ሺህ ብር እና ከ2 ሺህ ብር በላይ ጭማሪ አልተደረገለትም። ስለዚህ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች ኑሯቸውን እንዴት እንዲመሩ ታስቦ ነው ?
በእኔ በኩል ቢያንስ መንግሥት ሌሎች የmarket variables ትቶ የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል ጭማሪ መጨመር ነበረበት።
አንድ የ12 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ከምንዛሬ ለውጡ በፊት ወደ 300 እስከ 350 ዶላር አካባቢ ያገኝ ነበር አሁን መንግሥት ጨመርኩ ያለው 1 ሺህ ብር ነው ወደ ዶላር ሲቀየር ደመወዙ የሚወድቀው ወደ 150 ዶላር አካባቢ ነው።
ይህ ከፍተኛ ጫና፣ የመንግሥት ሰራተኛውን ወደ ልመና፣ ወደ ጎዳና እያስወጣው እንደሆነ መሸፈን በማንችልበት ሁኔታ ዘገባዎች እየወጡ ነው።
ስለዚህ ይህን በስነስርዓት address በሚያደርግ መንገድ የደመወዝ ማስተካከያው መስተካከል ነበረበት። ጭማሪውም ለዛ ትኩረት መስጠት ነበረበት።
ሌላው የ281.5 ቢሊዮን ተጨማሪ ታክስ raise በማድረግ ይሄን 532 ቢሊዮን ተጨማሪ በጀት ለመሸፈን ከሚደረገው ውስጥ አንደኛው ታክሱ ነው።
ይህ ከፍተኛ የታክስ ጫና (burden) ነጋዴው ላይ የሚጭን ነው። ነጋዴው ላይ ከፍተኛ የታክስ ጫና እየፈጠረ ነው። የንግዱ ማህበረሰብን ከፍተኛ confusion (መደናገር) ውስጥ እየተከተተው ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ ቀድሞውኑ shock ውስጥ ነው ቢዝነሱ ፤ ብዙ ነጋዴዎች confusion ውስጥ እንደገቡ ይናገራሉ ከዛ ላይ ተጨማሪ confusion እና ተጨማሪ መደናገጥ እንዲሁም shock የሚፈጥር ነው ይሄ እንዴት ታስቦ ነው ?
መንግሥት fair በሆነ መንገድ ከከፍተኛ ታክስ ከፋዩ ላይ ከሚደበቁትን፣ የታክስ ሆሎችን ተጠቅመው የሚሰወሩትን እሱን መሰብሰብ አለበት በእርግጠኝነት ፤ ግን ደግሞ ከአቅም በላይ የሆነውን የመንግሥት spending compensate ለማድረግ ሲባል የታክስ ጫናውን ከአቅም በላይ መለጠጥ በንግድ እንቅስቃሴው ላይ በተለይ በሀገር ውስጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለው ችግር በደንብ ተገምግሟል ? የሚኒስትሮች ም/ቤት ይሄን እንዴት አይቶት ነው ?
