TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#FilmScholarship

ታላቅ የስኮላርሺፕ ዕድል ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች ከመልቲቾይስ አፍሪካ!

በዲኤስቲቪ /መልቲቾይስ ታለንት ፋክተሪ/ ለአንድ ዓመት ለወጣት የፊልም ባለሙያዎች የሚሰጥ ነጻ የስልጠና ስኮላርሺፕ ዕድል ተካፋይ ለመሆን ማጎልበት የምትፈልጉ ዕድሜያችሁ ከ18-26 ዓመት የሆናችሁ ወጣት የፊልም ባለሙያዎች እስከ መስከረም 5 ቀን, 2017 ዓ.ም (September 15, 2024) ድረስ በ applications.multichoicetalentfactory.com ላይ እንድታመለክቱ ተጋብዛችኋል፡፡

ማሳሰቢያ፡ አመልካቾች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታና ጊዜው ያላለፈበት ፓስፖርት ሊኖራችሁ ይገባል!!

Take the first step towards realising your dreams and apply now. Your journey to success starts here!

#MultiChoiceTalentFactory #DStvEthiopia
@heyonlinemarket

•PlayStation 5, 73,000 Birr
•Playstaion 5 Slim, 78,000 Birr

•PlayStation 4 Slim, 37,000 Birr
•PlayStation 4 Pro, 43,000 Birr

•Playstaion portal, 25,000 Birr
•Meta Quest 2, 45,000 Birr
•Meta Quest 3, 73,000 Birr

Contact
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
🔈#የነዋሪዎችድምፅ

“ በጣም አንገብጋቢ የሆነው የጤና ችግር ነው፡፡ ሆስፒታል ስለሌለ እናቶች ሪፈር ሲባሉ ደም እየፈሰሳቸው መንገድ ላይ ይሞታሉ ” - ነዋሪዎች

በአማራ ክልል፣ በሰሜን ጎንደር ዞን የበየዳ ወረዳ ነዋሪዎች፣ “ በክልሉ በሚካሄደው የተኩስ ልውውጥ ከሚደርስብን ግፉ በተጨማሪ የጤና፣ የመብራት፣ የትራንስፖርትና የኔቶርክ አገልግሎት ባለመኖራቸው በከፋ ስቃይ ውሰጥ ነን ” ሲሉ አማረዋል፡፡

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የወረዳው ነዋሪዎች፤ ለችግሩ መፍትሄ እንዲሰጡ ባለድርሻ አካላትን በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ሰሚ እንዳላገኙ፣ በመጨረሻም በሚዲያ በኩል ምሬታቸው ለማሰማት እንደተገደዱ አስረድተዋል፡፡

ስለተማረሩባቸው ጉዳዮች ነዋሪዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ በበየዳ ወረዳ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ናቸው ያሉት፡፡ በጣም አንገብጋቢ የሆነው የጤና ችግር ነው፡፡ በወረዳው ሆስፒታል ስለሌለ እናቶች ሪፈር ሲባሉ ደም እየፈሰሳቸው መንገድ ላይ ይሞታሉ፡፡

ይህ የሚሆነው ሆስፒታል ባለመኖሩ ከበየዳ ወደ ደባርቅ ሪፈር ሲባሉ ነው፡፡ ከወረዳው ወደ ዞኑ ለመሄድ መንገዱ ሩቅ ከመሆኑ መንገድ የሚወልዱ እናቶች አሉ፡፡ በወረዳው ጤና ጣቢያ ብቻ ነው ያለው።

ሌላው ደግሞ፣ በወረዳው መብራት የለም፡፡ በጀነሬተር ከቀኑ 2 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት፤ ከምሽቱ ከ12 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት ነው የሚሰራው፡፡ አሁን ደግሞ ከግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ጠፍቷል፡፡

ለአንድ ወር ብቻ በጀኔሬተር ይሰራል፡፡ ከዚያ በኋላ ለ4 ወራት ይጠፋል፡፡ አንድ ስልክ አንድ ጊዜ ብቻ ቻርጅ ለማድረግ 25 ብር እንከፍላለን፡፡ በጣም ስቃይ ላይ ነን፡፡ በጨለማ ውስጥ እያደርን ነው፡፡

የትራንስፖርት ችግርም አለብን፡፡ ከወረዳው እስከ ደባርቅ ለ60 ኪ.ሜ መንገድ 350 ብር ለመክፈል እንገደዳለን፡፡ ይህ ክፍያ ለአንድ ጉዞ ብቻ ነው፡፡ ታሪፍ የለውም፤ እንደፈለጉ ነው ህዝቡን የሚበዘብዙት፡፡

