TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬም ሜዳሊያ ውስጥ አልገባንም። @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia

በ3000 ሜትር መሰናክል ፍጻሜ ወደ ማጠናቀቂያው በጥሩ ኃይል ወደፊት እየመጣ የነበረው እና ለኢትዮጵያ ሜዳሊያ ሊያስገኝ ይችላል ተብሎ የተጠበቀው ለሜቻ ግርማ ወድቆ ውድድሩን ማጠናቀቅ አልቻለም።

ጉዳቱ የከፋ እንዳይሆንበትና ጤናው  ደህና እንዲሆን እንመኛለን።

ሳሙኤል ፍሬው 6ኛ ፤ ጌትነት ዋለ ደግሞ 9ኛ ሆነው ነው የጨረሱት።

ሞሮኮ፣ አሜሪካ እና ኬንያ ሜዳሊያዎቹን ወስደዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#LamechaGirma : የ3,000 ሜትር መሰናክል ሪከርድ ባለቤቱ ለሜቻ ግርማ በውድድሩ ወቅት ሲዘል ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት በፍጥነት ወደ ሆስፒታል እንደተወሰደ ተነግሯል።

አትሌቱ በደረሰበት ጉዳት ሳቢያ እራሱን እንደሳተ አሁንም ሙሉ በሙሉ እንዳልነቃ ፤ በሆስፒታል በህክምና ላይ እንደሚገኝ ፤ ያለበት ሁኔታ ግን ለህይወቱ አስጊ የሚባል እንዳልሆነ ተሰምቷል።

ልጃችን ጉዳቱን ክፉ አያድርግበት ፤ ጤናውም አይጓደልበት !

ደህና ሆኖ ዳግም በውድድር መድረክ ላይ ሀገሩን ወክሎ እንድናየው እንመኛለን።

Photo Credit - AFP

@tikvahethsport @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

" በእግሩ እና በጭንቅላቱ ላይ ጉዳት አልደረሰበትም " - የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

ኢትዮጵያዊው አትሌት ለሜቻ ግርማ ራሱን ከሳተበት በመንቃት መናገር መጀመሩን ሌኪፕ የተሰኘው ታቃዊው የፈረንሳይ ጋዜጣ አስነብቧል።

በአሁን ሰዓት ተጨማሪ የህክምና ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝም ጋዜጣው ገልጿል።

የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ቃል አቀባይ በበኩላቸው ፤ " አትሌት ለሜቻ ግርማ አስፈላጊ የሆነ አፋጣኝ ህክምና ተደርጎለታል " ብለዋል።

ስለ ጉዳቱ ዝርዝርና የህክምና ውጤቱን በተመለከተ ግን በይፋ ምንም የተባለ ነገር የለም።

በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፥ " አትሌት ለሜቻ ግርማ በውድድሩ ላይ በደረሰበት የመውደቅ አደጋ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በተደረገለት የሲቲ ስካን ምርመራ በእግሩና በጭንቅላቱ ላይ ጉዳት እንዳልደረሰት ከሆስፒታል የሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች አረጋግጠዋል " ሲል በይፋ አሳውቋል።

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
2 ቀን ቀረው!

🏆 የአንድን ከተማ ሕዝብ በሁለት ጎራ የከፈሉት ማን ዩናይትድ እና ማን ሲቲ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋዜማ በኮሙኒቲ ሺልድ ዋንጫ ተፋጠዋል!

⚽️ ዩናይትድ እና ሲቲ የሚያደርጉትን የዋንጫ ፍልሚያ ቅዳሜ ነሐሴ 4 በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

🔥 ዋንጫው የማን ነው? 

ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ የኮሙኒቲ ሺልድ ጨዋታ ከትንታኔ እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ልዩ በቀጥታ ይከታተሉ!    

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
#አበሽጌ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ጉራጌ ዞን፣ አበሽጌ ወረዳ ዋልጋና ዳልጌ ከተሞች የሚኖሩ በተለይም የአማራ ወጣቶች ፣ ባለሀብቶችና አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች በጸጥታ ኃይል በአፈሳ እየተያዙ መሆናቸውን ተከትሎ ወጣቶች ከቤት ለመውጣት ፍርሀት ውስጥ መሆናቸው ተሰምቷል።

አካባቢው በተለይ ከኦሮሚያ ጋር የሚዋሰንባቸው መንደሮች ካሁን በፊት ግጭቶች መፈጸማቸውን ተከትሎ በስጋት መቆየታቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች ከሰሞኑ እየሆነ ያለው ነገር እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

ምንም እንኳን ወጣቱ በፍርሀት ቤቱ ቢቀመጥም አንዳንዶቹ ቤታቸዉ ባሉበት መያዛቸዉን ተከትሎ ፍርሀቱ ከፍ ሊል ችሏል።

ቃላቸውን የሰጡ አንዳድን ነዋሪዎች አፈሳው እየተደረገ ካለባቸው ምክንያቶች አንዳንዶቹ " እናተ ፋኖን ትደግፋላችሁ፤ ከፋኖ ጋርም ግንኙነት አላችሁ " የሚል ነው ብለዋል።

ሁኔታውን በተመለከተ ማን ማንን ነው እየያዘ ያለው ? ስንል የጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ገና ደገሞን ጣይቀናል።

እሳቸውም " የተቀናጀ የጸጥታ ኃይል ወንጀለኞችን እየያዙ ነው " ብለዋል።

በተጨማሪም ሰው ፍርሀት ውስጥ ነው ለሚባለው " ወንጀል ውስጥ እጁ ካለበት ሰው ውጭ ንጹሀኑ ፍርሀት ሊገባው አይገባም " ሲሉ መልሰዋል።

" አሁን ላይ የብሄራዊ ደህንነትን ጨምሮ የፌደራል ፖሊስና መከላከያ ሰራዊት በአካባቢዉ ተሰማርተዉ አሰሳ በማድረግ የጥፋት ኃይሎችን እየያዙ ነው " በማለት አካባቢዉ በፍጥነት ወደነበረ ሰላሙ ይመለሳል ብለዋል።

ዋና ኢንስፔክተሩ አክለዉ " እንቅስቃሴዉ በአበሽጌ ወረዳና በኦሮሚያ ወሰን መካከል መሆኑን በመግለጽ ሰላማዊ ሰዎች ያለስጋት የእለት ተእለት እንቅስቃሴያቸውን እንዲቀጥሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia ለተከታታይ ቀናት የውጭ ምዛሬ ዋጋ ባለበት እየቀጠለ ነው።

የንግድ ባንክ ዛሬም ለ5ኛ ተከታታይ ቀን የውጭ ምንዛሬው ላይ ምንም የተለየ ለውጥ ሳያደርግ ውሏል። ዶላር 95.6931 ይገዛል፣ 101.4347 ይሸጣል።

በግል ባንኮችም ያን ያህል ጭማሪ አልታየም።

ትላንትና ብሔራዊ ባንክ 27 ባንኮች በተሳተፉበት ባወጣው ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 107 ነጥብ 9 ብር ዋጋ መሸጡን ይታወሳል።

ይኸው አማካይ ዋጋ የዛሬ የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ጠቋሚ ሁኔታዎች ውስጥ አንዱ ነው ማለቱ አይዘነጋም።

በሌላ በኩል ምንም እንኳን በሀገሪቱ  ውስጥ ያሉት ባንኮች  በየዕለቱ የውጭ ምንዛሬ ዋጋቸውን እያወጡ ቢሆንም ዶላር እንደልብ ማግኘት ገና አልተጀመረም።

@tikvahethiopia