ሌው ጭማሪው 532 ቢሊዮኑ በዋነኝነት ለዕዳ ክፍያ፣ ለማህበራዊ ድጎማ ፣ ለደመወዝ ጭማሪ እንደሚውል ነው የተገለጸው።
ባለፈው 971 ቢሊዮኑ በጀቱ ሲፀድቅ አሁንም የካፒታል ፕሮጀክቶችን ጉዳይ አንስቼ ነበር። መንግሥት literally ትቶታል።
- አዲስ መንገድ
- አዲስ ግድብ
- አዲስ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ ሆስፒታል ... አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን መተው የሚታየው አሁን በተጨመረው 582 ቢሊዮን ውስጥ 90 ቢሊዮን ብቻ የካፒታል ፕሮጀክት ማሻሻያ ብቻ ነው የተካተተው።
ሌላው ነገር የለም። already እያልን ያለነው ኮሪደር ልማት ብቻ እንስራ ነው። እንደዚህ ሆኖ ሀገር እንዴት ሊለማ ይችላል ? መሰረታዊ የሚባሉ የ irrigation development ፣ ግድቦች ላይ ፣ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ፣ ፈጣን መንገዶች ላይ ፣ የኃይል ተቋማት ላይ፣ ሆስፒታሎች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እንዲህ አይነት critical የሆኑ የህዝብ መሰረተ ልማቶች ላይ በጀታችንን ካላዋልነው አሁንም ዞሮ ዞሮ የማብለጭለጭ አይነት ልማት structurally ምንም ለውጥ የማያመጣ ልማት ላይ ነው እንዳለ ገንዘባችንን ፈሰስ እያደረግን ያለነው። እዚህ ላይ ስጋት አለኝ።
መሰረታዊ የሚባሉ investment ላይ መንግሥት ውጪውን ቅድሚያ መስጠት አለበት። "
#TikvahEthiopia #ደመወዝ #ዶክተርደሳለኝጫኔ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update
" ሰባቱን ፍርድ ቤት ዋስትና እያስሞሉ ነው። ሌሎቹን ደግሞ ፈተዋቸዋል " - የኮሬ ዞን መምህራን ማኀበር
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ የሚገኙ መምህራን ያለፈቃዳቸው ከደመወዛቸው የተቆረጠ ገንዘብ እንዲመለስ በመጠየቃቸው መታሰራቸውን የዞኑና የክልሉ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ነው።
በአጠቃላይ ታስረው የነበሩት ከ66 በላይ እንደነበሩ፣ 22 የሚሆኑት መምህራን እስከዛሬ ድረስ በእስር ላይ እንደቆዩ፣ ቀሪዎቹ ግን ሰሞኑን እንደፈቷቸው የዞኑ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲገልጽ ነበር።
ከእስራት ያልተፈቱት ቀሪ 22ቱ መምህራን ዛሬ እንዲፈቱ ውይይት እየተደረገ እንደነበርም ማኀበሩ ጠቁሞ ነበር።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ በበኩሉ፣ 22ቱ መምህራን እንዲፈቱ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ገልጾ፣ ዛሬ እንደሚፈቱ ለቲክቫህ ተናግሯል።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰርበ አሻግሬ ዛሬ ከሰዓት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ደመወዛቸው የተቆረጠው ተስማምተው ስለመሆኑ ስም ዝርዝር እንዳላቸው ፤ በእስር ላይ ያሉትም እንደሚፈቱ ገልጸዋል።
ጥያቄያቸው ወይ የእነርሱ ይስተካከል ወይ የእኛ ይመለስ የሚል ቢሆን እኔም ከጎናቸው ነኝ ብለዋል።
አቶ ሰርበ አሻግሬ ምን አሉ ?
“ ተስማምተው ከቆረጡ በኋላ እኔም ጋ የመጡት ‘እኛ ቆርጠን ሌሎቹ አልቆረጡም፤ ልክ አይደለም ተነጋገሩ’ ብለው ነበር። እኔም ስልጠና ላይ ስለነበርኩ ነው የቆየነው።
መምህራኑ ይፈታሉ። ማታ ለሁለት በድን ነግሬአለሁ። የመጀመሪያዎቹ ዋና በጥባጮቹ ሰባት ናቸው። ‘እነርሱ ለምን ታሰሩ?’ ብለው የገቡት 15 ናቸው። 15ቱ ከትላንትና ወዲያም ይውጡ ተብሎ ‘አንድ ላይ ነው የምንወጣው’ ብለው ነው።
የእናንት የሁለታችሁ ኬዝ የተለያዬ ስለሆነ ነው። የእናንተ ከፓሊስ ጋር በመጋጨት ነው ውጡ ተብለው እኮ 15ቱ መምህራን አንወጣም ነው እኮ ያሉት።
የታሰሩት 22 መምህራን ናቸው። ሰባቱ ተማሪዎቹን አባረው መምህራንንም የጠበጡ ናቸው። አሁን 66 ታሰሩ የሚለው ውሸት ነው። ሰባቱ መጀመሪያ ተያዙ፤ 15 በኋላ ገቡ። ትላንት ውጡ ተብለው እምቢ ብለው ነው። ዛሬ ይወጣሉ። ” ብለዋል።
መምህራኑ ተፈተዋል ?