ሁለት አውቶብሶች ብቻ ናቸው ያሉት፡፡ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎች ቁጥር ደግሞ ብዙ ነው፡፡ የተሳፋሪ ወንበር ለማግኘት ለደላላ 50 ብር መክፈል ግድ ይላል፡፡

ለዚያውም ከ50 በላይ ሰዎችን መያዝ በማይችል ተሽከርካሪ እስከ 90 ተሳፋሪዎችን አጭቀው በመጫን ነው፡፡ በዚህም ህፃናት፣ ነብሰ ጡሮች፣ አረጋዊያን እንኳ ተጨፍለቀው ነው የሚጓዙት፡፡ በጣም ይሰቃያሉ፡፡

እንዲሁም ከድል ይብዛና ልዋሬ መካከል ያለው መንገድ 27.3 ኪ.ሜ ነው፡፡ ለዚህም ነዋሪዎች ለትራንስፖርት ከ200 - 250 ብር ይጠየቃሉ፡፡ በዚህ ልክ በደል እየደረሰብን መሆኑ በጣም ያሳዝናል፡፡

በሌላ በኩል፣ በወረዳው ወደ ከ25 ቀበሌዎች አሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በ18 ቀበሌዎች የኔትወርክ አግልግሎት የለም፡፡ እኛ የበየዳ ነዋሪዎች ግን እንደ ማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ግብር እየከፈልን፣ መሰረተ ልማት እያለማን ነው፡፡ ሆኖም መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት አለመስጠቱ በጣም አሳዝኖናል፡፡

ባለድርሻ አካላትን ስንጠይቅም መልስ እንኳን በአግባቡ አይሰጡንም፡፡ ከዚህ በኋላ ግን ፈጣን ምላሽ የማይጠን ከሆነ ወደ ሌላ አቅጣጫ ለማምራት እንገደዳለን፡፡ ነገሩ ወደ መጥፎ ሁኔታ ከማምራቱ በፊት ለችግሩ በአፋጣኝ ምላሽ ይሰጠን፡፡

የተከበረው የኢትዮጵያ ህዝብ በደላችንን፤ ብሶታችን ይወቅልን ”
ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ቲክቫህም፤ ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጥ ወደ ሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢደረግም፣ ስልክ ለማንሳትም ሆነ መልዕክት ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆነም፡፡

አስተዳዳሩ ለሚያስተዳድረው ህዝብ ቅሬታ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ በመሆን ኃላፊነቱን የሚወጣ ከሆነ በድጋሚ የምንጠይቀው ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia

የገንዘብ ሚኒስቴር ፥ በአዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 በውሃ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል እና በትራንስፖርት አቅርቦት ላይ ስለሚከፈል የተጨማሪ እሴት ታክስ ማብራሪያ ሰጥቷል።

አነስተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል በመኖሪያ ቤቱ የሚጠቀመውን አማካይ ወርሃዊ የውሃና ኤሌክትሪክ ፍጆታ ከታክሱ ነፃ የሚያደርግ ሲሆን ከታክሱ ነፃ ከተደረገው በላይ የውሃና ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተፈፃሚ እንዲሆን ያደርጋል ተብሏል።

የትራንስፖርት አገልግሎትን በተመለከተ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የመሆን መብት ባለሶስት እግር ተሽከርካሪን ሳይጨምር ከስምንት መቀመጫ በታች ያላቸውን ሌሎች ተሽከርካሪዎች እንዳይመለከት ተደርጓል፡፡

አሁንም የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት አቅርቦቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ ሲሆን ባለሦስት እግር ተሽከርካሪን ሳይጨምር፣ አሽከርካሪውን ጨምሮ ከስምንት ሰው በታች የመጫን አቅም ያላቸውን ተሽከርካሪዎች በመጠቀም የሚሰጥ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲከፈልበት መደረጉን ገንዘብ ሚኒስቴር አመልክቷል።

(ሙሉ ማብራሪያው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ #ጎንደር🕯 በአማራ፣ ሰሜን ጎንደር ዞን 3 ወረዳዎች በመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ እና የተጎዱ ሰዎች ቁጥር በዛሬው ዕለት ጨምሯል። ሟች ወገኖቻችን 23 ደርሰዋል። የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖቻችን ደግሞ  8 መድረሳቸው ተነግሯል። ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችን አጠቃላይ ከ2 ሺህ 700 በላይ ናቸው። አደጋው የደረሰው በዞኑ በጠለምት፣ በጃናሞራ፣ በአዲአርቃይና በየዳ ወረዳዎች በሚገኙ…
#ትኩረት🚨

" የመሬት መንሸራተቱ እየጨመረ ነው፡፡ በዞኑ ከ50 ሺሕ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል " - ዞኑ


በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ከ50 ሺሕ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውንና እስካሁን የ5 ሰዎች አስከሬን እንዳልተገኘ ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰላምይሁን ሙላት በሰጡት ቃል፤ " የመሬት መንሸራተቱ እየጨመረ ነው፡፡ በዞኑ ከ50 ሺሕ በላይ ሰዎች ተፈናቅላዋል " ብለዋል።

የመሬት መንሸራተቱ ከዚህ ቀደም ካደረሰው ውጪ በሰዎች ሕይወት ላይ ተጨማሪ ጉዳት ባያደርስም በተለይ ጠለምት ወረዳ ላይ እንደቀጠለ መሆኑን አሰድተዋል።

ችግሩ የከፋ ከመሆኑ በሻገር ሊቆም ባለመቻሉ ለአደጋው ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በዘላቂነት ከችግሩ ለማውጣት፣ አደጋው የደረሰባቸውን ወገኖች ለመርዳት የሌሎች ድጋፍ እንደሚያሻው ዞኑ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርቧል፡፡

" ከመንግስት ውጪ ያሉ አካውንቶች ተገቢ አይደሉም፡፡ ግልጽነት የጎደላቸው ናቸው፡፡ የጣምራ አካውንት የተከፈተ አለ " ያሉት ኃላፊው፣ ተከታዩን አካውንት ልከዋል፡።

ድጋፍ ማድረግ የሚሹ በውጪም በውስጥም ያሉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000647478453 ወይም በአማራ ባንክ አካውንት ቁጥር 9900028121157 ድጋፍ እንዲያደርጉ ነው ጥሪ ያቀረቡት።

በመሬት መንሸራተት አደጋው 23 ሰዎች እንደሞቱ፣ 8 ሰዎች የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ 318 የቤት እንስሳት የጉዳቱ ሰለባ እንደሆኑ፣ 1,775 ሄክታር ማሳና 48 ቤቶቾ እንደወደሙ ዞኑ አስረድቷል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#MesiratEthiopia

💵 የኢንቬስትመንት ውል እና ድርድር ምን መምሰል አለበት? 📝

በዚህ ሃሳብ ዙሪያ ለምንሰጠው ስልጠና ይመዝገቡ 👇
📅 አርብ፣ ነሐሴ 24, 2016 ዓ.ም
🕑 ከቀኑ 8:00 - 11:00 ሰዓት
🔗 https://forms.gle/GnvR5rE7DRGXtfaP8

ቀድመው ይመዝገቡ ቦታዎን ያሲዙ!

#መስራት #ስራፈጠራ #MesiratEthiopia #Investment #Entrepreneurship #MesiratTraining
#Tigray

በትግራይ የክረምቱ ሃይለኛ ዝናብ ባስከተለው አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አልፋዋል።

በበርካታ የክልሉ አከባቢዎችም ከአሁን በፊት ታይቶ በማያውቅ መልኩ የመሬት መደርምስ አደጋ እየተከሰተ ነው።

ነሃሴ 17 እና 19/2016 ዓ.ም በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የሓውዜንና ብዘት ወረዳዎች የጣለ ሃይለኛ ዝናብና በጥልቅ ጉድጓድ በተጠራቀመ ውሃ የ7 እና 9 ዓመት እድሜ ህፃናት የሚገኙባቸው 4 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።

የሓውዜን ወረዳ ነዋሪ የሆኑ ህፃናቱ በአከባቢያቸው በሚገኘው በጥልቅ ጉድጓድ በተጠራቀመ የዝናብ ውሃ ሊዋኙ ሲሉ ነው ለህልፈት የተዳረጉት። 

በዞኑ ብዘት ወረዳ ነዋሪ የሆኑ የአንድ ቤተሰብ አባላት በሃይለኛ ዝናብ ምክንያት ቤታቸው በላያቸው ላይ ፈርሶ የ5 ልጆች አሳዳሪ የሆኑ ባልና ሚስት ወድያውኑ ህይወታቸው አልፏል።

ልጆቻቸው እቤት ስላልነበሩ የሟቾች ቁጥር ሊቀንስ እንደቻለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከወረዳው ያጋኘው መረጃ ያሳያል።

ልጆቹ ወላጅ እናት አባታቸውን አጥተው በፈረሰ ቤት ሜዳ ላይ መውደቃቸው ተገልጿል።

ከአሁን በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በክልሉ የተለያዩ አከባቢዎች የመሬት መደርመስ አደጋ ተከስቷል።

በአላጀና ሰለዋ ወረዳዎች በሚገኙ አራት የቀበሌ ገበሬ ማህበራት ፣ በእንደርታና ሕንጣሎ ወረዳዋች ፣ በዓዴትና ፀለምቲ ወረዳዎች የመሬት መደርመስ አደጋ መከሰቱ ከአከባቢዎቹ የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ🚨

“ በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ " - ኮሚሽኑ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 በተለምዶ ሰላም ሰፈር አካባቢ 4 ሜትር ከሚገመት ከፍተኛ ቦታ በተከሰተ የአለት ናዳ 3 ሰዎች መሞታቸውን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

አደጋው የደረሰው ዛሬ ነው።

የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ባደረጉት ጥረት የ8 ሰዎች ሕይወት ማትረፍ ተችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
- የአደጋው ምንስኤ ምንድን ነው ?
- ይህ አደጋ በከተማዋ ሲከሰት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ?
- ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት? የሚሉ ጥያቄዎችን ለኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ አቅርቧል፡፡

አቶ ንጋቱ ምን ምላሽ ሰጡ ?

“ እንዲህ አይነት አደጋዎች በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሜትሮሎጅ ኢንስቲትዩትም የመሬት መንሸራተት፣ ጎርፍ አደጋ ሊያጋጥም ስለሚችል ጥንቃቄ ይደረግ የሚል መረጃ ሲያስተላልፍ ነበር፡፡

ያልተጠበቀ ዝናብ ያጋጥማቸዋል የተባሉ ከተሞችን ሲጠቅስም አዲስ አበባም እዛ ውስጥ ተጠቅሳለች፡፡

በእርጥበት ምክንያት ናዳ፣ የአፈር መደርመስ ሊኖር ስለሚችል በተለይ እንቅስቃሴያቸውንና ኑራቸውን አፋፍ ሥር ያደረጉ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡

ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ላይ መፍትሄ ለመስጠት በሚደረገው ጥረትም የመፍትሄው አካል መሆን ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ ሰዎችን ከቦታው ማንሳት ሊያስፈልግ ይችላል።

አዲስ አበባ ላይ የአለት ናዳ አደጋ አጋጥሞ አያውቅም፣ አላስታውስም፡፡ በእርግጥ ደረጃቸውን ያልጠበቁ፣ የአደጋ ደህንነት መስፈርት ሳይጠብቁ አፋፍ ላይ የተሰሩ ቤቶች ተንደው የሰው ሕይወት ጠፍቶ ያውቃል።

ጠሮ መስጂድ የሚባለው (አዲስ ከተማ ፍለ ከተማ ውስጥ) ሰባት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈበት ሁኔታ ነበር ከኮንስትራክሽን ጥራት ጋር በተያያዘ፡፡

ይሄኛው (የአሁኑ የአለት አደጋ) እዛው መሬቱ ጋር ተያይዞ የበቀለው አለት ከዝናብ ብዛት በመሬት መሸርሸር የሚያጋጥም ነው፡፡

የአለት አደጋውን መስንስኤ ማጣራት የሚጠይቅ ነው ግን ከክረምቱ ወቅት ጋር የሚያያዝ ሊሆን ይችላል ብለን እንገምታለን፡፡ አደጋ የደረሰባቸው መኖሪያ ቤቶቹ ከታች ነው ያሉት፤ አለቱ ደግሞ አፋፍ ላይ ነው ያለው፡፡ በግምት ወደ 4 ሜትር ከፍታ አለው፡፡

ብዙ ጊዜ አፋፍ ላይ ተንጠልጥለው ያሉ ቤቶች ላይ የመውደቅ እድልም አለው፡፡ የሰዎቹም የአኗኗር ሁኔታ፣ የቤቱ አቀማመጥና ደረጃ አስተዋጽኦ አድርጓል። ”


#TikvaEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Urgent🚨

በአማራ ክልል፣ በሰሜን ጎንደር ዞን ፣ ጠለምት ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የበርካታ ወገኖቻችን ህይወት አልፏል።

በርካቶችም ችግር ላይ ወድቀዋል፤ ተፈናቅለዋል።

ለተፈናቃዮቹ አስቸኳይ ድጋፍ ያስፈልጋል።

ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ወረዳው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርቧል።

የወረዳው አስተዳደሪ አቶ ጋሻው እንግዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ቃል ፦

“ አካባቢው ከዚህ ቀደም በድርቅ የተጠቃ ነው፡፡ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ለተፈናቀሉት ነዋሪዎች ደግሞ ከ14, 400 በላይ እህል ያስፈልገናል።

የእርዳታ ምግብ ድጋፍ ፤ 480 ድንኳን / ሸራ ፣ እንደ ብረት ድስት፣ ሳፋ አይነት የቤት ቁሳቁሶች በአስቸኳይ የሚያስፈልጉ ናቸው። ”

#TikvahEthiopiaFamyAA

@tikvahethiopia