የዞኑ መምህራን ማኀበር ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ጭበጮ ምሽት 12 ሰዓት ገደማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በገለጹት መሠረት፣ መምህራኑ ከእስር ተፈትተዋል።
የማኀበሩ ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ሰባቱን ፍርድ ቤት ዋስትና እያስሞሉ ነው። ሌሉሎቹን ደግሞ ፈትተዋቸዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ሁሉም ተፈትተዋል ማለት ይቻላል? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ "ኦረዲ አዎ ለሰባቱ ብቻ ተያዢ ፈልገው ነው፡፡ ተያዦቹም ኦረዲ እየጨረሱ ናቸው" ብለዋል።
ተደበደቡ የተባሉት ምህራን እስከዛሬ ህክምና አግኝተው ነበር ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ ሳያገኙ እንደቆዩ የሚታከሙት ገና ካሁን ወዲያ እንደሆነ ምላሽ ሰጥተዋል።
የተፈቱት በምን ተስማምታችሁ ነው ? ለተሚለው የቲክቫህ ጥያቄ የሰጡት ማብራሪያ ደግሞ፣ መምህራኑና ትምህርት መምሪያው እንዲወያዩ፣ መምህራኑ ይመለስ ካሉ ገንዘቡ እንዲመለስ መወሰኑን ነው የገለጹት።
#Update - መምህራኑ ከእስር ተፈተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የሕግ ባለሙያውና ጠበቃው ምን ገጠማቸው ?
" ቅስም ይሰብራል ! " - የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አንዷለም በውቀቱ
🔴 " ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው !! "
የሕግ ባለሙያና ጠበቃ የሆኑት አንዷለም በውቀቱ ዛሬ እጅግ ቅስማቸውን የሰበረ ክስተት እንደገጠማቸው ገልጸዋል።
ነገሩ እንዲህ ነው ...
ባለፈው አርብ " ፒኮክ መናፈሻ " አካባቢ አትክልት በማምረት ስራ የሚተዳደሩ ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ቢሯቸው ይመጣሉ።
እነዚሁ ነዋሪዎች " ሰፈሩ ለልማት ሊነሳ ነው እየተባለ ነው። ከወላጆቻችን ዘመን ጀምሮ በአካባቢው ለ73 አመታት ቆይተናል። ድንገት ተነሱ ብንባል ምን ይዋጠን!? " ሲሉ ይገልጹላቸዋል።
እሳቸውም " መጀመሪያ የምትሄዱበትን ቦታ ማመቻቸት የመንግስት ግዴታ ነው። ያ ሳይሆን ለማስነሳት እንቅስቃሴ የሚደረግ ቢሆን ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቤ እግድ እንዲሰጣችሁ አደርጋለሁ ! " ብለዋቸው ይለያያሉ።
ቅዳሜ ጉዳዩ የሚታይበትን አግባብ ሲያዘጋጁ እንደዋሉ የሚናገሩት የሕግ ባለሙያው ፤ እሁድ ጠዋት ግን ስልክ ይደወልላቸው። በዚህም " ከቤተክርስትያን ስንመለስ ቤታችን እየፈረሰ አገኘነው " ሲሉ እነዚሁ ቤተሰቦች ይነግሯቸዋል።
እሳቸውም ከባልደረባቸው ጋር ወደ ቦታው ሄዱ።
አፅናንተዋቸው " መትረፍ የሚችለውን ለማስቆም እንሞክራለን " ይሏቸዋል።
እስከ ማታ ድረስ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጨምሮ ለሚመለከታቸው አካላት የህግ አቤቱታዎችን ሲያዘጋጁ ያመሻሉ።
ሰኞ ጠዋት ኮሚኒቲው ህጋዊ የህብረት ስራ ማህበር ያላቸው በመሆኑ በማህበራቸው ስም ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ኑርጋ ውክልና እንዲሰጧቸው እንደተነጋገሩ የሕግ ባለሙያው አመክተዋል።
ትላንት ከሰአት ሊቀመንበሩ የጠበቃ ውክልና ለመስጠት የማህበሩን የመመስረቻ ጽሁፍ ስላጡት ለማክሰኞ ጠዋት እንደሚሰጧቸው ቀጥሮ ይይዛሉ።
ዛሬ ጠዋት ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ከቤታቸው ሲወጡ ግን የማህበሩ አባላት ሰፈር ውስጥ ለማፍረሻ የመጣ ዶዘር ቆሟል።
ሌሎች አባላቶች ውክልና ለመስጠት ውልና ማስረጃ እየጠበቋቸው ነበር።
እንደ ሕግ ባለሙያው ማብራሪያ ሊቀመንበሩ አብራቸው ከቤት የወጡትን ባለቤታቸውን " መጣሁ እየሄድሽ ጠብቂኝ ! " ብለዋቸው ወደ ቤት ይመለሳሉ።
በኃላም በአንዲት ቀጭን ሲባጎ እራሳቸውን አንጠልጥለው እንደተገኘ አስረድተዋል።
የሕግ ባለሙያው ዛሬ ጠዋት 3:00 ላይ አቤቱታውን ይዘው የአቶ ዱላን ስልክ ሲጠብቁ እንደነበር ገልጸዋል። መጨረሻው ግን ፍጹም አሳዛኝ ነው የሆነ።
" ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው " ሲሉ የሕግ ባለሙያው ሁኔታውን በሀዘን ገልጸዋል።
" አቶ ዱላ ለ20 አመት ያህል በሊቀመንበርነት ያገለገሉትን ከ70 አመት በላይ በአንድ ቦታ የቆየውን ለፍቶ አዳሪ ማህበረሰብ ' ፌይል አደርጌያቸዋለሁ ' ብለው እራሳቸውን አጥፍተዋል " ያሉት የሕግ ባለሙያው " እኔም ያንን ኮሚኒቲ ፌይል አድርጌዋለሁ። ትላንት አቤቱታውን ባስገባ ምናልባት ሊቀመንበሩ ከውሳኔው ይቆጠብ ይሆን?! ከጠዋት ጀምሮ በሰቀቀን ውስጥ ነኝ! ቀብራቸው ነገ ይፈጸማል! ነፍሳቸውን ፈጣሪ ይቀበላት!! " ሲሉ ቃላቸውን ደምድመዋል።
#AddisAbaba
@tikvahethiopia
" ቅስም ይሰብራል ! " - የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አንዷለም በውቀቱ
🔴 " ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው !! "
የሕግ ባለሙያና ጠበቃ የሆኑት አንዷለም በውቀቱ ዛሬ እጅግ ቅስማቸውን የሰበረ ክስተት እንደገጠማቸው ገልጸዋል።
ነገሩ እንዲህ ነው ...
ባለፈው አርብ " ፒኮክ መናፈሻ " አካባቢ አትክልት በማምረት ስራ የሚተዳደሩ ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ቢሯቸው ይመጣሉ።
እነዚሁ ነዋሪዎች " ሰፈሩ ለልማት ሊነሳ ነው እየተባለ ነው። ከወላጆቻችን ዘመን ጀምሮ በአካባቢው ለ73 አመታት ቆይተናል። ድንገት ተነሱ ብንባል ምን ይዋጠን!? " ሲሉ ይገልጹላቸዋል።
እሳቸውም " መጀመሪያ የምትሄዱበትን ቦታ ማመቻቸት የመንግስት ግዴታ ነው። ያ ሳይሆን ለማስነሳት እንቅስቃሴ የሚደረግ ቢሆን ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቤ እግድ እንዲሰጣችሁ አደርጋለሁ ! " ብለዋቸው ይለያያሉ።
ቅዳሜ ጉዳዩ የሚታይበትን አግባብ ሲያዘጋጁ እንደዋሉ የሚናገሩት የሕግ ባለሙያው ፤ እሁድ ጠዋት ግን ስልክ ይደወልላቸው። በዚህም " ከቤተክርስትያን ስንመለስ ቤታችን እየፈረሰ አገኘነው " ሲሉ እነዚሁ ቤተሰቦች ይነግሯቸዋል።
እሳቸውም ከባልደረባቸው ጋር ወደ ቦታው ሄዱ።
አፅናንተዋቸው " መትረፍ የሚችለውን ለማስቆም እንሞክራለን " ይሏቸዋል።
እስከ ማታ ድረስ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጨምሮ ለሚመለከታቸው አካላት የህግ አቤቱታዎችን ሲያዘጋጁ ያመሻሉ።
ሰኞ ጠዋት ኮሚኒቲው ህጋዊ የህብረት ስራ ማህበር ያላቸው በመሆኑ በማህበራቸው ስም ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ኑርጋ ውክልና እንዲሰጧቸው እንደተነጋገሩ የሕግ ባለሙያው አመክተዋል።
ትላንት ከሰአት ሊቀመንበሩ የጠበቃ ውክልና ለመስጠት የማህበሩን የመመስረቻ ጽሁፍ ስላጡት ለማክሰኞ ጠዋት እንደሚሰጧቸው ቀጥሮ ይይዛሉ።
ዛሬ ጠዋት ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ከቤታቸው ሲወጡ ግን የማህበሩ አባላት ሰፈር ውስጥ ለማፍረሻ የመጣ ዶዘር ቆሟል።
ሌሎች አባላቶች ውክልና ለመስጠት ውልና ማስረጃ እየጠበቋቸው ነበር።
እንደ ሕግ ባለሙያው ማብራሪያ ሊቀመንበሩ አብራቸው ከቤት የወጡትን ባለቤታቸውን " መጣሁ እየሄድሽ ጠብቂኝ ! " ብለዋቸው ወደ ቤት ይመለሳሉ።
በኃላም በአንዲት ቀጭን ሲባጎ እራሳቸውን አንጠልጥለው እንደተገኘ አስረድተዋል።
የሕግ ባለሙያው ዛሬ ጠዋት 3:00 ላይ አቤቱታውን ይዘው የአቶ ዱላን ስልክ ሲጠብቁ እንደነበር ገልጸዋል። መጨረሻው ግን ፍጹም አሳዛኝ ነው የሆነ።
" ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው " ሲሉ የሕግ ባለሙያው ሁኔታውን በሀዘን ገልጸዋል።
" አቶ ዱላ ለ20 አመት ያህል በሊቀመንበርነት ያገለገሉትን ከ70 አመት በላይ በአንድ ቦታ የቆየውን ለፍቶ አዳሪ ማህበረሰብ ' ፌይል አደርጌያቸዋለሁ ' ብለው እራሳቸውን አጥፍተዋል " ያሉት የሕግ ባለሙያው " እኔም ያንን ኮሚኒቲ ፌይል አድርጌዋለሁ። ትላንት አቤቱታውን ባስገባ ምናልባት ሊቀመንበሩ ከውሳኔው ይቆጠብ ይሆን?! ከጠዋት ጀምሮ በሰቀቀን ውስጥ ነኝ! ቀብራቸው ነገ ይፈጸማል! ነፍሳቸውን ፈጣሪ ይቀበላት!! " ሲሉ ቃላቸውን ደምድመዋል።
#AddisAbaba
@tikvahethiopia